
ደስታ መብራቱ
በፒ ዲ ኤፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
_
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
ደስታ መብራቱ
በፒ ዲ ኤፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
_
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
ከአልማዝ አሸናፊ
ዋዮሚንግ: አሜሪካ
በቅድሚያ አምባገነንነት ማለት ምን ማለት ነው ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ከመስጠቴ በፊት : በኢትዮጵያ ውስጥ በድህነት ተወልጄ : በጉዲፈቻ ያሳደጉኝን አጎቴንና ባለቤቱን በቸሩ ፈጣሪ ስም አመሰግናለሁ:: ጥሩ ጭንቅላት ለግሶኝ በእቴጌ መነን ትምህርት ቤት በአዳሪነት ተምሬ የነፃ ትምህርት ዕድል በአሜሪካ እግኝቼ በመማር ዛሬ ላለሁበት ዕድሜና የኑሮ ደረጃ ላደረሰኝ አምላኬ ከፍ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ:: በዚህም አጋጣሚ ለእኔ ትምህርት አስተዋፅኦ ያደረገው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ስለሆነ : ከ86 ጎሳዎች በላይ ያለው ይህ ሕዝብ ለትምህርቴ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለሰጠኝ ስጦታ ሳላመሰግነው አላልፍም:: ይህንን የምልበት ምክንያት በመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ የተማሩ የዘመኑ ሊቆችና ፖለቲከኞች ያስተማራቸውን መላውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ዘንግተው በጎሳቸው አስተዋፅኦ ብቻ እንደተማሩ አድርገው የሌሎችን ጎሳዎች ውለታ ሲያሳጡና በጎሳዎች መሃል ጥላቻ በመፍጠር ሲያጋድሉና ሲያፋጁ ሳይ : እነዚህ ውለታቢሶች ጎሰኞችና ፅንፈኞች እንዴት ዝቃጮች እንደሆኑ መናገር ስለሚያስፈልግ ነው:: ሃቁ የማንኛውም ጎሳ አባል የተማረው በኦሮሞ : በአማራ : በትግሬ : በሱማሌ : በጋምቤላ: በወላይታ ወዘተ ኢትዮጵያውያን ተወላጆች አስተዋፅኦ ነው:: በአገር ውስጥም ሆነ በዲያስፓራ ያለው በኦሮሞ በትግራይ በአማራ ወዘተ ስም የሚነግደው የጎሳ ፖለቲከኛ : ንቃት ያገኘው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ግብር ከፍሎ ባስተማረው ትምህርት ነው:: ዛሬ በዲያስፖራ ተመችቶት የሚኖረው የተሰደደው በኢትዮጵያዊነት ስም መሆኑን የማይገነዘብ ካለ : የሰው ዶማ ነው:: ጥገኛ ሆነን በምንኖርበት ባእድ አገሮች : ኦሮሞ : አማራ : ትግራይ : ወላይታ ወዘተ ስለሆንን በጎሳ ስም ጥገኝነት አልተሰጠንም:: ጥገኞች የሆንነው በኢትዮጵያዊነታችን ነው:: በኢትዮጵያ አምባገነን መንግስታት ሰብዓዊ መብቶቻችን ስለተገፈፉና ሕይወታችን ለአደጋ ስለተጋለጠ በመሰደድ ሕይወታችንን ያተረፍን ሰዎች ሕዝባችንን በጎሳ ፖለቲካ ሰላም ስናሳጣ ከጠላናቸውና ከምንጠላቸው የኢትዮጵያ አምባገነኖች በምን እንሻላለን?
ኢትዮጵያውያን በአገራቸው ተጨናንቀው ባሉበት ወቅት እኛ በዲያስፖራ በምቾት የምንኖር የሕዝባችን መከራና ሰቆቃ ከመረዳት ይልቅ : በጎሳ ሕዝባችንን እየከፋፈልን ስናዋጋቸው ለምን ብለን ራሳችንን መጠየቅ ይገባናል:: የሚሞቱት እንደኛ ሰዎች ናቸው:: እንሰሶች እንኳን የትኛው ዘራቸው እንደሆነ ያውቃሉ:: እንዴት ሰዎች ዘራችን የሰው ዘር መሆኑ ተሰናነን? የትግላችን ትኩረት በጋርዮሽ መሆን ያለበት በአምባገነን ስርዓት ላይ እንጂ : ጎሳን ከጎሳ ማጋጨት መሆን የለበትም:: ሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ የተበደለው በየጊዜው እያስመሰሉና እያጭበረበሩ ስልጣን ላይ በሚወጡ አምባገነኖች ነው:: የአማራ ጎሳ : የኦሮሞ ጎሳ : የትግራይ ጎሳ : ወዘተ እርስ በርሱም ሆነ ሌላውን ጎሳ በድሎና ጎድቶ አያውቅም:: ለስልጣን ጥቅማቸው የጊዜው እምባገነኖች ጎሳዎችን ማባላትና ማፋጀት አንዱ ዘዴያቸው አድርገውታል:: እኛም የጎሳ ፖለቲካ አራማጅዎች በመሆን አምባገነኖችን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በመርዳት የተንኮላቸው ተባባሪ ሆነን እንገኛለን:: የመላው የኢትዮጵያ ጠላት እምባገነንነት መሆኑን እንገንዘበው::
ወደ ቅድመ ሃሳባችን ስናመራ : አምባገነንነት በአንድ ወይም በጥቂት መሪዎች ስብስብ ከጥቂት እስከ ምንም ገደብ በሌለው የመንግስት ስልጣን የሚመራ የመንግስት አይነት ነው። በዚህ ስርአት ሶስት አይነት አምባገነን መንግስታት አሉ። ወታደራዊ መኮንኖች የሚቆጣጠሩት ወታደራዊ አምባገነን መንግስት : አንድ ፖለቲካ ፓርቲ ፍፁም ተቆጣጣሪ ሆኖ የሚመራው አምባገነን መንግስትና አንድ ግለሰብ ቆራጭ ፈላጭ በመሆን እንደ ግል ሀብት የሚያስተዳድረው አምባገነን መንግስት ናቸው። የ”ዶ/ር” አብይ አህመድ መንግስትም ከተመረጠበት ጊዜ ጀምሮ የአምባገነንነትን ጠባይ ቀስ በቀስ እያሳየ ይገኛል:: የዶ/ር ማዕረጉን በቅንፍ ያስቀመጥኩበትን ምክንያት አንባብያን ሊጠየቁ ይችላሉ:: ለዚያም መልሴ አምባገነን የፈለገውን ማዕረግ ለራሱ ይቅርና የሱን ፍላጎት ለሚሟሉ ዕውቀተ አልባዎች እንደፈለገው መስጠት ይችላል:: የዚህም ትዝብት ምስክርነት በምርኮት ጊዜውን ላሳለፈ ወታደር ለብርሃኑ ጁላ የፊልድ ማርሻልነት ማዕረግ የሰጠ አምባገነን የዩኒቬርስትን አስተዳደር በማስፈራራት የሰውን ፅሁፍ በመገልበጥ ለምን የዶክቶሬት ድግሪ ለራሱ ማግኘት አይችልም? አምባገነን መሪዎች ስልጣን ላይ የሚቆዩት ማን ፈቅዶላቸው ነው? የአምባገነን መሪ ዋናው መታወቂያው የሕዝብን ፈቃድ ጠይቆ ሳይሆን ያለውን የአገሪቱን ጦር ኃይል እንደ ግል ደህንነት ጠባቂ በመቁጠር በወታደራዊ ጉልበት ስልጣን ላይ መቆናጠጥ ነው:: አምባገነን መሪዎች ስልጣን ላይ የሚቆዩት የማህበረሰብ ሂደቶችንና የአገር ሕዝብን የስነ-ልቦና ተለዋዋጭነትን ለጥቅማቸው በማዋል ነው::
ከጥንት የአመራር ስርዓቶች ሥረመሰረቶች ጀምሮ ፣ አምባገነኖች : በባላባትነት ሆነ : ጎሳዎችን በመምራት ፣ ሃይማኖቶችን ወይም ድርጅቶችን ሆነ : አገሮችን በመምራት ሁልጊዜ ሕዝብን በማጭበርበር ሕዝቦችን እንወክላለን በማለት ወታደራዊ ኃይልን በመጠቀም ሥልጣን ላይ ለመቆየት የማያደርጉት ሻጥር የለም:: እኛ ሕዝቦችም ጠንካራና ጎበዝ ወደ ሚመስሉን ግለሰቦች በመሳብ የችግራችን መፍትሔ ይሆናሉ ብለን በመገመት መሲህ እድርገናቸው እምነታችንን እንጥልባቸዋለን:: እነዚህ አምባገነኖች ይህንን የሕዝብ እምነት በመጠቀም ለሕዝብና ለሀገር ደህንነት ማስጠበቂያ በሚል መሰረት የጦር ኃይልን ለስልጣናቸው ማስጠበቂያ ያደርጉታል። ይህም ወታደራዊ ኃይል የሕዝብ አካል መሆኑን መገንዘብ ተስኖት ለሕዝብ መቆም ትቶ ሕዝቡን ሲገድልና ሲጨርስ በተለያዩ በአምባገንነ አስተዳደር የሚመሩ አገሮች ውስጥ ተደጋግሞ ታይቷል:: እየታዩም ናቸው:: ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ የሰፈነው የአብይ አህመድ አምባገነናዊ አስተዳደር ይህንን ብልሹ አካሄድ ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል::
ያለፈው ታላቅነት ይታደሳል በሚል የተሳሳተ እምነትና በምናባዊ የአገር መረጋጋትና ጥበቃ ስሜት አንዳንድ ሕዝቦች ነፃነታቸውን እሳልፈው እንዲሰጡ አምባገነኖች በቀላሉ ያሳምነዋቸዋል:: በጥቅሉ ሲታይ የማህበረሰብ አለመረጋጋት ጊዜዎች ለአምባገነኖች አመራር ላይ ለመውጣት ሁሌም አመቺዎች ናቸው:: የኢኮኖሚ ውድቀትና ድቀት : ፖለቲካዊ ወይም ማህበራዊ ትርምስ : አምባገነኖች እንደ አዳኝ (SAVIOR) እንዲታዩና ሁኔታዎች ሲፈቅዱ በመፈንቅለ መንግስት ወይም በሌላ መንገድ ስልጣን እንዲይዙ እድል ይሰጣቸዋል። የእነርሱ ህዝባዊ አራማጅነት የህዝቡን ሰፊ ክፍል ማታለያ ወጥመድ እንደሆነ ሁላችንም በደርግና በኢሐደግ አገዛዝ ዘመኖች ያየናቸው ናቸው:: አሁንም የአብይና የብልፅግና አስተዳደር ይህንን ሕዝብን ማጭበርበሪያ መንገድ በግልፅ እየተጠቀመበት መሆኑን ቀን በቀን በገሃድ እያሳየን ይገኛል::
ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የተጋነኑ ቃሎቻቸው ሕዝብን ለማስገረም ከሚባለው ባዶ አነጋገር አይበልጥም። ታዲያ ሥልጣንን እንዴት ማግኘትና ማቆየት ቻሉ ብለን ስንጠይቅ : መልሱ የታወቁ ማህበራዊ ሂደቶችንና ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን ሙሉ በሙሉ በመጠቀም የስልጣን ጥማታቸውን.ያሳካሉ ነው::
የሀገር ፍቅር : የፍትሕና የመልካም አስተዳደር ጩኸታቸው ህዝቡ መስማት የሚፈልጋቸው ናቸው። ይህን የሚያሳኩት የማረጋገጫ አድልዎን (CONFIRMATION BIAS) መረማመጃቸው በማድረግ ነው:፡ ቀድመው የሚያምኑበትን ለማረጋገጥና ሕዝቦች እንዲቀበሉ ለማድረግ የሕዝቦችን የማመንን ፍላጎት በማፋፋም ረገድ እጅግ በጣም ጎበዞች ናቸው።
ለዚህም የአምባገነን የሽንገላ ንግግር ያለምንም ጥርጣሬና ጥያቄ ተቀባይነትን የሚያገኘው በሰው ልጅ እጅግ በጣም በተስፋፋው የማረጋገጫ አድልዎ (CONFIRMATION BIAS) ላይ የተመሰረተ ስለሆነ ነው። ይህም ተቃራኒ መረጃዎችን ከቁጥር ሳናስገባ ሀሳባችንና ፍላጎታችንን የሚደግፍ ማስረጃ እንድንፈልግ ያስገድደናል። እንዲህ ዓይነቱ አድልዎ የዓለማችንን ውስብስብነት ቀላል ከማስመሰል በተጨማሪ ግብ ላይ ያላተኮረ የአስተሳሰብና የአመለካከት ስንኩልና መስሎ ሊታይ ይችላል:: አምባገነኖች በአስመሳይነት የተካኑ ስለሆኑ ይህንን ሁለንተናዊ የግንዛቤ አቋራጭ መንገድ ይጠቀማሉ።
አምባገነኖች በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ለችግር ተጋላጭ የሆነውን የማህበረሰብ ክፍል ኢላማ ማድረግ ላይ ጥሩ ችሎታ አላቸው:: ሁልጊዜ በደንብ ያልተማሩትን ወይም በቂ መረጃ የሌላቸውንና ብዙውን ጊዜ ግራ በመጋባት በራስ የመተማመን ስሜት የማይሰማቸውን በሚፈልጉት የማሳመን ወጥመድ ውስጥ ከተው ሕዝብ ደግፎናል በማለት ስልጣን ላይ መውጣት የአምባገነኖች ትልቁ ሻጥር ነው። አምባገነኖች የህዝብን ቁጣና ብስጭት እንደገደል ማሚቱ በማስተጋባት ከተጎዳው ጋር ቆመናል በሚል ስነ-ልቦናዊ ሂደት ይጠቀማሉ:: ጉልበት ወይም አቅም የለንም ብለው የሚያስቡ ብዙ ሰዎች በጠንካራ ወንድ ወይም ሴት ውስጥ የራሳቸውን ነፀብራቅና በደከመውና በወደቀው ሀገራቸው ላይ የድል ተስፋን ያያሉ። እነዚህም እኛ ችሎታም ሆነ አቅም የለንም ብለው የሚያስቡ ራሳቸውን አሳንሰውና ጥለው ተፈጥሮ የሰጣቸውን እምቅ ችሎታና ኃይል መገንዘብ ተስኗቸው በቅዠት የተሞላ አስተሳሰብ ውስጥ የተዘፈዘፉ ናቸው:: አእምሮአቸው የግል አስተሳሰብ እንዳይፈጥር አምባገነኖች በሚረጩት የማጭበርበር ዲስኩር ይበረዛል።
የአምባገነኖች ሌላው የስልጣን መውጫ እቅድ የወቀሳና የውንጀላ ጨዋታ ነው፡: የማህበረሰቡ ጥፋት ምንም ይሁን ምን አምባገነኖች ተወቃሽ የሚሆነውን ፈልጎ በዚያ ላይ ሕዝብን በመቀስቀስና በስህተት መወንጀል ላይ እጅግ የተካኑ ናቸው። ከፋፍለህ አጥቃ የሚለውን ጥንታዊ የማጥቂያና የመከላከያ ዘዴን በመጫወት ስልጣን ላይ ይወጣሉ:: ከዚያም ያንኑ የሻጥርና የተንኮል መንገድ በመጠቀም ስልጣን ላይ ለመቆየት ሹር ጉድ ይላሉ:: ጉዳዮችን በቡድን በመለየት በውስጥና በውጪ ጠላት አንፃር በማስቀመጥ የውስጥ ጠላት ተብሎ የተፈረጀው የውጭ ጠላት ወኪል ነው ተብሎ በመወንጀል የውጭ ስጋቶችን አጉልተው ሕዝባዊ ፍራቻ የተሞላበት ውዥንብር እንዲስፋፋ ያደርጋሉ። ዛሬ ኢትዮጵያን የሚመራው የአብይ አህመድ ብልፅግና እየሰራ ያለው ይህንኑ ነው:: ከዚህም በተለይ እጅግ እፍረት በሌለው መንገድ አምባገነኖች በስልጣን ላይ እንዲቆዩ የሚረዳቸው ሻጥራቸው የማይቋረጥ የእርስ በርስ ጥላቻ በዜጎች መሃል መፍጠር ነው:: የኦሮሞን ጎሳ በሌሎች ተጠልተሃል በማለት እያደናበሩት ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወንድሞቹ በመለየት ደጋፊው እንዲሆንና የአብይ እህመድን : የሽመልስ አብዲሳን : የአዳነች አበቤንና የኦሮማማን ፅንፈኞችን የስልጣን ጥማትን ማርኪያ መሳሪያ እያደረገው ይገኛል:: ትውልደ ኦሮሞ ያልሆነው የኢትዮጵያ ክፍል መጠንቀቅ ያለበት የኦሮሞን ሕዝብ በጎሳ ለይቶ በመውቀስና በመስደብ ለእምባገነኑ የኦዴድ ብልፅግና ፕሮፓጋንዳ መንገድ እንዳይከፍት ነው:: አብይና የኦዴድ ብልፅግና ስግብግቦችና የጥላቻ መርዝ እረጪዎች ሁለት ምላስ እንዳላቸው ደጋግመው አስመስክረዋል:: ይህም በኦሮምኛ ሲናገሩ መልክታቸው ኢትዮጵያን ለማሳደግ : አንድነቷን ለመጠበቅና ለማዳን ሳይሆን ኦሮሚያን የአፍሪቃ ትልቁ ኢኮኖሚና ሸገርን በኦሮሚያ የአፍሪቃ አንደኛ ከተማ ለማድረግ ያላቸውን ቅዠት በተደጋጋሚ አሰምተውናል:: በአማርኛ ሲናገሩ ኢትዮጵያውያን ነን:: ኢትዮጵያን ካለችበት ረመጥ (በድንቁርናቸውና በጎሰኝነታቸው ከከተቱበት) ውስጥ እናድናለን ነው::
እንደምታዩትና እንደምትሰሙት አምባገነኖች ራሳቸውን እንደ ፅኑ አገር አዳኝ (SAVIOR) አድርገው ያቀርባሉ። በቀላሉ ሲታይ ይህ ሻጥራቸው ሁለትዮሽ ሃሳቦች ያንፀባርቃል:: በአንድ በኩል እነሱ አገር አፍራሽ ናቸው ብለው ለሚያቀርቡት የውሸት ትረካ ተከታዮቻቸውን የመልካም ትግል አጋር ናችሁ በማለት ሲደልሉ ተቃዋሚ ናቸው ብለው የሚያስቧቸውን ሰዎች አለመታገስና ማጥፋትን ዋና ዓላማቸው ያደርጋሉ:: በአብይ አህመድ አምባገነናዊ አመራር ሂደት እነዚህን የከፋፍለህና የለያይተህ አመራርን አካሄዶች እናያለን:: በአንድ በኩል በጎሳና በፖለቲካ አመለካከት ላይ የተመሰረተ ድጋፍ በአጋሮቹ በኩል ሲያራምድ : በተመሳሳይ በጎሳና በፖለቲካ አመለካከት ጠላት ብሎ የፈረጃቸውን በጦርነት ሊያጠፋቸው እየሰራ ይገኛል::
አምባገነኖች በውሸት የማሳመን ጌቶች ናቸው፡: አምባገነኖች ሰዎችን የማሳመንን ዋጋና ጥቅም ጠልቀው መማር ለስልጣን መውጫ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ቀድመው በመረዳት ለዘመናት ይዘጋጁበታል:: በውሸት ዲስኩሩ ማሰራጫ እርዳታ የተነሳ አምባገነኖች የሁሉም ሰው ህይወት አጠቃላይ አካል ይሆናሉ:: ያለእነሱ ሕዝብም ሆነ አገር አይሻሻልም : አይራመድም:: ያለእነሱ በረከት ብልፅግናም ሆነ ሰላም አይገኝም የማለት እምነት አላቸው:: ይህንንም በአገራችን ኢትዮጵያ በተለይም አብይ አህመድ ዛሬ ላለበት የስልጣን መቆናጠጥ እንዴት እንደሚዘጋጅ እንደነበረ ደጋግሞ በነገረን ትረካና በየቀኑ በሚለፈልፈው ልንገነዘብ እንችላለለን:: የሚገርመው ነገር አምባገነኖች ምን ያህል በከንቱ ስሜት ውስጥ ተዘፍቀው እንዳሉ ያለመገንዘባቸው ነው::
አምባገነኖች የስልጣን ዘመናቸውን ለማቆየት፣ ሁሉንም ዋና ዋና ሚዲያዎችን ማዕከላዊ በማድረግ መረጃን ይቆጣጠራሉ። ይህንንም ሃቅ ዛሬ በኢትዮጵያ የሕዝብ ሚዲያዎች የሚባሉ የቴሌቪዥን : የሬዲዮና የፅሁፍ ሚዲያዎች እንዴት የብልፅግና የስልጣን ማራመጃ ልሳኖች እንደሆኑ በጋህድ እያየን እንገኛለን:: አወንታዊ ዜናዎች የአምባገነን ማድነቂያ ሲሆኑ አሉታዊ ዜናዎች የመንግስት ጠላቶችና አገር አጥፊዎች ተብለው የተፈረጁ አገር ወዳዶችና ዲሞክራሲ አራማጂዎች መገለጪያ ናቸው። የሚዲያ አውታሮቹ ብቻ ሳይሆኑ የሚዲያው ሰዎችና ጋዜጠኞች ገለልተኛ መሆን ትተው የአምባገነኑ አስተዳደር መሳሪያና አፈቀላጤዎች ሆነው ይገኛሉ:: ጥሩ ምሳሌ የምናደርገው እርግጠኛ ስሙን ማስታወስ የማልችለው የሕዝብ ሚዲያ የሆነው ሰራተኞች ለአዳነች አበቤ በቢሮዋ ሄደው አበባየሁሽ ማለታቸው ምን ያህል የአብይ አስተዳደር አምባገነንና አመስግኑኝ ባይ እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል::
ይህ መሪ የዛሬ 5 አመታት በዓለም እየዞረ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ በማለት ሁላችንም ስናልምና ስንመኝ የነበረውን ኢትዮጵያዊነትን ሲሸጥልን ከርሞ ከሶስት ዓመት በሗላ ወያኔን አገር አጥፊ ነው በማለት ጦርነት ጀምሮ : አገር እናድን በሚል ጥሪ ኢትዮጵያውያንን አማራውን ጨምሮ በማሰለፍ ወያኔን ካሸነፈ በሗላ : አማራን ለመውጋት የወሰደው እርምጃ አባርቆበት የአብይን አስተዳደርንና የብልፅግናን አምባገነንነትን አጋልጦ እያሳየ ይገኛል::
ሌላው አምባገነኖች በስልጣን ላይ በመቆየት የስልጣን ጥማታቸውን ማርኪያ መንገድ : በምርጫ ወቅት የፕሬስ ነፃነትን በመገደብ የተቃዋሚዎችን የምርጫ ቅስቀሳ አቅም በመገደብና የተሳሳቱ መረጃዎችን ማለትም የውሸት ዜና (FAKE NEWS) በማሰራጨት የመጨረሻውን ውጤት መቀልበስ ወይም እነሱ አሸናፊ ሆነው መታየት ነው:: አምባገነኖች ማህበራዊ ማዕቀፎችንና እንደ ተቃዋሚ ሃይሎች የሚያገለግሉ ተቋማትን ለመገደብ ወይም ለማጥፋት ይሞክራሉ። ይህንን የአምባገነን የስልጣን መቆያ እርምጃ በአገራችን በአብይ ዘመን ባናየውም : በሚቀጥለው ምርጫ ወቅት አይከሰትም ብዬ ለመገመት አልደፍርም:: ጊዜው ደርሶ የአብይ ብልፅግና መንግስት ይህንን ዓይነት እርምጃ ካልወሰደና ዲሞክራሲያዊ አሰራርን በገሃድ ካሳየን ቀደም ብዬ ስሙን ስላጎደፍኩ በሁሉም ሚዲያዎች ታላቅ ይቅርታ እጠይቀዋለሁ:: እሱ ዲሞክራሲንና የሕዝብን ፍላጎት አክብሮ ከጠበቀ እንደ ታማኝ በየነ እሱ ሳይለምነኝ: እኔ ለምኜው ለይቅርታው በአሮጊትነቴ እግሩ ላይ እወድቃለሁ::
አምባገነንነት የባህሪዎች ውጤት ነው:: የባህሪያቸው ቅንብር ለአምባገነንነት የሚያበቃቸው ሰዎች ይኖራሉ። ብዙ ያለፉትና የዘመኑ አምባገነኖች ባልተለመደ ሁኔታ ከፍተኛና ጤናማ ያልሆነ ራስን የማምለክ (NARCISSISM) ፍላጎት አለባቸው:: አንዳንዶንቹ ደግሞ በተጨማሪ በአእምሮ በሽታና (PSYCHOPATH) ሌሎችን ባለማመን በጥርጣሬ (PARANOIA) ተሞልተው ይሰቃያሉ። ለራሳቸው ከፍ ያለ ግምት ስለአላቸው የሌሎችን አድናቆት የማግኘት መብት ይሰማቸዋል:: ለዚህም የሌላቸውን ችሎታና ዕውቀት አለን : ያልተማሩትን ተምረናል በማለት የሌላቸውን የትምህርት ደረጃ ውሸት በተሞላበት ምስክር ወረቀቶችና ዲግሪዎች ሊያስመሰክሩ ይሞክራሉ:: በራሳችን አገር መሪ በአብይ አህመድ ሰሞኑን በተነሳበት የትምህርት ደረጃው ጥያቄ ይህን ራስን የመካብ ዝንባሌ ማየት ችለናል:: ይህ በውሸት ራስን ከፍ ከፍ ማድረግ የአምባገነኖች ባህሪይ እንደሆነ ያሳሳስበናል::
በሰብዓዊነት መነፅር ስናይ : አምባገነኖች ግፈኞችና ጨቃኞች ለመሆናቸው ምንም አያጠራጥርም:: የሰው ሕይወት መጥፋት የማያሳዝናቸውና የማይቆረቁራቸው ናቸው:: የርኅራኄ ማጣት የጥፋተኝነት ወይም የፀፀት እጦታቸው እጅግ በጣም ተንኮለኛና ሊነገር የማይችል ግፍ እንዲፈፅሙ ያስችላቸዋል። ይህንን አስከፊ አረመኔነት በመንግስቱ ኃይለማርያም አመራር በተለይ በቀይ ሽብር ወቅት በአገር ቤት ውስጥ የነበሩት ፀረ-ደርጎች ያስታውሳሉ:: ዛሬም የአብይ አህመድ መንግስት በጦርነት ሰበብ የሚፈፅመውን የሕዝብ ፍጅትን አግባባዊ ነው የሚል ድምዳሜ ላይ የደረሰ ይመስላል:: በእርግጥም አብይ አህመድ ለሰው ሕይወት ርህራሄ ቢኖረውና ቢሰማው ኖሮ በአማራ ሕዝብ ላይ ያወጀውን ጦርነት “አንድ መቶ ሺህ ሰዎች አስጨርሰንም ቢሆን ጦርነቱን እናሸንፋልን” ባላለ ነበር:: ታድያ ለአምባገነኖች ተጠያቂው ማነው?
ምንም እንኳን አምባገነኖችን ስማቸውን ማጉደፍና መሳደብ ቀላል ቢሆንም፣ በብዙ መልኩ ወደንም ሆነ ተገደን ድርጊታቸውን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በመደገፍ እኛው ሕዝቡ ራሳችን ግፋቸውን እንዲፈፅሙ ያስቻልናቸው መሆናችንን ልንገነዘብ ይገባል። ለነገሩ አምባገነኖች ያለ ተከታዮች ሊኖሩ : ሊሰሩና ሊጠናከሩ አይችሉም። ጮክ ብለን ባንቀበልም ሌሎች ሰዎች ትክክልና ስህተት የሆነውን እንዲነግሩን ማድረጉ ይማርከናል። ነገር ግን የግል ሃላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት ሀሳብን በነፃነት ለመግለፅ ያለንን ችሎታና የዴሞክራሲ ሂደቶችን ያሰናክላል። ማወቅ ያለብን መልካሙ ዜና ግን አምባገነኖችን በድጋፋችን እንዲቆሙ እንደምናስችላቸው ሁሉ : ግፋቸው ሲበዛ እነሱን አሰናክለናቸው የመጣል ችሎታ እንዳለን እንደ ሕዝብ መገንዘቡ ነው። ይህም ሊከናወን የሚቻለው የአገርን ሕዝብ መብታቸውንና ግዴታቸውን ተረድተው የተቀበሉ ኃላፊነት የሚሰማቸው መራጮች ስናድርግ ብቻ ነው::
በብዙ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታን በአቋቋሙ አገሮች የአምባገነንነት ማንሰራራት የምር ሥጋት እየሆነባቸው ነው። ይህም ሥጋት ሁለት አስቸኳይ ጥያቄዎችን እያስነሳ ነው:: በሂደት ላይ ያሉ አምባገነኖች ሊፈወሱ ይችላሉ? አምባገነኖች ስልጣን እንዳይይዙ ማድረግ እንችላለን? ለመጀመሪያው ጥያቄ የሚሰጠው ምላሽ “አይሆንም” የሚል ስጋት አለኝ:: የታሪክ ልምዶችም ደጋግመው ይህንን አረጋግጠውልናል። ከክሊኒካዊ እይታ አንፃር ስንቃኘውም : አብዛኞቹ የሥነ ልቦና ባለሙያዎች አምባገነኖች (በሥነ ልቦና ባህሪያቸው) ሊታከሙ እንደማይችሉ ያምናሉ። ስለዚህ ወደ ስልጣን እንዳይወጡ እንዴት መከላከል እንደሚቻል ሁለተኛውን ጥያቄ ለመፍታት ብዙ ተቃዋሚ ኃይሎች ያስፈልጋሉ።
ለማዳን ከመሮጥ አስቀድሞ መከላከል ይሻላል እንደሚለው: አምባገነኖች ስልጣን ይዘው ሕይወታችንን ከማበላሸታቸውና ከማጥፋታችው በፊት የአባምገነንነት እምቅ ኃይላቸውንና ባህሪያቸውን ተረድተንና ተገንዝበን በመገኘት ለዲሞክራሲ ዘበኝነት መቆም ይኖርብናል:: አንዴ ስልጣን ከያዙ ከዚያ በሗላ ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥሱ ይተረትብናል። ይህንንም አቢይ አህመድና ብልፅግና ፓርቲ በማያዳግም ሁኔታ እያስተማረን ይገኛል:: የእምባገነንነት እምቅ ኃይሉንና ባህሪውን በሚገባ ደብቆ መጥቶ አታሎናል:: የተለያዩ አመለካከቶችን የሚያዳምጥና አሻሚ ጉዳዮችን በሚገባ ይዞ መቆጣጠር የሚችል ሕዝብ ውስጥ ጤናማ ዲሞክራሲ ቦታ ይኖረዋል:: እንዲሁም ምርጫ የእኔ ግዴታ ሳይሆን የሌሎች ጉዳይ ብሎ የሚያምነውን ሳይሆን ዕውቀት ያለውን: የተሰባሰበንና የተረዳውን መራጭ ሕዝብ ይመለከታል:: አምባገነኖች ወደ ፊት ስልጣን እንዳይዙ ለመከላከል ለነፃነት የሚቆረቆርና ለነፃነት ኃላፊነት የሚወስድ ህዝብ ይጠይቃል።
በተጨማሪም መንግሥት : ርዕሰ መስተዳድሩ : ሕግ አውጪው አካል : ፍርድ ቤቶች : የዜና ማሰራጫዎችን መራጮች ነፃ ሆነው ዲሞክራሲ እንዲያድግና እንዲያብብ አፀፋዊ ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው።
ታዲያስ እንዴት ለተሻለ ዓለም እንታገል ብለን ስንጠይቅ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በሗላ እንደ እውሮፓውያን እቆጣጠር በ1940 የተሰራውን የቻርሊ ቻፕሊንን ፊልም እንድናስታውስ ያደርገናል::
በ 1940 The Great Dictator በተባለው ፊልም ላይ ቻርሊ ቻፕሊን አይሁዳዊ ፀጉር አስተካካይ ሆኖ በመጫወት ላይ እያለ የተሳሳተ ማንነት ባለው ሁኔታ የልበወለዳዊ ቶማይኒያን አገር ፈላጭ ቆራጭ ገዥ በመምሰል ተገዶ ናዚዝምንና (NAZISM) አዶልፍ ሂትለርን በምፀት አቅርቧቸዋል::
በፊልሙ መገባደጃ ላይ ቻፕሊን ህዝቡ ተባብሮ አምባገነንነትን እንዲታገል ንግግር ይሰጣል፡: “እናንተ : ህዝቦች : ይህንን ህይወት ነፃና ውብ ለማድረግ ኃይል አላችሁ:: ህይወትን አስደናቂ ትንግርት ለማድረግ : በዲሞክራሲ ስም ያለንን ኃይል እንጠቀም:: ሁላችንም በአንድነት እንሰለፍ:: አምባገነኖች ራሳቸውን ነፃ አውጥተው ህዝብን በባርነት ይገዛሉ። ዓለምን ነፃ ለማውጣት፣ ብሔራዊ መሰናክሎችን ለማስወገድ : ስግብግብነትን : ጥላቻንና አለመቻቻልን ለማስወገድ እንታገል።”
እንደ አለመታደል ሆኖ፣ እኛ ቻፕሊን ከገለፀው ዓለም ርቀን እንገኛለን። ብዙዎቹ የአሁን የዓለም መሪዎቻችን የዲሞክራሲ ሂደቶችን አደጋ ላይ ለመጣል ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ናቸው። ጠባብ ብሔርተኝነት : የውጭ ዜጋ ጥላቻ : ስግብግብነትና የማይታሰብ ጥቃት በየቦታው ይታያሉ። ይህም ዛሬ በዓለማችንና በኢትዮጵያ አገራችን ያሉት ሰው በላሽ አምባገነናዊ ስርዓቶች በቻፕሊን የታሰበውን ዓይነት ዓለም ለማግኘት መጣርን የበለጠ ወቅታዊ ያደርገዋል።
አሳልፈን የሰጠነውን ነፃነት ከራሳችን በስተቀር ማንም አያስመልስልንም:: ለደህንነት ተብሎ ነፃነትን አሳልፎ የሰጠ ደህንነትም ሆነ ነፃነት አይገባውም:: ከሕዝብ የተጣላ አምባገነን : ሕዝብን ይገላል እንጂ አያሸንፍም:: ድል ምንጊዜም የሕዝብ ነው::
_
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
በራየ ብዕሩ
ከደጃች ውቤ ሰፈር
ሙሉውን ጽሁፍ በፒ ዲ ኤፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
__
በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com
የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
በሊጋባው
የጽሁፉ አላማ
የዚህ ፅሁፍ አላማ በአማራ ህዝብ ላይ ከዛሬ አራት አስርት አመታት ጀመሮ እየተካሄደ ያለውን የአማራን ዘር ከምድረ ገጽ የማጥፋት መንግስት መራሽ እና ሕጋዊ የሚመስል ሁሉን አቀፍ ዘመቻ እንዲሁም ከ 16ተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበሩትን አማራን የማጥፋት እና መሬቱን የመውረር እንቅስቃሴ እንድሚረዳ አማራ ለአዲሱ ትውልድ የትግል አቅጣጭን ለማሳየት ነው። አሁን ባለው ነባራዊ የአማራ ብሔርተኝት እንቅስቃሴ ተሳታፊ እየሆነ
ያለው አዲሱ የአማራ ትውልድ የሚሄድበትን መንገድ ለማዛባት እና ብሔርተኝነቱን ለማደብዘዝ ከፍተኛ የሆነ እንቅስቃሴ እየተደረገ ስለሆነ ወጣቱ ትግሉ እንዳይጠለፍ እንዲሰራ እና ትግሉ በህልም አለም በሚኖሩ ሰዎች እንዳይጠለፍ ለማሳሰብም ጭምር ነው።
በዚህ ፅሁፍ ዉስጥ ስማቸውን ልጠራቸው የምችላቸው ግለሰቦችም ሆነ ቡድኖች ወይም ተቋማት አሉ። እነዚህን ተቋማት ወይም ግለሰቦች የማነሳበት እና ገንቢ ሂስ የምሰጠው በሚከተሉት 6 ምክንያቶች ነው።
● እንደ አንድ አማራ በአማራ ስም የሚካሄድ ትግል እና የፖለቲካ እንቅስቃሴ ስለሚመለከተኝ።
● የአማራ ህዝብ የሚመራው እና የሚያታግለው ድርጅት በሚሻበት ሰአት፣ የአማራን ሞትና መፈናቀል
ለማስቆም ዘለቄታዊ መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ ሞታችንን እና በደላችንን እንደመቆስቆሻ በመጠቀም
በምእናባችው ዉስጥ ብቻ የሚኖርን ቅዠት እንዲያድን የአማራን ወጣት ለመጠቀም የሚታይ ትግል
የመጥለፍ እንቅስቃሴ ስላለ።
● የአማራ ህዝብ በመዋጮ ያቋቋማቸው ድርጅቶች ለአማራ ህዝብ ዘላቂ መፍትሄ ከማምጣት ይልቅ ጠላት
ማፍራት በተካኑ አካላት እጅ ስለተጠመዘዙ።
● የአማራ ህዝብ መደራጃ ምሰሶ የሆነን አማራዊ ጎሰኝነት የሚጸየፉ ሰዎች ትግሉን ሊመሩ ስለመጡ።
● የአማራን መሞት እና መፈናቀል እንዲሁም የዘር ፍጅት በቻሉት አቅም ማሳወቅ ወይም (advocate)
በማድረግ የተሳካልቸው አካላት፣ ይህንን ስኬታቸውን የአማራን ፖለቲካ ለማቡካት እንደ ፍቃድ
መጠቀማቸው እና የአማራን ፖለቲካ በተሳሳተ መንገድ እየቀረፁ ስለሆነ።
● በደርግ ጊዜ ያልተሳካላቸውን “ኢትዮጵያን ማዳን” ያልቻሉ አካላት የአዲሱን የአማራ ትውልድ ደም
ለማይሳካ ትግል ለመማገድ ስላሰፈሰፉ።
ማህበራዊ መስተጋብር ( Social fabric )
ሙሉውን በፒ ዲ ኤፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
__
በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com
የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
ቦርከና
ብልጽግና መራሹ የኢትዮጵያ መንግስት ፋኖን ትጥቅ ለማስፈታት በሚል በአማራ ክልል በከፈተው መጠነ ሰፊ ጦርነት ሳቢያ በመቶዎች የሚቆጠሩ ንጹሃን ዜጎች በግፍ እንደተገደሉ በርካታ መንግስታዊ ያልሆኑ የሃገር ውስጥ ሚዲያዎች የዘገቡበት ጉዳይ ነው፡፡
ትላንት የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ትላንት ያወጣው መግለጫም በአመዛኙ በተለይ በነሃሴ ወር የተፈጸሙትን ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች የሚያረጋግጥ ነው፡፡
የመግለጫው ከታች እንደሚከተለው ቀርቧል : –
“አማራ ክልል:- ከትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ አሳሳቢነታቸው የቀጠለ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከሚያዝያ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በአማራ ክልል የሚታየው የጸጥታ ችግር በተለይ ከነሐሴ ወር 2015 ዓ.ም. ወዲህ ተስፋፍቶ ወደ ትጥቅ ግጭት ማምራቱን ተከትሎ፣ አጠቃላይ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታዎችን በቅርበት መከታተሉን ቀጥሏል፡፡
ግጭቱና የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች እርምጃዎች የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ በተለይም በሲቪል ሰዎች ላይ እያደረሰ ያለውንና ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት አስመልክቶ በነሐሴ 8 ቀን 2015 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፤ ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሔ ማፈላለግን ጨምሮ በሲቪል ሰዎች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል አፋጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ ማሳሰቡ የሚታወስ ነው። በተጨማሪም ከሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ሥራ ላይ የዋለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሰብአዊ መብቶች ላይ ያለውን ተጽእኖ በመከታተል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጠቅላይ መምሪያ ዕዝ እና የአዋጁ መርማሪ ቦርድን ጨምሮ የሚመለከታቸውን የመንግሥትና የጸጥታ አካላትን በማነጋገርና ምክረ ሐሳቦች በመስጠት በቅርበት ክትትል በማድረግ ላይ ይገኛል።
ኮሚሽኑ ይህን መግለጫ ይፋ እስከአደረገበት ጊዜ ድረስ ባደረገው ክትትል መሠረት፤ በሲቪል ሰዎች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶች፣ ከሕግ/ፍርድ ውጭ የተፈጸሙ ግድያዎች እና የዘፈቀደ እስር እጅግ አሳሳቢ ሆነው ከተለዩ ጉዳዮች መካከል ናቸው፡፡
በተለይም በአማራ ክልል ኮሚሽኑ ከነዋሪዎች፣ ከተጎጂዎች፣ ከተጎጂ ቤተሰቦችና ከዐይን ምስክሮች ባሰባሰባቸው መረጃዎች መሠረት የትጥቅ ግጭቱ ወደ ክልሉ ልዩ ልዩ ወረዳዎች መስፋፋቱን ተረድቷል፤ በነዋሪዎች ላይ የሚያደርሰው ጉዳትም ተባብሶ ቀጥሏል። ለምሳሌ ከነሐሴ 19 እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ በተለይም በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ፣ በሰሜን ጎጃም ዞን አዴትና መራዊ፣ በደቡብ ጎንደር ዞን ደብረታቦር፣ በማእከላዊ ጎንደር ዞን ደልጊ፣ በሰሜን ሸዋ ዞን ማጀቴ፣ ሸዋ ሮቢት እና አንጾኪያ ከተሞች እና በአካባቢዎቻቸው በሚገኙ አንዳንድ የገጠር ቀበሌዎች በግጭቱ ዐውድ በርካታ ሲቪል ሰዎች መሞታቸውን፣ ለአካል ጉዳት መዳረጋቸውን እና የንብረት ውድመት እንደደረሰባቸው ለመረዳት ተችሏል። በተኩስ ልውውጦች ወይም በከባድ መሣሪያ ተኩስ ከሚሞቱ ሰዎች መካከል በመንገድና በእርሻ ሥራ ላይ እንዲሁም በቤታቸው ውስጥ የነበሩ ሰዎች ጭምር የሚገኙ መሆኑን ቤተሰቦች እና የዐይን ምስክሮች ያስረዳሉ።
በዚሁ የግጭቱ ዐውድ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች በመንግሥት የጸጥታ አካላት ከሕግ/ፍርድ ውጭ የተፈጸሙ ግድያዎች (extrajudicial killings) እጅግ አሳሳቢ ነው። ለምሳሌ ከሐምሌ 24 እስከ ጳጉሜን 4 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ በተለይም በአዴት፣ ደብረማረቆስ፣ በደብረ ታቦር፣ ጅጋ፣ ለሚ፣ ማጀቴ፣ መራዊ፣ መርጦ ለማርያምና ሸዋ ሮቢት ከተሞች ተስፋፍተው በተፈጸሙ ከሕግ/ፍርድ ውጪ የሆኑ ግድያዎች ሰለባ ከሆኑ ሰዎች መካከል ቤት ለቤት በተደረገ ፍተሻ የተያዙ ሰዎች፣ በግጭቱ ወቅት መንገድ ላይ የተገኙ እና ያልታጠቁ ሰዎች፣ “የጦር መሣሪያ ደብቃችኋል አምጡ” በሚል የተያዙ ሰዎች፣ የሰዓት እላፊ ገደቦችን ተላልፈው የተገኙ ሲቪል ሰዎችና በቁጥጥር ስር የዋሉ የታጣቂው ቡድን (በተለምዶ ፋኖ በመባል የሚታወቀው) አባላት የሚገኙበት ሲሆን፤ በኮሚሽኑ እና በአስቸኳይ ጊዜ መርማሪ ቦርዱ አማካኝነት የተሟላ ምርመራ ሊደረግበት የሚያስፈልግ ነው፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የአስቸኳይ ጊዜ መምሪያ ኮማንድ ፖስት በይፋ ካሳወቃቸው እስሮችና ቦታዎች ውጪ በተለይ በአማራ ክልል፣ በኦሮሚያ ክልል እና በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች በአስቸኳይ ጊዜ ዐውዱ የተስፋፋና የዘፈቀደ እስር የተፈጸመ ሲሆን፣ ለምሳሌ በአማራ ክልል በባሕር ዳር፣ ደብረ ታቦር፣ ደብረ ማርቆስ፣ ፍኖተ ሰላም፣ ጎንደር፣ ላሊበላ፣ መካነሰላም፣ ቆቦ እና ሸዋ ሮቢት ከተሞች፤ በኦሮሚያ ክልል በተለይ በሸገር ከተማ እና በአዲስ አበባ ከተማ የተፈጸሙ የዘፈቀደ እስሮች ይገኙበታል፡፡ ከእነዚህ ታሳሪዎች ውስጥ በደቡብ ክልል ፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጅ ግቢ (በተለምዶ አቦስቶ በመባል የሚታወቀው ቦታ) የነበሩ ታሳሪዎችን ጨምሮ ከተለያየ ጊዜ መጠን በኋላ የተለቀቁ መኖራቸውን ማወቅ የተቻለ ቢሆንም፤ በአንጻሩ ገና ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቀ ሰዎች ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ በእስር ላይ ይገኛሉ። በመንግሥት የጸጥታ አካላት የሚታሰሩ ሰዎች በአብዛኛው “ለታጣቂ ቡድኑ ድጋፍ ታደርጋላችሁ” እና/ወይም “የጦር መሣሪያ ደብቃችኋል” በሚል ምክንያት ነው፡፡
በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ገላን ክፍለ ከተማ ውስጥ ሲዳ አዋሽ ወረዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘው ጊዜያዊ ማቆያ ማእከልን በተመለከተ በዚህ ማእከል ውስጥ ተይዘው የነበሩ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በፊትና በኋላም ከተለያዩ ክልሎች የመጡ ሕፃናትና ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ውሏቸውን ጎዳና ላይ ያደረጉ ነዋሪዎች ከጎዳና ላይ ተነስተው እንዲቆዩ የሚደረግበት ቦታ መሆኑን፣ በቅርቡ ወደ ማእከሉ ከተወሰዱት ውስጥ 29 ሰዎች በመታወቂያ ካርዳቸው ተለይተው እንዲለቀቁ መደረጉን፣ የተወሰኑት ደግሞ በመልሶ ማቋቋም ፕሮግራም ወደየመጡበት አካባቢዎች እንዲመለሱ የተደረገ መሆኑን፣ በጣቢያው ውስጥ ተከስቶ የነበረው ተላላፊ በሽታ በቁጥጥር ስር የዋለ መሆኑን ኮሚሽኑ በክትትሉ ተመልክቷል። እንዲሁም የጎዳና ላይ ተዳዳሪዎችን በተለይም ሕፃናትን በተመለከተ በችግሩ ዘላቂ መፍትሔ ላይ ከዚህ በፊትም ኮሚሽኑ ያቀረባቸውን ምክረ ሐሳቦች አፈጻጸም ክትትሉን ይቀጥላል፡፡
በኮማንድ ፖስቱ ትእዛዝ በእስር ላይ መሆናቸው ከሚታወቁት ሰዎችና ቦታዎች ውስጥ ኮሚሽኑ በአዋሽ አርባ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር የምዕራብ ዕዝ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ውስጥ ተይዘው የሚገኙትን ታሳሪዎች ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. መጎብኘቱና ማሳወቁ የሚታወስ ሲሆን፤ በሌሎቹም ቦታዎች ተመሳሳይ ክትትል ያደርጋል።
ስለሆነም ኢሰመኮ ከዚህ በፊትም ባቀረበው ጥሪ እንደገለጸው ግጭቱን በዘላቂነት ለመፍታት ላሉት ሰላማዊ አማራጮች በሙሉ ቅድሚያ መስጠትን ጨምሮ፤
_
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
1። የሸኔ እና የብልጽግና የአምስት ዓመታት ጉዞ፤ ለፋኖ መነሳት ገፊ ምክንያት
በእያደር ባሰ ( ከታዘብኩት)
ሀ፡ መንግስትነት ምንድን ነው? ሽፍታስነትስ ወይም ነጻ አውጪነት?
በሌላው ዓለም መንግስት የህዝብ ሰላምን ሊጠብቅ፤ ሊያስጠብቅ በህዝብ አደራ የሚቀበል ሀይል ነው፡፡ መንግስት የማህበረሰብ ጉልበት እና አሌንታ ነው፡፡ በግለሰብ ደረጃ ሊሟላ የማይችሉ ፍላጎቶች ( የሰላም እና የደንነትን የጨምራል) በመንግስት ጉልብት መሟላት አለባቸው፡፡ ሰላም የማስከበር ጉዳይ ወይም የፖሊስነት ጉዳይ መንግስት ከሚያስፈልግበት ዋነኛ ምክንያቶች ግንባር ቀደም ነው፡፡ የሆነው ሆኖ በአሁኒቱ ኢትዮጵያ የሰላም ጉዳይ ከመንግስት ሀላፊንተ አንጻር እጅግ አሳሳቢ ነው፡፡ ባንድ በኩል የለየለት ጦርነት ከትህነግ ጋር ተደርጎ በሰላም ደርድር ትቋጨ ተብሎ ሳይረጋ ኡሁን ደግሞ ከፋኖ ጋር ግብግብ ተይዧል፡፡ በሌላ በኩል በኦሮሚያ ‘ሸኔ’ በሚል የዳቦ ስም የሚጠራ ‘የጠራ የፖለቲካ ግብ የሌላው’ ቡድን መጠነ ሰፊ የግደያ እና የዘረፋ ዘመቻ ላይ ነው፡፡ ዘመቻው በዋነኝነት አማራ በማለት የሚጠሩት፤ ተዋልዶ እና ተቀላቅሎ በሚኖረው ግለሰብ እና ማህበረሰብ ላይ ነው፡፡ ዝምድና የማይገባው ከሀዲ ሰቆቃውን ይመራል እንዲሁም የፖለቲካ ግብ ሊሰጠው ይማስናል፡፡
ይህ የፕለቲካ እና የዘረፋ ቡድን መንግስታዊ ሥሥ ልብ እንዲሁም የጥቅም ሸርክና አግዞት እንደፈለገ ይናኛል፡፡ በአንድ በኩል በመንግስት ውስጥ ያሉ ቆራጦች እና የህዝብ አደራ እና ውክልና ሸክም የሚግባቸው የሚያረጉትን ትግል መና በማስቀረት ብሎም የሚላኩ የጸጥታ አካላትን የጭዳ በግ በማስደርግ በመንግስት የሚያሴሩብትን የመንግስት አካላትን መሪ ተብዬዎቹ መለየት አልቻሉም ወይም አልፈለጉም፡፡ ውጤቱ ኦሮሚያ ውስጥ ታማኝ የህዝብ አገልጋዮችን ተስፋ እያስቆሪጠ ነው፡፡ ወይም ተስፋ ቆርጠዋል፡፡ በሎም የአማራ ከልል ፋኖ መንግስትን እንዲታግል በር ከፍቷል በሎም ዋና ገፊ ምክያት ሆኗል፤ ትግሉም ተጀምሯል፡፡
ሆኖም የግድያ እና የዘረፋ ተጠቂዎች በዋነኝነት አማራ ይባሉ እንጂ ሁሉም ጥረው ግረው ትንሽ ጥሪት ያላቸው ፣የሚሰሩ እጆች እና የሚያስቡ አዕምሮ ባለቤቶች ናቸው፡፡ በዘራፊዎች ኦሮሞ የሚባሉትም ጭምር ጥቃቱ አይቅርላቸውም፡፡ ንብረት ካለው ኦሮሞም ቢሆን፤ በነሱ መስፍርት ማለቴ ነው አያምልጥም፡፡ ማምለጥ የሚችለው በመፈርጠጥ ነው፡፡ አሸዋ ሜዳ የተከማቸው ማህበረሰብ ከወለጋ እና ም/ ሸዋ የተሰደደ ነው፡፡ ቀማኛውም ወደ ሸገር ይሸሻል፤ ከተማዋ መደበቂያ ዋሻ ሆናለች፡፡ የመጨረሻው የጦር ሜዳ እንደምትሆን ግን እሙን፡፡ የጀመረም ይመሰላል፡፡
ለ፡ ታዲያ መንግስት ምን ያርግ ወይም ምን ሊያረግ ይችላል?
1ለ፡ መንግስት እንደ ተጠቂ?
መንግስት እንደ ተጠቂ ሲተውን እንደማየት የሚያም ነገር የለም፡፡ መንግስት ወይ ስራውን መስራት ወይም አልችልም ብሎ ካቢኔውን አፍርሶ መሰናበት አለበት፡፡ እንደ ተጠቂ እና ምን ላርግ? በሎ ሲብስም በዜጎች ዳተኝነት ላይ ማሳበብ መንግስታው ሀላፊነትን መሸሽ ወይም ድርብ እና የሚጋጩ ግብ ይዞ መዳከርን የሚያመልክት ነው፡፡ በሌላ ጎኑ ደግሞ ጀገና ሆኖ ለመታየትበአማራ ክልል ሲዳክር ይታያል፡፡
2ለ፡ ኦሮሚያ?
ኦሮሚያ የሚሰሩ እጆች እና የሚወጥን ልቦና የሚኮላሽብት ምድር ሆናልች፡፡ ባለንብረት ሁሉ ከተሰደደ ወይም ከተገደል የቀረው ማህብረስብ እጣፈንታው ምን ሊሆን ይችላል? ጥቃቅን ነጋዴዎች፣ መምህራን፣ ገበሬዎች፣ የመንግስት ሰራተኛ ሳይቀሩ እየታፈኑ ገንዘብ በመቶ ሺዎች ይጠየቃል፤ ከተከፈለ በኋል መርዶ ወይም ፈጣሪ ከረዳ በዱላ የላቆጦ እና ቅስሙ የተሰበረ ግለሰብ ይመላሳል፡፡ በአንዳንድ አከባቢ ደሞ መሉ ወረራ ይካሄድና ጅምላ ግድያ ይፈጸማል፤ ቀሪው ማህበረሰብ ስደት ይሆናል፡፡
3ለ፡ የኦሮሚያ መንግስት ምርጫ?
በገዳይ አስገዳይ ቡድን “ኦሮሞ አይደሉም” የተባሉትን አቶ መልስ ዜናዊ ‘ኤርትራዊያን” ላሏቸውን የወቅቱ ዜጎች የሰጧችውን “ክብር እና ምርጫ” መስጥት እንዲችል ፈጣሪን መለመን ብቻ ነው የሚቻለው፡፡ ወይም የፋኖን ትግል ዳር ማድረስ? በፌደራል መንግስት በኩል ምንም ተስፋ ያለ አይመስልም፡፡ ሊኖርም አይችልም፡፡ ድንበሩም ግልጽ አይደለም፡፡ በዚህ እሳቤ አንድ ግለሰብ ኦሮሞ ለመሆን ምን ያህል የደም ‘ጥራት’ እንደሚያስፍልግ የአሜሪካን ልምድ ቢጠቀሙ መልካም ይመስለኛል፡፡ አሜሪካ በነጭ አክራርሪ ዘረኞ መዳፍ በነበረች ጊዜ፤ 95% ነጭ መሆን ጥቁር ከመባል አያስጥልም ነበር፡፡ ባሪያነት ንግድ ስለነበረ የጥቁሩ ቁጥር መብዛት ይፈለግም ነበር፡፡ በኦሮሚያ አማራን፣ ሌሎች ጎሳዎችን፣ በተለይ “ቅይጥ እና የደም ጥራት” ( በሽመልስ አብዲሳ ትርጉም ሰጪነት) ችግር ያለበትን በአፋጣኝ መዝግቦ እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል፡፡ የፌደራል መንግስት ደሞ አማራ ክልልን እና ሌሎች “ደጋግ” ክልሎችን በማሳማን የአዲስ ሰፋራ ስራ መስራት ያስፈልጋል፡፡ የዓለም መንግስታትን እርዳታም በመጠየቅ፤ ሰው የሚፈልጉ አገራት ከተገኙ መስጠትም ጥሩ አማራጭ ነው፡፡ ውጤቱ የደም ጥራቱ የተጥበቀ የኦሮሚያ ምድር ለሸመልስ እና አብይ ( በሎም ለኦኔጋዊያን) ኦሮሞዎች ይኖራል፡፡ እንዲሁም የራሱ የኦሮሞም መዘረፍ ሰበብ ያጣል፡፡ ሰላም ይወለድ ይሆናል፡፡ ምን ትላላችሁ ጎበዝ?
የሆነው ሆኖ፤ የአማራ ሀዝብ የቆረጠ የምስላል፡፡ ጀገና ልጆች የባት፤ ያአያቶቻቸውን መንገድ ጀምረዋል፡፡ ፋኖ ተነስቷል፤ መነሻዬ አማራ መዳረሻዬ ኢትዮጲያ ብሎ ግብ አስቀምጧል፡፤ ብሶት የወለደው ወጣት ዱር ቤቴ ካለ ሰነባብቷል፡፡ ድልም እየቀናው፤ ማህበረሰባዊ መሰረቱን እያሰፋ ነው፡፡ በተለይ የመንግስት ተበዬው ውንብድና እስከቀጠለ ድረስ ይፍጠንም ያዝግምም ፋኖ ማሸነፉ አይቀሬ ነው፤ ታሪክም የግፏንን የመጨረሻ አሸናፊነት ሲዘክር ነው የሆኖረው፡፡
__
በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com
የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
በራየ ብዕሩ ከደጃች ውቤ ሰፈር
የማህበረሰብ ምህንድስና ጠበብት የሆነው ፈረንሳዊው ኤሚል ዳርካይም (on suicide) በተሰኘው የምርምር መድብሉ ላይ በጥልቅ የተመራመረው ነገር ቢኖር ግለሰብ እና ማህበረሰብ በሚለው ርዕስ ሥር የማህበራዊ ትስስር መላላት እንዴት ግለሰብን ብሎም ማህበረሰብን የመበጣጠስ እና የመበታተን አቅሙ ሃያል እንደሆነ በጥልቅ አሳይቷል። ሰው በግሉ ወይንም ማህበረሰብ በጋራ ለከፍተኛ ቀውስ ይጋለጣል፤ ይሄ የዳርካይም ንግግር በተለይ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ለቀባሪው ማርዳት ነው የሚሆንብን፤ የህብረተሰብ ትስሰር ሃያል የሆነባቸው አገራት ውስጥ ግለሰብ የራሱ ተነሳሽነት ብሎም የህብረተሰብን የጋራ በጎ ብልጽግናን ይከተላሉ፤ እራሳቸውንም ሆነ ህብረተሰብን የሚጎዳ ነገር አያደርጉም፤ ይህንንም ዳርከይም ሚዛናዊ የህይወት ምርኩዝ ይለዋል። እንደዚህ አይነት ማህበረሰብ ውስጥ ህየወቱን የሚያጠፋ በጣም ጥቂት ነው፤ ለእንደዚህ አይነቱ ከንቱ ጥፋት የሚጋለጡ ግለሰቦች የሚኖሩበት ማህበረሰብ ሁልጊዜም ቢሆን ምንም የጠበቀ የማህበረሰብ ትስስር የሌላቸው ሚዛናዊ የህይወት ምርኩዝ የተሰበረባቸው ናቸው ይላል።
እዚህ ላይ የኢትዮጵያዊያንን የጎረቤትን ቡና ጠጡን ጥሪ ልብ ይሏል፤ ምን ያህል የማህበረሰብ ማስተሳሰሪያ ገመድ እንደሆነ መዘንጋት የለብንም። ህብረተሰብ ቡና ጠጡን በሚመስል በጣም ትንሽ ነገር ግን የዘለቄታ የህወት መስተጋብር ያላቸውን በጎ እና ጠንካራ የጋራ ትስስር በማህበረሰቡ ውስጥ ይፈጥራሉ ፤ ብሎም በማህብርረሰቡ ውስጥ ያሉትን ግለሰቦች በራዕይ ያገናኛሉ ፤ ይሄም በዕለት ተዕለት ኑሮእቸው ይገለጣል። ቡና በመጠራራት፤ በዓላትን በጋራ የማክበር መንፈስ፤ ሐዘንን በጋራ የማጽጽናት ፤ በጎን በጋራ የመመኘትን ፤ ብሎም የጋራ የሆነውን “ጎጆ” አገርን የመጠበቅ ጅግንናን ይጋራሉ ። ይሄም በቀላሉ የማይታይ በቁም ነጋር ላይ የተመሰረተ ትልቅ ነገር እነደሆነ ማህበረሰቡ በሚሰጠው ከበሬታ፤ ግለሰቦችም በማህበረሰቡ ውስጥ የከበረ ቦታ በማግኘት ከበሬታ የሚቸረው ሥራ እንዲሰሩ ይገፋቸዋል። ይሄንን በሌላ አንጻር ስንመለከተው ግለሰቦች ብቸኛ እና ግለኛ ከመሆን የሚመጣ መላ ቅጡ የጠፋበት ምስቅልቅል የሆነ የስብዕና አረንቋ ውስጥ እንዳይዘፈቁ ይረዳቸዋል። ስለ ስብዕና ልዕልናም በእጅጉ ይጨነቃሉ ፤ የዚህ ማህበራዊ ማዕቀፍ የሌላቸው ግለሰቦች ግን ለሌሎች ቀርቶ ለራሳቸውም ግድ ስለማይኖራቸው በቀላሉ ይወታቸውን ይቀጥፋሉ ፤ ሌሎችንም ይቀጥፋሉ፣ ያስቀጥፋሉ፣ የህግ እና የስብዕና ደርዝን ይዘላሉ።
እነኚህ ከላይ የዘረዘርናቸው የማህበረሰብ ማዕቀፍ ሰጠፉ የህግ እና የስብዕና ደርዝ በህብረተሰብም ላይም ይጠፋል። ይህም ማንም ለማንም አይጨነቅም፤ የጋራ የሚለው ዕምነት ይሸረሸራል ፤ በህብረተስ ውስጥ እየኖሩ ብቸኛ ይሆናሉ፤ አገር ውስጥ ሆነው ባይተዋር ይሆናሉ፤ የአብሮነት ፤ የአገርነት ፤ የአገር ልጅነት ስሜት ይበናል፤ ወንድም ፤ እህት ፤ ጎረቤት ፤ መንደር ፤ ቀዬ ትርጉም ያጣሉ፤ ወጥ ሥርዓት አይኖርም፤ ዕውቀት ትርጉም ያጣል፤ ብልጠት የዕውቀትን ቦታ ተቆናጦ ይቀመጣል፤ ጥፋት የመንጋ ሥርዓት ይሆናል፥ፍርዱም የመንጋ ይሆናል። ትናንትና የጨዋነት ምግባር መለኪያ የነበረው መስፈርት ይወድቅና በሌላ ይተካል። ከእደዚህ አይነት ምስቅልቅል ውስጥ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስተር ያሉት አይነት ምግባር ማማው ላይ ይቀመጣል፤ “እናንተ የሰራችሁትን እየጻፉ ነው እነሱ ምሁር የሚባሉት እነሱ ጥሩ ጫማ እንኳን የላቸውም ”… እዚህ ላይ ልንገነዘብ የሚገባን ዛሬ ህብረተሰባችን የደረሰበት የህይወት ምስቅልቅል እንዲሁ የተከሰተ አይደለም የህብረተሰብ የአስተሳሰብ እና የአሰራር ውጤት ነው። በተለይ ይሄ ሁሉ ግብስብስ በተለያዩ የዕምነት ቋጠሮዎች እና ድባቦች ባይያዙ እና ባይሸፈኑ ኖሮ ዛሬ ኢትዮጵያ የምትባል አገርም ሆነ ኢትዮጵያዊ የሚባል ህዝብ አይኖርም ነበር። የሚባል ቦታም ሆነ ህብረተሰብ ህይወት አልባ ቦታ በሆነ ነበር፤ የቀረው ዓለምም እንደ ዙ አይነት እይታ ባየን ነበር።
ከዚህ እንዴት ነው የምንወጣው? ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ነገ ለሚኖረ ው የኛው ልጆች ትውልድ ? ነገ ምንድን ነው? ዛሬ የኢትዮጵያዊያን ሥነ ልቦና ምን ይመስላል? አገሩን በጋራ ገምዶ ያለውን የእምነት ገመዶች ውስጥ አንዱን ስንቃኝ ፤ በአንድ የሃይማኖት መምህር ፊት የምናየውን እንደዚህ ለቁጥር ያሚያዳግት የሰይጣን መዓት ከየት የመጣ ነው ብለን እንድጠይቅ ያደርገናል ፤ ሰይጣንን ዛሬ ነው እንዴ ኢትዮጵያ የምታውቀው? ለቁጥር የሚያታክት የህብረተሰባችን ክፍል በአደባባይ በሰይጣን ስም ሲውዘፈዘፍ የምናየው ለምንድን ነው? የእግዚአብሔርን መኖር አማኝ ነኝ፤ ጥያቄዬ ግን እውነት ኢትዮጵያችን ከላይ እስከ ታች የሰይጣን መናኸሪያ ሆናለች? ዛሬ ኢትዮጵያ አምስት ሺህ ዘመን ያስቆጠረች አገር በማይመስል መልኩ ከዛም አልፎ አስቂኝ በሚመስል ትርኢት ፈውስ ታገኛለህ እየተባለ ስብዕናን በሚያዋርድ መልኩ ፊቱ በጫማ እየተመታ የሚወድቅበት አገር መሆኗን ማየት ከየት የመጣ ነው? ይሄ ብቻውን አንዱ የማህበራዊ ህይወት ሠንሠለት መበጣጠስ አንዱ መገለጫው ነው። ኸረ ዕውቀት ከወዴት አለህ? ማስተዋልስ እንዴት ደረስክ ያሰኛል።
እንደ አገር እና ህብረተሰብ የነገ እጣችን ምንድን ነው? እራሳችንን ለመመገብ እንኳን የበቃን አይደለንም ፤ እንደዛም ሆነን መጀመሪያ የሚያስጨንቀን አገራዊ ጉዳይ አይደለም ፤ ሥርዓት፣ ህግ እና የግብረገብ ልዕልና የሌለው ግለሰብም ይሁን ማህበረሰብ እጣ ፈንታው የጭለማ ላይ ጉዞ ነው የሚሆነው። እንደ ኢትዮጵያ በአብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ወጣት በሆነበት አገር ውስጥ ሲሆን ደሞ ችግሩን ይበልጥ የከፋ ያደርገዋል። በተበጣጠሰ የማህበረሰብ ሠንሠለት ውስጥ አዱኛን ለማፈስ በሚሽቀዳደሙ ጥቂት የህይወት ጉንዳኖች የብዙሃኑ ቤት የሆነው አገር የሚባለውን ነገር ኩይሳ ያደርገዋል። መዓት እና ምስቅልቅል የሚሆነውም ይሄው ነው። ከሰማይ እንደ መና ዱብ የሚል ነገር አይደለም የእኛው የእጅ ሥራ ውጤት ነው። የዳበረ የነጠረ የማህበረሰብ ትስስር ይላል ዳርካይም ግለሰቦች ባልረባ ሃሳብ እንዳይባክኑ ያደርጋቸዋል ማህበረሰብን የማገልገል ሃላፊነት እንዳለባቸው የገነዘባሉ፤ በሚያጋጥማቸው የዕለት ተዕለት ችግርም ብዙዎች አይንገላቱም ፤ ከዛ የበለጠ የአገር ራዕይ አለ ብለው ለዛ መስዋዕትነት ይከፍላሉ ፤ ቢደክመኝ የሚረዳኝ፤ ቢደክመን የሚረዳን አለን ብለው በማሰብ እራስን ብቻ አልፎም ጎሳን ብቻ አምልኮ ከመሞት ይወጡ እና የሰውን ልጅ ወደሚለው ከፍተኛ የአስተሳሰብ ቅድስና እራሳቸውን ከፍ ያደርጋሉ፤ በዚህም እንኳን የሰው ልጅ ቀርቶ ሳርም ቅጠሉም ይጠቀማል ብለው ያምናሉ፤ የስብዕና ከፍተኛ ማማ ላይ ይቀመጣሉ፤ መለኪያቸው የሰው ልጅ ብቻ ይሆናል።
የብዙሃን እናት የሆነችውን ኢትዮጵያን ከጎሳ በተለቀሙ ጥቂት የድግስ አንጋቾችን ሰብስቦ በንዋይ ናላቸውን በማዞር አገር በዚህ አይነት መልኩ እናስቀጥላለል ብሎ ማመን የዋህነት ሳይሆን ድንቁርና ነው። ዘመናዊ ድንቁርና ፤ ይልቁንም ዳርካይም እንደ ድህነት ያለ እራስን ለመግዛት የሚያስችል ትምህርት የሚሰጥ ት/ቤት ከቶውንም አይገኝም ይላል፤ በአገራችን አብዛኞቹ ስልጣን ላይ የተንፈራጠጡትን ስንመለከት ከዚሁ ከድህነት አቧራ ላይ የተነሱ መሆናቸው እንኳን ይልቁንም ለመጡበት ማህበረሰብ እንኳን በጎውን ሌት ተቀን እንዲያስቡ እና እንዲሰሩ ባደረጋቸው ነበር፤ ከእነሱ ስልጣን ዘመን መራዘም ይልቅ የህብረተሰብ የአሁን እና የወደፊት እንግልት ብሎም ምስቅልቅል ህይወት መስተካከል ይበልጣል የሚል ሃሳብ ባዳበሩ ነበር።
የማህበረሰብ የጋራ ውል የሆነው ህገ መንግስት በጋራ ፍላጎት የሚቀመር የራስን ፍላጎት ከማስፈር ባሻገር የሌሎችን ለመገንዘብ የሚተጋ የእሳቤ ቀመር በመያዝ የግለስብን ብሎም የማህበረሰብን መብት እና ፍላጎት ፍጽም በሆነ ሰብዓዊ መንገድ የሚያስተናግድ ሰነድ ካልሆነ በስተቀር ትናንት እኛ እንዲህ ስለሆንን ዛሬ እንዲህ መጻፍ አለበት እነንቶኔ እንዲህ ነበሩ ተብሎ በጥቂቶች ተጽፎ ለእናንተም ጭምር ነው የሚለው አይነት ሰነድ መከራን በቆይታ የሚያሳድር እንጂ የትም አያደርስም። አሁን ባለንበት በሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን የምጣኔ ሃብት ብቻ ሳይሆን የአስተሳሰብ ምጣኔ በረቀቀበት ዘመን ዘመኑን የማይመጥን ንግግር በፖለቲካ ደቂቃን በአደባባይ ሲነገር ስንሰማ አቤቱ የፈጣሪ ያለህ ያሰኛል። ዛሬ በአሜሪካን ጥቁሮች ላይ የሚወርደውን የዘረኝነት በትር በዓለም ጥግ ላይ ያሉ ስለሰው ልጅ የላቀ እሳቤ ያለው የሰው ልጅ በሙሉ ሲቃወም ስናይ እኛ ኢትዮጵያዊያኖች ግን አገራችን ውስጥ የአንድነቱ ጽድቅ እንኳን ቀርቶብን አስከፊ እና አጸያፊ አዳፋ እና የከረፋ የሆነውን የጎጠኝነትን ሸማ እንደልብስ ለብሰን ከእንስሳ ባነሰ አስተሳሰብ በአድባባይ ዳንኪራ እየወረድንበት እንገኛለን። በጋራ እየተራቡ በተናጥል እንዴት መፍትሄ ይፈለጋል? በሃያ አንደኛው ክፈለ ዘመን እንዴት አንዱ በአንዱ ላይ ብልጥ ሊሆን ይችላል ፤ እረሃብተኝነት የቆየ የጋራ ችግራችን ነው እሱን መጀመሪያ ማድረግ ግድ ይላል የሰው ልጅ እና ረሃቡ ፥ ኢትዮጵያ እና ረሃቧ ፤ ሰው መሆናችን እና ረሃባችን ካላስተሳሰረን አስር ሚሊዮን ጊዜ ወረቀት ላይ የሚጻፍ ጽሁፍ ሊያስተሳስረን አይችልም ይሄ ሞኝነት ነው። ሳይበሉ በረሃብ አለንጋ እየተገረፉ የእንቶኔ ዘር ነኝ የእከሌ ጎሳ ነኝ ማለት አይበጅም። ኢትዮጵያ ወዴት ነው የምትሄደው? ማነውስ የሚመራት ፥ የወደፊት እጣዋስ ምንድን ነው? ማነውስ ወደላቀው ሃሳብ የሚወስዳት? በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ በአንድ ሰው እና በአንድ ጎጥ ላይ የተመሰረተ ፍላጎት ከቶውንም አገርን ወደ ፊት ሊያራምድ እና ህዝብን ላጋራ ተጠቃሚነት ሊያበቃ አይችልም። የጋራ የሆኑትን የተመረጡ በጎ የቅድስና ሃሳቦችን የሚያሰባስብ ባለ ራዕዩ ማን ይሆን…
__
በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
ማስተዋል ጠግነው (Mastewale Teginew from London, UK)
ለዚህ ፅሁፍ መነሻ የሆነኝ እኤአ የካቲት 12፣ 2023 በለንደን ተጠርቶ የነበረው የተቃውሞ ሰልፍ ነው፡፡ የሰልፉም ዓላማ የኢትዮጵያ መንግስት የኦርቶዶክስ ቤ/ክን ሲኖዶስን ለሁለት ለመክፈል እያደረገ ያለውን ጣልቃገብነት መቃወም ነበር፡፡ እኔም እንደ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይነቴ በለንደኑ ሰልፍ ላይ በመገኘት ተቃውሞዬን አሰምቻለሁ፡፡
ወደኋላ ሳስበው ግን፣ ጠ/ሚ/ሩ ወደ ሥልጣን እንደመጡ ሰሞን የህዝብ ድጋፍ ለማግኘት ሲጠቀሟቸው ከነበሩ ቃላት በተቃራኒ ቆመው መገኘታቸው ሁልጊዜ ይገርመኛል፡፡ ከእነዚህ የአብይ አህመድ የሽንገላ ቃላት መካከል በዚህ ፅሁፍ ሁለቱን ለማስታወስ እሞክራለሁ፡፡
‹‹ኦርቶዶክስ ሀገር ናት›› እያለ ሲያታልለን የኖረው አብይ አህመድ እንዴት እንደዚህ ዓይነት ፀረ-ኦርቶዶክስ አቋም ሊያራምድ ቻለ›› የሚለው ጥያቄ ሁልጊዜ ይገርመኛል፡፡ እስቲ የነገሩን ሂደት ከመነሻው ጀምረን እንየው፡፡
ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድ በ2010 (እኤአ በ2018) ወደ ሥልጣን ሲመጣ የህዝብ ድጋፍ ለማግኘት ካደረጋቸው ተግባራቶች መካከል አንዱ በአሜሪካ የነበረውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ሲኖዶስ ወደ ሀገር ቤት እንዲመለስና እርቀ ሰላም እንዲሰፍን ማድረግ ነበር፡፡ በዚህ የእርቅ ሂደት ውስጥ ነበር ጠቅላይ ሚ/ር አብይ ‹‹ኦርቶዶክስ ሀገር ናት›› የሚልና የብዙዎችን ድጋፍ ያስገኘለትን ንግግር የተናገረው፡፡
‹‹ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ሀገር ናት›› እያለ በአደባባይ ሲሸነግለን የነበረው ጠ/ሚ/ር አብይና የሚመሩት መንግስት ግን ፀረ-ኦርቶዶክስ የሆነ ተግባር ውስጥ መግባት የጀመረው ብዙም ሳይቆይ ነበር፡፡ አጀማመሩም የቤተ ክርስትያኗን የአደባባይ በዓላት በማወክ ነበር፡፡ በተለይ በኦሮሚያና በደቡብ ክልል ውስጥ የሚገኙ የኦርቶዶክስ ክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ለዘመናት የጥምቀትንና የመስቀል በዓል ሲከበሩባቸው የነበሩ ቦታዎችን በመከልከልና የሃይማኖቱ ተከታዮች በአደባባይ እንዳይዘምሩ በማፈን የመንግስት የፀጥታ አካላት በዓላቱን በየዓመቱ ሲያውኩ ኖረዋል፡፡
የአደባባይ በዓላትን በማወክ የተጀመረው የመንግስት ተግባር ግን ወዲያው ቤተ ክርስትያኗን ለሁለት የመክፈል ሴራ ውስጥ ገባ፡፡ ይሄንንም ሰይጣናዊ ሥራ መጀመሪያ፣ በሐምሌ ወር 2011 (2019) የኦሮሚያ እምባ ጠባቂ ኮሚሽነር እና በኦርቶዶክስ ቤ/ክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በሆኑት በቄስ በላይ መኮንን በኩል፤ በመቀጠል ደግሞ በጥር ወር 2015 (2023) በእነ አባ ሳዊሮስ በኩል ሞከረው፡፡ የነአባ ሳዊሮስ ተግባር ብዙ ኦርቶዶክሳውያንን መስዋዕትነት አስከፈለ፡፡ እኔ በታሪክ ንባቤም ሆነ በህይወቴ አይቼ በማላቀው ደረጃ ቤ/ክ ለመጀመሪያ ጊዜ ማቅ (ጥቁር) ለብሳ አየኋት፡፡ እኛም በለንደን ተቃውሞ ሰልፍ የወጣነው ይሄንን የቤ/ክናችንን ሐዘን ለመጋራት ነበር፡፡
የእነ አባ ሳዊሮስን ‹‹መፈንቅለ ሲኖዶስ›› ተግባር ተከትሎ፣ ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድ የሰጡት ዛቻና ማስፈራሪያ የተሞላበት መግለጫ ግን፣ በጉዳዩ ውስጥ መንግስት በቀጥታ እጁ እንዳለበት የሚያረጋግጥ ነበር፡፡ ቆይተው ግን፣ ከጀርባ ሴራውን ሲጎነጉኑ የነበሩት ጠቅላይ ሚ/ር የህዝቡን ቁጣ ሲያዩ፣ አስታራቂ ሆነው መጡ፡፡
ጠ/ሚ/ር አብይ በመጋቢት 2010 (2018) ልክ ወደ ሥልጣን እንደመጡ ካደረጓቸው የድጋፍ ማሰባሰቢያ ጉዞዎች ውስጥ ከጂግጂጋ በመቀጠል የተጓዙት ወደ መቀለ (ትግራይ) ነበር፡፡ መቀለ ላይ ‹‹የትግራይ ህዝብ ለኢትዮጵያ ሞተር ነው›› በሚል ያደረጉት ንግግር ከበርካታ የትግራይ ህዝብ ከፍተኛ ተቀባይነትን እንዲያገኙ አድርጓቸዋል፡፡
ጠ/ሚ/ር አብይ እንደዚህ በቃላት የሸነገሉትን ህዝብ ግን፣ ለመስደብና በጠላትነት ለመፈረጅ ጊዜ አልወሰደባቸውም፡፡ በመጀመሪያ፣ ህወሓት የሰራቸውን ነገሮች ሁሉ በማጥላላት ጀመሩ፤ በመቀጠል ህወሓት ሲመራቸው የነበሩ እንደ ሜቴክና ታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክቶችን ‹‹የህወሓት የሙስና ተቋማት›› በማለት ተፈርጀው በመንግስት የቴሌቪዥን ጣቢያዎች ዘጋቢ ፊልም እንዲሰራባቸው ተደረገ፡፡ በመቀጠል የተቋማቱን መሪዎች ኢ/ር ስመኘውንና ሜ/ጀ ክንፈ ዳኘውን ወደ መግደልና ማሰር ገቡ፡፡
ከዚያም፣ ጠ/ሚ/ሩ ህወሓትንና ደጋፊዎቹን ‹‹ጁንታ›› የሚል ስያሜ በመስጠት፣ በመላው ኢትዮጵያ ተበትነው የሚገኙ ትግራዋዮች በሀገራቸው ተሸማቀው እንዲኖሩ አደረጉ፡፡ በስተመጨረሻም፣ መገናኛ መስመሮችን ሁሉ በመዝጋትና ጦር በማዝመት ‹‹አሳውን ለማጥመድ፣ ባህሩን ማድረቅ›› በሚል መርህ፣ የትግራይ ህዝብ ላይ ጦርነት አወጁ፡፡ በቃላት ሽንገላ የተጀመረው የጠ/ሚ/ር አብይ አህመድ የሥልጣን ጉዞ፣ መጨረሻው ውድመትና የህዝብ እልቂት ሆነ፡፡
__
በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
ኤፍሬም ማዴቦ (emadebo@gmail.com)
አገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት ሃምሳ አመታት ከረሃብ፣ ከጦርነት፣ ከመፈናቀልና ከፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግሮች ተገላግላ እፎይ ብላ የኖረችባቸው አጋጣሚዎች በጣት የሚቆጠሩ ናቸው። ሆኖም ኢትዮጵያ እንዳለፉት አምስት አመታት መሉ በመሉ የቀውስ አዙሪት ውስጥ የገባችበትና ህልውናዋ እራሱ አደጋ ውስጥ የገባበት ግዜ የለም። የህወሓት አገዛዝ በህዝባዊ ትግል ከሥልጣን ተባርሮ ጠሚ አቢይ አህመድ ኢትዮጵያን መምራት ከጀመሩ በኋላ ኢትዮጵያን እንደ ደም መጣጭ ተባይ ተጣብተዋት አልላቀቅ ያሏት ብዙ ችግሮች አሉ። ከእነዚህ ችግሮች ውስጥ የመንግስት ደካማነትና ከህግ በላይ መሆን፣የኤኮኖሚና ማህበራዊ ችግሮች፣የሰላምና መረጋጋት አለመኖር፣ህገወጥነት፣ ብሔር ተኮር ግዲያ፣የብሔር ግጭትና የርስ በርስ ጦርነት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
ዕለተ ማክሰኞ ጥቅምት 24 2013 ዓ.ም ቀን ከሱ በፊት ከነበሩትና ከሱ በኋላ ከመጡት ዕለተ ማክሰኞዎች የሚለየው ምንም ነገር የለም። የትግራይን ህዝብ ለአመታት ሲጠብቅ፣ እርሻውን ሲያርስለት፣ መንገድ ሲሰራለትና በተቸገረ ግዜ ሁሉ ሲደርስለት የነበረው የሰሜን ዕዝ ሰራዊት ማክሰኞ ጥቅምት ሃያ አራትን ያሳለፈው ለአመታት ሲያደርግ እንደነበረው የትግራይን ህዝብ ሲረዳ፣ ሲንከባከብና የክልሉን ሰላምና ጸጥታ ሲያስጠብቅ ነው። ማክሰኞ ጥቅምት 24 ሌሊት ግን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሁሌም ስትታወስ የምትኖር የደምና የክህደት ሌሊት ናት። ጥቅምት 24 ማክሰኞ ወደ ረቡዕ መሸጋገሪያ ሌሊት ላይ ነበር ሰሜን ዕዝ “የኔ ናቸው” በሚላቸው በራሱ ልጆች ክህደት የተፈጸመበትና በተኛበት እንደ ፋሲካ በግ የታረደው። የትግራይን፣የአፋርንና የአማራን ክልሎች ለሚቀጥሉት ሁለት አመታት ጦርነት፣መፈናቀል፣ ረሃብ፣ ስደት፣ ሞትና መከራ ውስጥ ይዞ የገባው ይህ ማክሰኞ ጥቅምት 24 ሌሊት የህወሓት ኃይሎች የፈጸሙት ክህደትና ጭካኔ ነው።
የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት ከህወሓት ጋር ያደረገውና 2 አመት የፈጀው እልህ አስጨራሽ ጦርነት ዕልባት ያገኘው ዛሬ “የፕሪቶሪያው ስምምነት” እየተባለ በሚጠራው ስምምነት ነው። የዛሬ አመት ጥቅምት ወር ላይ የኢትዮጵያ መንግስትና የህወሓት አማጽያን ፕሪቶሪያ ላይ የደረሱት የሰላም ስምምነት 15 አንቀጾች አሉት።-ከ15ቱ አንቀጾች በተለይ በዚህ ጽሁፍ ጸሃፊ እምነት ከዋና ዋናዎቹ አምስት አንቀጾች ውስጥ የኢትዮጵያ መንግስት ተሽቀዳድሞ ተግባራዊ ያደረገው “የኢትዮጵያ መንግስት ህወሓት የሽብርተኝነት ፍረጃው እንዲነሳለት ያደርጋል” የሚለውን አንቀፅ ብቻ ነው። የህወሓት ኃይሎች ትጥቅ ይፈታሉ፣ በተለይ ከባድ መሳሪያቸውን የማስፈታቱ ስራ ቅድሚያ ይሰጠዋል የሚለው አንቀፅ ሙሉ በሙሉ ተጥሷል፣ የህወሓት ሰራዊት ትጥቁን ፈትቶ ሰላማዊ ህይወት የሚኖርበት መንገድ ይፈለግለታል የሚለው አንቀፅ ሙሉ በሙሉ ተጥሷል፣ ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ መካከያ ሰራዊት ብቻ ነው የሚኖረው የሚለው አንቀፅ ተጥሷል። የኢትዮጵያ መንግስትና ህወሓት ተወያይተው ትግራይ ውስጥ ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ያቋቁማሉ የሚለው አንቀፅም ተጥሷል። በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት ትግራይ ውስጥ የሽግግር መንግስት ተቋቁሟል የሚል መከራከሪያ ሊነሳ ይችላል፣ ነገር ግን ትግራይ ውስጥ የተቋቋመው የሽግግር መንግስት በ”ሃላላ ኬላ” ስምምነት መሰረት ነው እንጂ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት አይደለም። ባጠቃላይ ጥቅምት 24 2013 ዓ.ም ሌሊት ላይ የህወሓት ኃይሎች በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸሙትን አይነት ክህደት የኢትዮጵያ መንግስት ሃላላ ኬላ ውስጥ ከህወሓት መሪዎች ጋር ተሰብስቦ በፕሪቶሪያው ስምምነት ላይ ደገመው። ዛሬ አማራ ክልል ውስጥ ለሚታየው ፍጹም አላስፈላጊ የሆነ የእርስ በርስ ጦርነት አንዱ ምክንያት የሃላላ ኬላ ክህደት ነው!
ባለፉት አምስት አመታት ኢትዮጵያ ውስጥ በነጋ በጠባ እንቆቅልሽ እየተባለ “ምን አውቅልሽ” የሚል አካል ያልተገኘለት ኩነት ቢኖር ኦሮሚያ ውስጥ በተለይ ወለጋ ውስጥ ኦነግ-ሸኔ የሚባለው ሽብርተኛ ቡድን የአማራ ተወላጆችን በነጋ በጠባ ያለምንም መከልከል የመግደሉ ጉዳይ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ በ2013 ዓ.ም ሐምሌ ወር የህወሓት ኃይሎች “ሂሳብ እናወራርዳለን” ብለው እየዛቱ መጥተው ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱትም አማራ ክልል ውስጥ ነው። የዚህ ጽሁፍ ጸሃፊ ይህንን የሚለው ከማህበራዊ ሚድያ ባገኘው መረጃ አይደለም። ወራሪው የህወሓት ጦር ከደሴና ኮምቦልቻ ከተባረረ በኋላ በመጀመሪያዎቹ ሶስት ቀናት ውስጥ ደብረሲናን፣ሸዋ ሮቢትን፣ደሴን፣ጢጣን፣ኮምቦልቻን፣ ባቲን፣ሚሌን፣የካሳጊታ አካባቢዎችን፣ጭፍራን እና ሰመራን እየተዘዋወረ ከጎበኘና የህወሓት ኃይሎች ጥቃት ሰለባ የሆኑ ዜጎችን ካናገረ በኋላ ባገኘው የመጀመሪያ መረጃ መሰረት ነው። የሚገርመው የህወሓት መሪዎች ጦርነቱ ከቆመ ከአስር ወር በኋላ ዛሬም ወልቃይትና ራያ የኛ ነውና እናስመልሳለን በሚል ከፍተኛ የጦር ዝግጅት የሚያደርጉት ከአማራ ጋር ለመዋጋት ነው።
የኦሮሞ ኃይሎች በሽመልስ አብዲሳ አጋፋሪነት ሸገር ከተማን ለመመስረት ባደረጉት የቤት ማፍረስ ዘመቻ በከፍተኛ ደረጃ የተጎዳው አማራው ነው። አማራ በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች በተለይ ወለጋ ውስጥ ባለፉት አምስት አመታት በግፍ ተገድሏል። በተለይ ባለፈው አመት ጥቅምት ወር አካባቢ ከ200 በላይ የአማራ ተወላጆች ወለጋ ውስጥ በግፍ ተጨፍጭፈው ዜናው የአለም አቀፍ የዜና ተቋሞችን ትኩረት በሳበበት ቀን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ትኩረት ሰጥቶ ለህዝብ ያሳየው ጠሚ አቢይ አህመድ ችግኝ ሲተክሉ ነው። ይህንን ጉዳይ በተመለከተ የተከበሩ ዶር ደሳለኝ ጫኔ ሟቾችን በብሔራዊ ሀዘን እናስባቸው ብለው ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሃሳብ ሲያቀርቡ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ የ200 ሰላማዊ ዜጎችን በግፍ መጨፍጨፍ ከመጤፍ አልቆጠሩቱም፣እንዲያውም በዕለቱ ለዶር ደሳለኝ ጫኔ የሰጡት መልስና መልሱን ሲሰጡ የነበራቸው የሰውነት ቋንቋ ሰውየው የርህራሄ ጠብታ የሌለባቸውና ምን ያክል የህግ አስፈጻሚው አካል ተላላኪ እንደሆኑ ነው ያሳበቀባቸው!
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከቆመ በኋላ ከትግራይ ልህቃን አፍ በየቀኑ የሚወጣው ቃል ወልቃይት ጠገዴን አናስመልሳለን የሚል ቃል ነው። ጌታቸው ረዳ ሥልጣን ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የትግራይን ክልል ችግር ለመፍታት ከሄደበት መንገድ ይልቅ አገር ቤትና ውጭ አገር ላለው የትግራይ ማህበረሰብ ትግራይ ምን ያክል የታጠቀ ሰራዊት እንዳላትና ወልቃይት ጠገዴን ለማስመለስ በዝግጅት ላይ እንዳሉ ለመናገር የሄደበት መንገድ እጅግ በጣም ይበልጣል። እስካፍንጫቸው የታጠቁ የህወሓት ኃይሎች ወልቃይት ጠገዴን ለማስመለስ አሁንም ከፍተኛ ስልጠና እና የጦር ልምምድ እያካሄዱ እንደሆነ የሚያሳዩ ብዙ መረጃዎች አሉ። በመጨረሻም ከሰሞኑ የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶር አብርሃም በላይ የወልቃይት ጠገዴ ተፈናቃዮችና ወልቃይት ጠገዴ ወደ ቀድሞ ቦታቸው ይመለሳሉ በማለት በ1928 ዓ.ም. የሮማው ጳጳስ ቤኒቶ ሙሶሊኒ ኢትዮጵያን እንዲወር የሰጡትን አይነት ቡራኬ የመከላከያ ሚኒስትሩም ወልቃይት ጠገዴን ወደ ትግራይ ለማስመለስ ምንም አይነት ስራ መሰራት አለበት የሚል አይነት ቡራኬ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ካለፈው መጋቢት ወር መጨረሻ የክልል ልዩ ኃይል የሚባል ስብስብ አያስፈልግም የሚል ህግና መመሪያ አውጥቶ ህጉን ተግራባዊ ማድረግ ጀምሯል። የክልል ልዩ ኃይል መኖር የለበትም የሚለውን ሃሳብ የዚህ ጽሁፍ ጸሃፊ ከማንም ሰው በላይ ይደግፋል፣ ይህንን ሃሳብ ባለፉት 20 አመታት በከፍተኛ ደረጃ አራምዷል። ነገር ግን የክልል ልዩ ኃይሎች መፍረስ አለባቸው ብሎ ህግና መመሪያ ማውጣትና ህግና መመሪያውን ተግራባራዊ ማድረግ በጣም የተለያዩ ስራዎች ናቸው። የኢትዮጵያ መንግስት ያልተረዳው ይህንን ቁልፍ ሃሳብ ነው። ግን በእርግጥ የኢትዮጵያ መንግስት ይህንን ሃሳብ አልተረዳውም ወይስ ሌላ ድብቅ አላማ አለው?
ከቅርብና ከሩቅ ከፍተኛ ርብርብ ባይደረግና ከፍተኛ መስዋዕትነት ተከፍሎ አከርካሪውን ባይመታ ኖሮ እጅግ በጣም ከፍተኛ ቁጥር ያለውና የፌዴራሉን መንግስት ጭምር ማንገዳገድ የቻለ የታጠቀ ኃይል ያለው የትግራይ ክልል ነው፣ በሌላ በኩል ደግሞ ለፌዴራሉ መንግስት መሳሪያ መስጠት የቻለና ከፍተኛ ቁጥር ያለው የታጠቀ ልዩ ኃይል ያለው ኦሮሚያ ክልል ነው። የፕሪቶሪያውን ስምምነት የሃላላ ኬላ ውኃ በላው እንጂ የትግራይ ልዩ ኃይሎች በአለም አቀፍ ደረጃም ድርድር ተደርጎ መሳሪያቸውን እንዲፈቱ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ታዲያ ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነና እስካፍንጫው የታጠቀ ልዩ ኃይል ያላቸው እነዚህ ሁለት ክልሎች እያሉ የክልል ልዩ ኃይሎች ትጥቅ ይፍቱ የሚል ህግና መመሪያ ሲወጣ መመሪያው የተጻፈበት ቀለም ሳይደርቅ መጀመሪያ አማራ ክልል ውስጥ ተግባራዊ እንዲሆን የተፈለገው ለምንድነው? የአማራ ክልል ልዩ ኃይሎች ትጥቅ መፍታት የለባቸውም እያልኩ አይደለም። የዚህ ጽሁፍ ጸሃፊ ትልቁ ጥያቄ በዚህ ጽሁፍ ውስጥ የተጠቀሱት የኢትዮጵያ መንግስት በማድረግም ባለማድረግም የፈጠራቸው ውስብስብ ችግሮች እያሉ፣አማራ በየቦታው ያለምንም ከልካይና ጠባቂ እየተገደልኩ ነውና እራሴን መከላከል አለብኝ የሚል እምነት ባደረበት ግዜና፣ የአማራ ህዝብ ከዚህ በፊት ወደ ክልሌ መጥቶ ከፍተኛ በደል የፈጸመብኝ ኃይል አሁንም በህልውናዬ ላይ እየመጣ ነው ብሎ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ በገባባት ወቅት፣ የኢትዮጵያ መንግስት የአማራን ልዩ ኃይልና ፋኖ ትጥቅ ለማስፈታት እሽቅድምድም ውስጥ የገባው ለምንድነው የሚል ነው። የፕሪቶሪያውን ስምምነት ጠጋ ብለን በአንክሮ ካየነው፣ አገር ለማፍረስ ቆርጠው የተነሱትን የህወሓት ኃይሎች ትጥቅ የማስፈታቱ ሂደት የትግራይን ክልል የጸጥታ ሁኔታ ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት ይላልኮ፣ ታድያ ለምንድነው የአማራ ልዩ ኃይልና ፋኖን ትጥቅ የማስፈታቱ ዘመቻ የአማራ ክልል ያለበትን የህልውና ስጋት ከግምት ውስጥ ያላስገባው?
ደግሜ ደጋግሜ መናገር እፈልጋለሁ፣ የጠሚ አቢይ አህመድ መንግስት ከአማራ ኃይሎች ጋር የጀመረው አርቆ አስተዋይነት የጎደለው ጦርነት የኢትዮጵያን እንደ አገር ቀጠይነት አደጋ ላይ የሚጥል አደገኛ ጦርነት ነው። ስለዚህ የኢትዮጵያ መንግስት በጦር መሳሪያ፣በዋና ዋና የሜዲያ አውታሮቹና በማህበራዊ ሜዲያ በአማራ ክልል ውስጥ የከፈተውን ዘመቻ በአስቸኳይ አቁሞ ለከሃዲዎቹና አገር ለመበትን ቆርጠው ለተነሱት ህወሓትና ኦነግ – ሸኔ በአለም አቀፍ ደረጃ ያደረገውን የድርድር ግብዣ፣ ከፌዴራል ኃይሎች ጋር ተሰልፈው አገር ላዳኑ የአማራ ኃይሎችም መስጠት አለበት። የኢትዮጵያ መንግስት ይህንን የማያደርግበት ምንም ምክንያት ሊኖር አይችልም። ስለዚህ የአገር መከላከያ ሰራዊትን በአገራዊ ኃይል ላይ አዝምቼ ኢትዮጵያን እገነባለሁ እያለ የሚነግረን የኢትዮጵያ መንግስት፣ኢትዮጵያዊያን እርስ በርስ ተዋግተን ኢትዮጵያን ማፍረስ እንጂ መገንባት እንደማንችል ተረድቶ ይህንን የጀመረውን ጭፍን የጨለማ ጉዞ በአስቸኳይ ማቆም አለበት።
በቅርቡ አንድ የኦሮሚያ ክልል ባለሥልጣን በአሸንዳ በዓል አከባበር ላይ ተገኝቶ ባሰማው ንግግር “የትግራይና የኦሮሞ ህዝብ በጋራ ሆኖ የሚታገልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል” የሚል አጅግ በጣም አሳፋሪ ንግግር ተናግሯል። ይህ ሰው የኦሮሞና የትግራይ ልህቃን ከሁለቱ ብሔሮች ውጭ ላለው ከ70 ሚሊዮን በላይ ለሆነው ኢትዮጵያዊ ምን ያክል ንቀት እንዳላቸው በግልጽ በአደባባይ መስክሯል። በእርግጥም እነዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ለብሔር ፖለቲካ ህጋዊ ቅርጽና ይዘት የሰጠውን ወልጋዳ ህገመንግስት አብረው የጻፉ የትግራይና የኦሮሞ ልህቃን “ብሔር” የኢትዮጵያ ፖለቲካ መሰረት ሆኖ እንዲቀጥል የማያደርጉት ምንም ነገር የለም።
ብዙዎቻችን የዚህን ሳያስበው እውነቱን የነገረንን ሰው ንግግር ንቀን እናልፍ ይሆናል፣ ነገር ግን የታሪክ ባለጸጋዋ መንደር ሃላላ ኬላ ብዙ ትምህርት አስተምራናለችና የኢትዮጵያ እንደ አገር ቀጣይነት የሚጠቅመንና ከኢትዮጵያና ከኢትዮጵዊነት ውጭ ሌላ ምንም መጠጊያ የሌለን ኢትዮጵያዊያን ይህንን በእኛነታችን ላይ ለመዝመት ቆርጦ የተነሳ አገር አፍራሽ ህብረት ማስቆም አለብን። በረጅም ግዜ ፀረ-ኢትዮጵያ አቋማቸው የሚታወቁት የትግራይና የኦሮሞ ልህቃን አማራውን ቢቻል ቁጥሩን በግማሽ ለመቀነስ አለዚያም አጎንብሶ እነሱን እየተለማመጠ እንዲኖር ለማድረግ መተባበራቸውና ጥምረት መፍጠራቸው ሊገርመን አይገባም። ወደኋላ ዞር ብለን የቅርብ ግዜውንና የሩቁን ታሪካችንን ብንመለከት፣ ኢትዮጵያን ለመውረር የመጡ ተስፋፊዎችና ቅኝ ገዢዎችም አልሳካ አላቸው እንጂ፣ ኢትዮጵያን ለማንበርከክ መጀመሪያ አማራውን መከፋፈል፣ ማዳከምና አቅመ ቢስ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አምነው ምሁራኖቻቸው ስትራቴጂና ዕቅድ ነድፈዋል፣የጦር አበጋዞቻቸውም ዕቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚችሉትን ሁሉ አድርገዋል።
ባለፉት 30 አመታት አገራዊ ማንነት (ኢትዮጵያዊነት) ደብዝዞ የብሔር ማንነት ጎልቶ እንዲወጣ ከፍተኛ የፖለቲካ ስራ በመሰራቱ ዛሬ ኢትዮጵያዊነት ተዳክሟል፣ ኢትዮጵያ ሲባል የሚያንገፈግፋቸው ኃይሎች የፖለቲካውን መድረክ ተቆጣጥረዋል፣ከሁሉም በላይ ደሞ አማራውን ካጠፋን ወይም ካዳከምን “ኢትዮጵያ” ብሎ የሚነሳ ሌላ ኃይል አይኖርም ብለው ያሰቡ የኦሮሞና የትግራይ ጽንፈኛ ኃይሎች የአላማ አንድነት መፍጠራቸው ብቻ ሳይሆን አማራ ክልል ውስጥ ጦርነት ከፍተዋል። የትግራይና የኦሮሞ ልህቃን ትብብር አላማው ከተቻለ የተዳከመች፣ የእነሱን ጥቅም የምታስጠብቅና በነሱ የበላይነት የምትመራ ኢትዮጵያ መፍጠር ነው፣ ይህ ካልተቻለ ደሞ የየራሳቸውን አገር መፍጠር ነው። ይህ ያልተቀደሰ የኦሮሞና የትግራይ ልህቃን ትብብር የሚያስፈራው አማራውን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ከምትባል አገር ውጭ ህልውናቸው አደጋ ውስጥ የሚገባውን የአፋርን፣ የሱማሌን፣የጋምቤላንና የደቡብ ኢትዮጵያን ህዝብ ጭምር ነው።
ባለፉት 5 አመታት ጎራ ለይተን ተወነጃጅለናል፣ተሰዳድበናል፣አንዳችን ሌላውን ተለጣፊ፣ ከሃዲ፣ባንዳ ተባብለናል። አንዳንዶቻችን በፍጹም ለአገር የማናስብ ሌሎቻችን ደሞ የኢትዮጵያ ብቸኛ ጠበቃ ሆነን እራሳችንን አይተናል። እነዚህ አንዳንዶቻችን ደጋፊዎች ሌሎቻችን ተቃዋሚዎች መስለን የታየንባቸውና ያደረግናቸውና ያላደረግናቸው ነገሮች ማናችንንም የተሻለ ቦታ ላይ አላስቀመጡንም፣ይልቁንም እኛ ስንኗቀርና ስንባላ አይናችን እያየ አገራችን የመበታተን አደጋ ውስጥ ገብታለች። የጠሚ አቢይን መንግስት ደግፈንም ተቃውመንም ታግለናል፣ግን ማናችንም አገራችንን ዛሬ ከገባችበት እጅግ በጣም አደገኛ ሁኔታ ማዳን አልቻልንም! ይህ ፍጹም አሌ ልንለው የማንችለው ሃቅ የሚነግረን አንድ ትልቅ ጉዳይ አለ፣ እሱም እኛ ኢትዮጵያዊያን እስካሁን በመጣንበት መንገድ መቀጠል እንደሌለብንና አካሄዳችንን፣የትግል ስልታችንን፣ ስትራቴጂያችንን እና በተለይ የኢትዮጵያን ችግሮች የምንመለከትበትን መንገድና ለችግሮቹ መፍትሄ ለማምጣት የምንሄድበትን መንገድ ፈትሸን መቀየር እንዳለብን ነው።
ኢትዮጵያ እንደ አገር ብትቀጥልም ባትቀጥልም ይብዛም ይነስ አማራ በቆዳ ስፋቱ፣በህዝብ ቁጥሩና በተፈጥሮ ኃብቱ ትልቅ ህዝብ ነውና ካለ ኢትዮጵያ መኖር ይችላል። ኢትዮጵያ የምትባል አገር ግን ካለ አማራ መኖር እንደማትችል ኢትዮጵያ ብቸኛ ውሎ መግቢያችን እና ማደሪያ ቤታችን የሆነች ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ኢትዮጵያና አማራ ተለያይተው የሚኖሩበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ዛሬ ነገ ሳንል አሁኑኑ ማድረግ ያለብንን ሁሉ ማድረግ መጀመር አለብን። ኢትዮጵያንና አማራን ከፀረ-ኢትዮጵያና ፀረ-አማራ ኃይሎች ማዳን የምንችለው ነገ ሳይሆን ዛሬ ነው። ትናንት እና ከትናንት ወዲያ የታገልናቸው ኃይሎች ባህሪይ፣የፖለቲካ ፍላጎትና አላማ ዛሬ ከምንታገላቸው ኃይሎች ባህሪይ፣የፖለቲካ ፍላጎትና አላማ ይለያልና፣ እኛም ትናንት እና ከትናንት ወዲያ የታገልንበት መንገድና የተከተልነው የትግል ስትራቴጂ ዛሬ መከተል ካለብን የትግል ስትራቲጂና ስልት የተለየ መሆን አለበት። ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ የትናንቱን ከስህተታችን ለመማር ብቻ እንጂ ለመሰዳደብ፣ እርስ በርስ ለመካሰስና ለመወነጃጀል አናድርገው። የምናቅደው ዕቅድ፣ የምንሰራው ስራ፣ዘመቻችን፣ውሏችንን፣ አዳራችን እና ፀሎታችን ሁሉ ኢትዮጵያን ከፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች ለማዳን ይሁን! ለክሱና ለመወቃቀሱ ኢትዮጵያችን ከዳነች በኋላ ብዙ ግዜ ይኖረናልና ለሱ አንቸኩል!!!
__
በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ
ነጻ ምልከታ
ከእስጢፋኖስ መኰንን
ብልጽግና በኦሮሞ ጽንፈኞች የበላይነት የሚመራ አደገኛ ሃይማኖታዊ ፓርቲ ነው። የኢትዮጵያ መንግሥትን ከፍተኛ ሥልጣን በአብዛኛው የተቆጣጠሩት የብልጽግና ወንጌል ተከታይ ኦሮሞች መሆናቸውን ለመገንዘብ ከጠቅላይ ሚንስትሩ እስከ ከንቲባዋ፡ ከኢታማጆር ሹሙ እስከ ማረሚያ ቤት አዛዦች ያሉትን ዋና ዋና ባለሥልጣናትን መመልከት ይበቃል። መከላከያን፡ ፖሊስንና ድህንነቱ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ደረጃ የተቆጣጠሩት እኒህ አማራ ጠል ኦሮሞች ሲሆኑ የኦሮሞ ልዩ ኃይልን አሰልጥነው መጠነ ሰፌ ዘር ትኮር ጭፍጨፋ ለማስጀመር ሁነኛ ቀን እየጠበቁ ነው።
ጠቅላይ ሚንስትሩ “በአንድ ጀንበር መቶ ሺ ሰው ማሳረድ . . . “
“ቀይ ሽብርን አሥር ግዜ የሚያጥፍ እርምጃ እንወስዳለን” ያሉት ያስታውሷል።
የብልጽግና አባል የሆናችሁ የክልል ባለሥልጣናት ፡
በኦሆዴድ የበላይነት ከሚመራውን ብልጽግና በአስቸኳል ለቅቃችሁ ካልወጣችሁ፡ በዚህ ፓርቲ ባለሥልጣናት፡ ካድሬዎችና የታጠቁ ኃይላት ለተፈጸሙ እጅግ አሰቃቂና ዘግናኝ ግድያዎች ሁሉ ተጠያቂ እንደምትሆኑ፥ ለግለ-ሰባዊ በቀልም የምትጋለጡ እንደሆነ ልታውቁ ይገባል።
የብልጽግና ግፍ ተዘርዝሮ አያልቅም። በፖለቲካ ሻጥር ምክንያት የተለኮስውን የሰሜኑን ጦርነትና ያስከተለውን ሰብኣዊና ቁሳዊ ውድመት ትተን፡ በኦሮሚያና በአዲስ አበባ ብቻ የተፈጸመውን ግፍ በጥቂቱ እንዳሥስ፥ ኦሆዴድ ብልጽግና በኦነግ ሸኔ አያማኻኘነት በመቶዎች የሚቆጠሩ ህጻናት አሳርዷል፡ የእናት ሆድ ቀዶ ሽል ወርውሯል። በሻሸመኔ ሰው በቁሙ ቆዳው ሲገፈፍ፥ ካህን በካራ ሲታረድ፥ ቤቶች በእሳት ሲጋዩ እያየ ለማስቆም ምንም ሙከራ አላደረገም። ወለጋ ውስጥ በሺህ የሚቆጠሩ ንጹህ አማሮች በዘግናኝ ሁኔታ ሲጨፈጨፉ እንደ መንግሥት አልደረሰም፥ ጥፋተኞችንም ለሕግ አላቀረበም።
ኦሆዴድ ብልጽግና በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማሮችን በማንነታቸው ከኦሮሚያ አፋናቅሎ ለረሃብና እርዛት፡ ለበሽታና ሞት ዳርጓቸዋል። ሸገር በሚለው ከተማ መስጂድ አፍርሷል፥ አብያተ ክርስቲያን አጋይቷል፡ ካህናት አስደብድቧል፡ አስገድሏል። በሺዎች የሚቆጠሩ አማሮችን በማንነታቸው ብቻ ከሥራ አባርሮ ለመከራና ለችግር ዳርጓቸዋል። የድሆች ጎጆ አፍርሶ በአስራ ሺህ የሚቆጠሩ ዜጎችን ጎዳና ላይ በትኗል፡ መድረሻ ያጡ ህጻናትን በጅብ አስበልቷል።
ብልጽግና ዜጎችን በሃሰት ከስሶ በእስር ያማቅቃል፡ በማጎሪያ ያሰቃያል፣ አሥሮ ምግብና ሕክምና ይነፍጋል፥ ከእስር ቤት አውጥቶ ይረሽናል። በአማራ ክልል ጦርነት ከፍቶ ከተሞችን በድሮንና በከባድ መሳሪያ ይደበድባል። ቤት ለቤት እየዞረ ያልታጠቁ ሰዎችን ይደበድባል፡ ወጣቶችን ደጃፋቸው ላይ ይረሽናል።
እናንት የክልል ብልጽግና ፓርቲ አባላት፡
የፓርቲው አባላት እንደመሆናችሁ መጠን ኦሆዴድ ብልጽግና ለሚፈጸማቸው አሰቃቂ ግፎች ሁሉ፡ እጃችሁ በቀጥታ ባይኖርበትም፡ በፓርቲ አባልነት ብቻ ተጠያቂ ከመሆን ፈጽሞ አታመልጡም። ከተጠያቂነት የምታመልጡበት መንገድ ቢኖር ከወዲሁ ራሳችሁን ከፓርቲው በማግለል ብቻ ነው። በአንዳንድ ክልሎች በሺዎች የሚቆጠሩ የብልጽግና አባላት ፓርቲውን ተሰናብተዋል። የቀራችሁትም በግዜ ለቅቃችሁ ካልወጣችሁ በቀር ለፈሰሰው ንጹህ ደምና በወገን ላይ ለደረሰው ግፍና መከራ ተጠያቂ ከመሆን አትድኑም።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ
__
በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ ፡ t.me/borkena
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ