spot_img
Wednesday, March 22, 2023
Home Blog

ሞትና ምላሽ  (በሺፈራው አበበ )

ከኦንታሪዮ ሀዘን ባለስልጣን ገጽ የተወሰደ

በሺፈራው አበበ 

በምድር ላይ ስንኖር ትልቁ አደጋ ሞት ነው። 

ድሮ ሞት ብርቅ ነበር ፣ ክብርም ነበረው። ባለፍ ባገደም የሚጠፋ ህይወት አልነበረም። በተለይ በሰው እጅ መሞት ትልቅ ጉድ ነበር፤ በመብረቅ የመመታት ያህል እንግዳ ነገር ነበር። 

ሰው እግዜሩንም መንግስትንም ፣ ማህበረሰቡንም ፈርቶና አክብሮ ይኖር ነበር። 

ዛሬ ላይ የሰው ሞት የዝንብ ሞት ያህል ተቆጥሯል። ከቅርብ ዘመድ ባለፈ ማንም ስለሌላው ሞት ግድ አይለውም። ሺህዎች በአንድ አርፋጃ በማንነታቸው ተገድለው ምንም እንዳልተፈጠረ የመንግስትም የግለሰብም ቢዝነስ እንደተለመደው ይቀጥላል። 

መንግስት ለሰው ህይወት የሚሰጠው ዋጋ ለአንድ የዛፍ ችግኝ ከሚሰጠው ዋጋ ያነሰ ሆኗል። 

ንጹሃን ዜጎች በመቶዎች ተገድለው፣ የአገሪቱ መሪዎች ነብስ ይማር እንኳ ሳይሉ የሃብታም መኪና ማቆሚያ ለማስመረቅ ተግተልትለው ይሄዳሉ። 

በዛሬዋ ኢትዮጵያ ፣ የእቃ ዋጋ ሰማይ ተሰቅሏል ፤ የሰው ህይወት ግን ጥንቡን ጥሏል። 

በእርግጥ የሰው ህይወት መርከስ ከጀመረ ውሎ አድሯል፤ ሃምሳ አመት ሊሞላው ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ የግፍ ሞትን እንደ አርባ ቀን እድሉ ቆጥሮ መኖር ከጀመረም ያንኑ ያህል ጊዜ ሆነው። 

የደርግ መንግስት ቀይ ሽብር ብሎ ቁጥሩ በውል የማይታወቅ ወጣት ጨፈጨፈ። ከቁጣ ቢዘል ከቁንጥጫ የማያልፍን ልጅ ጭምር፣ ጸረ-አብዮተኛ የሚል ታርጋ ለጥፎ በጥይት ደብድቦ ገደለ። አዛውንቱ አደባባይ ወጥቶ የወጣቶች ሬሳ ረግሞ እንዲመለስ ተደረገ። ወላጅ የጥይት ዋጋ ከፍሎ የልጆችን አስከሬን ወሰደ:: ሞቴን ከልጆቼ በፊት አድርገው ብሎ እንዳልጸለየ፣ የልጅ መቃብር ላይ ቆሞ አለቀሰ። 

ያኔ የተጀመረው ለቅሶ ዛሬ ድረስ ቀጥሏል፤ በስፋቱም በክፋቱም ያለፈውን እያስናቀ። መለስ የሚል የመሪ ልቦና፣ ዘንበል የሚል የፈጣሪ ጆሮ ወይም ሞት በቃኝ የሚል ህዝብ አልተገኘም!  

የኢትዮጵያ ህዝብ ላለፉት 50 አመታት ስጋትና ፍርሃት የሞላበት ህይወት ነው የሚኖረው። ጨካኝ መንግስታት ሃሞቱን አፍሰውታል። ለመብቱ መቆም ቀርቶ ፣ ርህራሄ እንዲደረግለት እንኳ በድፍረት አይጠይቅም። በእግዜር አምሳል ተፈጥሮ የሰውነት ክብሩ ምድር ላይ ሲጎተት፣ የባሰ አታምጣ ብሎ የሚኖር ነው ። 

የባሰው ከመምጣት ግን አልቀረም። ስልጣን ከአንድ “ሰው-በላ” መንግስት ወደ ሌላ “አገረ-በላ” መንግሥት 1983 ዓ.ም. ላይ ተሸጋገረ። ህወሃት-ወያኔ አገርና ህዝብን የሚክድ ስርአት በክንዱ ብርታት አቆሞ ወደግድያ ተሰማራ። አጅቦት ከመጣው ኦነግ ጋር ሆኖ በአርባጉጉ፣ በበደኖ ፣ በጋራሙለታ እና ፣ በሃረር መአት አማሮችን በአሰቃቂ ሁኔታ ፈጀ። እስከዛሬ ለዘለቀው ዘር-ተኮር ግድያና እልቂት መሰረት የሆነው ይኸው ስርአት ሲሆን የሚነቀንቀው ሃይል ግን ሊገኝ አልቻለም።  

በ27 አመታት የህወሃት-ወያኔ አገዛዝ ፣ ስርአቱን በሰላማዊ መንገድ በመቃወማቸው ወይም በመተቸታቸው ብቻ በግልጽና በስውር የተገደሉት ፣ በድብደባ አካለ ስንኩል የተደረጉት እና በአስከፊ እስራት መከራቸውን የበሉት ወገኖች የትየለሌ ናቸው። ግን ማን በቁጥር ይዞት? ማንስ ግድ ብሎት? 

የኢትዮጵያ ህዝብ ስጋትና ፍርሃት በወለደው ቀቢጸ-ተስፋ የሚኖር ህዝብ ነው። ተስፋውን ወደ እምነት ፣ እምነቱን ወደ እውነት መለወጥ የሚያስችል ጠንካራ ድርጅታዊ ውክልና የለውም። አብዛኛው ፖለቲከኛ በጎጥ ተደራጅቶ የግል ጥቅምና ስልጣን የሚያባርር ነው። የተረፈው በትርኪ ምርኪ ጉዳይ ተለያይቶ ፣ የከፋፋይ ገዢዎች መጫወቻ ከመሆን አልፎ ለህዝብ ከለላ የሚሆን ድርጅታዊ አቅም ሊመሰርት አልቻለም። 

ስለዚህ የኢትዮጵያ ህዝብ ፍዳ ከህወሃት-ወያኔ አገዛዝ ጋር ሳያከትም ቀርቶ፣ ዛሬ ላይ ብሶበት ይገኛል። 

የብዙ ኦሮሞ እና አማራ ወጣቶች ህይወት ተገብሮበት የመጣን ለውጥ ተጠቅመው ስልጣን ላይ ቁጢጥ ያሉት የዛሬ መሪዎች በሃያ ሰባቱ የህወሃት-ወያኔ አገዛዝ አገልጋይ የነበሩ ብቻ ሳይሆን የጥቅም ፣ የስልጣን ፣ የመብት ጥሰትና የግፍ ወንጀል ተጋሪዎችም የነበሩ ናቸው:: 

የኢትዮጵያን ህዝብ “አጥፍተናል” ፣ “እንክሳለን” ብለው የወሰዱትን ስልጣን ፣ ቃል ኪዳናቸውን ለመፈጸም ቢሰሩበት ኖሮ ባልከፋ ነበር። እነሱ ግን እጃቸው ውስጥ ያስገቡትን ስልጣን ስለመቀራመት እንጂ ፣ ስለንጹሃን ዜጎች ስቃይ እና ሞት ግድ ሊላቸው አልቻለም።  

ሰለሆነም በ”ብልጽግና” ዘመን የሰው ሞት በቁጥሩም በአሰቃቂነቱም የህወሃት-ወያኔ ዘመኑን አስከነዳ። 

በደርግና በህወሃት-ወያኔ አገዛዝ ፣ ባብዛኛው የሚገደለው የፖለቲካ ተቀናቃኝ የተባለው ነበር። ባለፉት አምስት አመታት በኦሮሚያ ፣ በቤሻንጉል ግሙዝ እና መሰል ቦታዎች ህይወታቸው የታጨደው ፖለቲካ ምን እንደሆነ የማያውቁ ለፍቶ አዳሪዎች፣ ህጻናት ፣ ሴቶች እና አረጋውያን ናቸው። ወንጀላቸው ተፈጥሮአቸው ነው። <<ዘራቸው>> ነው። ባብዛኛው አማራ ሆነው መገኘታቸው ነው። ከቤታቸውና ከቀያቸው ውጡ ተብለው የሚፈናቀሉትና መንገድ ዳር ለጅብ የሚጣሉትም እንዲሁ። 

በመንግስት ሃይላት ጭምር ፣ በገዛ አገሩ መጻተኛ የተደረገ እንደኢትዮጵያ ህዝብ ያለ ሌላ ህዝብ የለም። 

ደርግና ወያኔ የፖለቲካ ተቀናቃኞችን መግደል የሚጠበቅ ነገር ተደርጎ እንዲታሰብ አድርገውት ነበር። የዛሬዎቹ መሪዎች የሰውን መገደል ባጠቃላይ ፣ እንደ ተራ ክስተት እንዲታይ ፣ ህዝብ ስለሞት እንዳይደነግጥ ፣ እንዳይጨነቅ ፣ እንዳይጠይቅም፣ እያደረጉት ነው። 

ለሰው ህይወት ግድ የሌለው መንግስት ህዝብን አያከብርም፤ ውሎ አድሮ አገርን ያጠፋል እንጂ ሊያለማ አይችልም። ሞትን ተላምዶ የሚኖር ማህበረሰብ የግፍ ተሸካሚ ይሆናል እንጂ በነጻነት መኖር አይችልም። 

የ127ኛው የአድዋ ድል በተከበረበት እለት ፣ መንግስት ታሪካዊዉን የህዝብ በአል መቀማቱ አንሶ ፣ ሁለት ወገኖች በፖሊስ እንደተገደሉ ተዘግቧል። አንድ ወጣት አስተማሪ እና አንድ አዛውንት። በደላቸው ወጣቱ “መንግስት ባልፈቀደው” የምንሊክ አደባባይ በአሉን ለማክበር መገኘቱ ፣ አዛውንቱ ባቅራቢያ ባለው የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ መገኘታቸው ነበር። ይህ አይነት የመንግስት እብሪት ሌላ አገር ቢሆን ኖሮ የተፈጸመው ህዝብ በታላቅ ተቃውሞ ይወጣ ነበር። የአ.አ. ህዝብ ግን አንገቱን ደፍቶ ወደቤቱ ተመለሰ። 

ከህወሃት-ወያኔ ጋር በተደረገው ጦርነት በአንዳንዶች ግምት በሚሊየን ቢያንስ ግን በመቶ ሺህዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ህይወታቸውን እንዳጡ ይገመታል። የወደመውን ንብረትና የደረሰውን መፈናቀል ማንሳት አያስፈልግም። 

ይሁንና ህዝብ ስለሞቱት አያነሳም ፤ ለምንና እንዴት ሞቱ ብሎ አይጠይቅም። መሪዎቹም ለደረሰው እልቂጥና ጥፋት ቅንጣት ያህል ሃላፊነት አልወሰዱም። 

እንዲያውም “ብልጽግና” ጄኔራሎቹን በሹመትና በማእረግ አምበሸበሸ ፤ መቀሌ ድረስ ሄዶ የጥፋት አጋፋሪዎቹን አቅፎ ሳመ። ከሞት የተረፉት የህወሃት-ወያኔ መሪዎች ትግራይ ውስጥ ዳግም ስልጣን ለመያዝ ሽር ጉድ እያሉ ነው።

እንደልማዱ ልጆቹን ገብሮ ባዶ እጁን የቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው። እንደዚህ አይነት ንቀትና ውርደት የሚሸከም ህዝብ ቢኖርም እሱ ብቻ ነው!!  

ሞትን ከነምላሹ በጸጋ እየተቀበለ የሚታደም ህዝብ የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ነው!!! 

መቼ ሞት በቃኝ ብሎ እንደሚነሳ እግዜሩስ ያውቅ ይሆን?

__

በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena 
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

በዐብይ አህመድና ሽመልስ አብዲሳ መሪነት እየተስፋፋ የመጣውን የፅንፈኛ ኦሮሙማ የጥፋት ዘመቻ በተመለከተ ከቪዥን ኢትዮጵያ የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ

0
Vision Ethiopia _ abiy - shimeles

ከቪዥን ኢትዮጵያ ሥራ አስኪያጅ ኮሚቴ

የዘረኛው የወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ በሕዝብ ትግል ተገርስሶ ከወደቀበት ጊዜ ጀምሮ በዐብይ አህመድና ሽመልስ አብዲሳ መሪነት በአማራው ላይ ሲካሄድ የቆየው የኦሮሙማ የዘር ማጥፋት ዘመቻ ዛሬ ወደ ሌሎች ክፍሎች ተስፋፍቶ፣ የጉራጌ፣ የሲዳማ፣ የወላይታ፣ የቤኒሻንጉል፣ የሱማሌ፣ የጋምቤላና ሌሎች ወገኖቻችንም በአሰቃቂ ሁኔታ እየተጠቁ፣ ንብረታቸው እየተዘረፈና ሰላማዊ ነዋሪዎች እየተጨፈጨፉ ይገኛሉ::

በዘር ማጥፋት፣ በታሪክ ክለሳ፣ በባህል ምረዛ፣ በሃይማኖት ብረዛ፣ በሃብት ዝርፊያና በእርስት ቅሚያ ላይ የተመርኮዘው፣ የኦሮሙማ ኋላ ቀርና ስግብግብ ስርአት፣ አገሪቱን እያናወጠ ይገኛል::

በቅርቡ በእስልምና ሃይማኖት ተከታዮችና በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ ላይ የተነጣጠረ የከፋፍሎ ማዳከምና የማፈራረስ ዘመቻ አካሂዶ አገሪቱን እንደ ድርና ማግ ያስተሳሰሯትን እሴቶች በተቀነባበረ ስልት እየበጣጠሰ ይታያል።

በይበልጥም፣ በአረሜኔያዊ ድንቁርናው ታውሮ፡ ከኢትዮጵያ አልፎ ለመላው ጭቁን ሕዝብ መመኪያ በሆኑ ቅርሶችና የምርምር መሰረቶች ላይ ከመጠን ያለፈ ጉዳት አድርሷል::

የመላው ሕዝብ መግባቢያ ቋንቋ የሆነውንና የፅሁፍና የምርምር መሣሪያነቱ በዓለም አቀፍ መድረኮች ላይ ተደናቂነት ያስመዘገቡትን የአማርኛ ልሳንና የግእዝ ፊደልን አግዶና በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍል በትምህርት ደረጃ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ አድርጓል::

የጥቁር ሕዝብ ነፃነት መንፀባረቂያና መመኪያ የሆነውን የአድዋ ድል በአል በአግባቡ እንዳይከበር በተደጋጋሚ አስተጓጎሎአል፣ ይባስ ብሎም በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በአማኞችና የአድዋ በአል ኣክባሪዎች ላይ ፋሽሽታዊ እርምጃ በመውሰድ አስከፊ የታሪክ ጥቁር ነጥብ አስፍሮአል።

የአዲስ አበባ ከተማን አስተዳደር በኦርሙማ አክራሪ መሪዎች እጅ አስገብቶ፣ ብዙውን የከተማይቱን ክፍል ወደ ኦሮሚያ ክልል አስተላልፎአል። ከዚያም በላይ፣ ወደ መዲናይቱ መግቢያ የሆኑ የአካባቢ መንደሮችን “ሸገር” በሚል ስያሜ አደራጅቶ በመቆጣጠር ላይ ይገኛል። ወደ አዲስ አበባ በነፃነት የመግባትና የመውጣት እድልን ዘር እየመረጠ ያግዳል፤ በተለይም አማሮችን እየመረጠ ይከለክላል።  ከዚህም አልፎ፣ የኦሮሞ ያልሆኑ ዜጎች፡በተለይም የአማሮችን የመኖሪያ ቤቶች እያፈረስ ተከላካይ የሌላቸውን ወገኖቻችንን መጠጊያና መጠለያ አጥተው እንዲሰቃዩ አድርጓል::

በወለጋ፣ ሰሜን ሸዋና ተመሳሳይ ቦታ ነዋሪ የነበሩትን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የአማራ ተወላጆች ከቀያቸው አፈናቅሎ፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩትን ፈጅቶ ሲያበቃ፣ አሁን በጉራጌና በሌሎች ወገኖች ላይ ተመሳሳይ የሕግ አልባና የወንጀለኛ ድርጊቶችን እየፈፀመ ይገኛል::

ኢትዮጵያዊነቱን በጽኑ የሚያምነውን የደቡብ ክልል ለኦሮሙማ በላይነት በሚያመች መንገድ በማፈራረስና ከፋፍሎ እያዳከመ ይገኛል። የራሳቸውን ክልል የመመስረት ጥያቄ ያቀረቡትን እንደ ጉራጌና ወላይታ ላሉት ዜጎቻችን ለጥያቄቸው መልስ መስጠት ቀርቶ መብታቸውን ለማስከበር ሰላማዊ ሰልፍ እንኳን እንዳያደርጉና ድምጻቸዉን እንዳያሰሙ እየታፈኑ፤ ከሥራ እየተባረሩ የእስር፣ የድብደባና የእንግልት በደል እንዲደርስባቸው ሆነዋል።

በተለይም ሰሞኑን በወልቂጤና ሌሎች አካባቢዎች በሚኖረው የጉራጌ ሕዝብ ላይ እየደረሰ የሚታየው ከፍተኛ ዝርፊያ፣ ግድያና እስራት የዚህን አስተዳደር ኋላቀርና ጨካኝ አረመኔያዊ ገፅታ በጉልህ የሚያሳይ ማስረጃ ሆኖ ይቆጠራል። የዞኑን በጀት ለደቡብ ልዩ ኃይልና ለፌዴራሉ ኃይል አፈና ማስፈፀሚያ በማድረግ፣ ውሃ ፍለጋ ጀሪካን ይዞ የወጣው ሰላማዊ ሰው እስከመገደል ጥቃት ደርሶበታል። የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ የሕዝብ ምክር ቤት ተመራጮች፣ ነፍሰጡርና የቤት እመቤቶች ሳይቀሩ የህክምና እርዳታ እንዳያገኙ ተከልክለው፣ በእስር ቤት እንዲማቅቁ ተደርገዋል። 

ቀደም ሲል የአማራውን ሕዝብ ለማዳከም ባለው እኩይ አላማ፣ ክልሉን ለሕወሓትና ለሰሜን ሱዳን አጋልጦ እንዳስጠቃ ሁሉ፣ ዛሬ ደግሞ የጋምቤላን መሬት በደቡብ ሱዳን አስወርሮ፣ የወገናችን ኃብት እንዲዘረፍ፣ እርስቱ በውጭ ወራሪ ኃይል እንዲነጠቅና ሕዝቡም በባእድ ጦር እንዲሰቃይ አድርጓል::

“ሁሉም የእኔ” በሚል የነጣቂ መንፈስ የተለከፈው የኦሮሙማ ስርአት፣ ሰሞኑን ትኩረቱን ወደ ታላቁ የአባይ ግድብ (GERD) አዙሮ፣ ለዓመታት የዘር ማፅዳት ዘመቻ በአማራው ላይ ሲያካሄድበት በነበረው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ላይ የተስፋፊነት ጦሩን እያዘመተ ይታያል::

ቪዥን ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ እንዳስገነዘበው፣ በዐብይ አህመድና ሽመልስ አብዲሳ መሪነት ኢትዮጵያን እያፈራረሰ፣ ነዋሪወቿን እየጨፈጨፈና እየዘረፈ የሚገኘውን የኦሮሙማን ፋሽሽታዊ ስልቀጣ መግታት የሚቻለው በተቀነባበረና በተናበበ ሕዝባዊ ትግል ብቻ መሆኑን አጥብቆ ያምናል:: ስለሆነም ወገኖቻንን ከከፋ ችግርና እልቂት ለመታደግና አገራችንንም ከተደቀነባት አደገኛ ቀውስ ለማዳን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የትግል ስልቶች በመጠቀም ይህን ዘረኛ ስርዓት መታገል የግድ ይሆናል። ለዚህም የህልውና ትግል ጥሪ በድጋሚ ያቀርባል::

  1. በአገር ውስጥ የሚገኙ ተጠቂ ዜጎቻችን በሙሉ በሰላማዊ ሰልፍ፣ በሥራ ማቆም አድማ እና ሌሎችም የኦሮሙማን የጭቆና አገዛዝ በሚጎዱ ሰላማዊ መንገዶች ባለማቋረጥ ተቃውሟቸውንና እምቢተኝነታቸውን መግለፅ::
  2. በውጭ የሚኖሩ ፍትህ-ወዳድ ወገኖች፣ የኦሮሙማ የጭቆና አገዛዝ የገንዘብ ምንጭ የሆኑትን መንገዶች ሁሉ ማድረቅ:: በተለይም የአገዛዙን ጨካኝና አደገኛ ባህሪ ዓለም አቀፋዊ እውቅና እንዲያገኝ በማድረግ የውጭ እርዳታ ማእቀብ ማስደረግና እንደ ኢትዮጵያ አየር መንግድ ያሉትን የዘረኛው መንግሥት የገንዘብ ምንጮችን መጠቀሚያ አለማድረግ:: 
  3. በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ተቃዋሚ ኃይሎች የጋራ የትግል መርሀግብር በአስቸኳይ ነድፈው፣ በዲሞክራሲያዊ አሠራር ላይ የተመረኮዘ አንድነትን መፍጠር:: በተለይም የአማራው ክፍል በአንድነት ቆሞ፣ አሁን በመጠቃት ካሉት ወገኖቹ ጋር ኃይሉን በማቀናጀት፣ የራሱን ህልውናና የወገኖቹን ደህንነት ለመከላከል በቁርጠኝነት መነሳት::
  4. በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ ምሁራንና  የተለያዩ የሀይማኖት ተከታዮች፣ በኦሮሙማ እየተካሄደ የሚታየውን የታሪክ፣ የእምነትና የባህል ማጥፋት ዘመቻ በሚቻለው መድረክ ሁሉ አጥብቆ መዋጋት::
  5. በመጨረሻም፣ ዐብይ አህመድ፣ ሽመልስ አብዲሳና ጭፍሮቻቸው በተከታታይ የፈፀሙትን ፋሽሽታዊ ወንጀል ለፍርድ አቅርቦ፣ ወንጀለኞቹ ለተግባራቸው ተመጣጣኝ የሆነ ዓለማቀፋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ማድረግ::

ከላይ የተዘረዘሩትን የትግል ስልቶች ተግባራዊ ለማድረግ በቂ ኃይልና አስተማማኘ ነባራዊ ሁኔታ አለ ብሎ እያመነ፣ ቪዥን ኢትዮጵያ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ትጋትና አለመሰልቸት ከጭቁን ወገኖቹ ጋር በመሰለፍ፣ በዘር ላይ የተመረኮዘውን አረመኔያዊ አገዛዝ ለመታገል  ጠንክሮ እንደሚሠራ እንደገና ያረጋግጣል::

የተደቀነውን የሀገር ህልውና አደጋ በቅጡ እንረዳለን፤ ጊዜውን የዋጀ አመራር ለመስጠትም ቁርጠኛ ነን! (የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ )

0
Ethiopian News _ EZEMA

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ከምስረታው ጀምሮ እንደ ሀገር የደረስንበትን የፖለቲካ ስብራት በጥልቀት በመመርመር እና በመረዳት የሀገራችንን የፖለቲካ ቋጠሮዎች ደረጃ በደረጃ የሚፈቱበትን የመፍትሄ አማራጮች ማመላከት ላይ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ኢዜማ ሃገራችንን እየተፈታተኑ ያሉ የፖለቲካ ችግሮች እንዲባባሱ እና ሁላችንም እንዲሆን ወደ ማንፈልገው የከፋ ችግር እንዳንገባ ራሱን ከሃገር ህልውና በታች አድርጎ ሲንቀሳቀስ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም፡፡

የለውጡ መንግሥት ከመጣ በኋላ ያለፉትን አምስት ዓመታት ያሳለፍነው አንድ ወደፊት ሁለት ወደኋላ የሆነ ጉዞ በፅንፈኛ ብሔርተኝነት እየተገፋ ዛሬ ለደረስንበት ጠርዝ አብቅቶናል፤ እያለፍንበት ያለውን የፖለቲካ ዑደት በጥንቃቄ ላስተዋለና ቀልቡን ሰብስቦ ሁኔታዎችን ለተመለከተ የትኛውም አካል ዛሬ የገባንበትን ቅርቃር ማስተዋል ከባድ አይሆንም፡፡

በየቀኑ በሚፈጠሩ ውጥንቅጦች እና የሚፈለፈሉ አጀንዳዎች ማህበረሰባችንን የሥነልቦና ጫና ውስጥ እንደከተተውና ሁላችንም ውጥረት ውስጥ እንዳለን የሚያጠራጥር አይደለም፡፡ ዛሬ ላይ ህዝባችን የደረሰበት የመንፈስ ጭንቀት ከዛሬ ነገ ምን ይፈጠር ይሆን እያለ በከፍተኛ ስጋት ውስጥ በመውደቁ መሆኑን እንረዳለን፡፡ ኢዜማ የደረስንበት አሳፋሪ ሃገራዊ ዕውነታዎች ከሥር መሠረታቸው እንዲቀየሩ የመፍትሔ አካል መሆን እንዳለበትና ሀገራችን ወደ ቀና መንገድ እንድታመራ ከፊት ተሰልፎ አመራር መስጠት እንዳለበት እናምናለን፡፡

በተለይ በሰሜኑ የተከሰተው ጦርነት እንዲቋጭ የሰላም ስምምነት ከተፈረመ ማግስት ጀምሮ ሀገሪቷን የሚንጡ አጀንዳዎችን በመፈልፈል ዜጎችን እረፍት የሚነሱ ተግባራት ላይ የተጠመዱ በመንግሥት ውስጥና ከመንግሥት ውጪ ያሉ ፅንፈኛ ብሄርተኞች ተናበው እየሰሩ መሆኑን መረዳት አዳጋች አይደለም፡፡ በዘር ፖለቲካ የሰከሩ ሰዎችን በመጋለብ መላው ህብረተሰብ በቁጣ እንዲወጣና አጠቃላይ ሃገራዊ ቀውስ እንዲፈጠር ያለእረፍት እየሰሩ ይገኛል፡፡ ይህን ተከትሎም ሁላችንንም በስሜት ነድቶ የተዘጋጀልን ወጥመድ ውስጥ ገብተን አቅል የሳተ የእብደት መንገድ እንድንከተል ግፊት ለመፍጠር እየተሞከረ ያለውን ጫና በአትኩሮት ልንመለከተው ይገባል፤ መንግሥት በጉያው አቅፎ እዚህ ያደረሳቸው በሃሰት ትርክት የተሞሉ፣ በጥላቻ የሰከሩ ለተቀረው ኢትዮጵያዊ ቀርቶ እንወክለዋለን ለሚሉት ህዝብ እንኳን ግልጽና የጠራ መዳረሻ ያላስቀመጡ አክራሪ ኃይሎችን በግልጽ ሊፋለማቸውና፣ ከመዋቅሩ ሊመነጥራቸው ይገባል፡፡ ከመንግሥት መዋቅር ውጪ፣ በተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ መገናኛ ብዙኃን፣ አክቲቪስቶችና ባለሃብቶች ጭምር እየተቀጣጠለ ያለው የአክራሪ ብሄርተኝነት ጦስ ካሁን በኋላ እያስነከሰን እንዲቀጥል ሊፈቀድ አይገባም፡፡ መንግስትም ጉዳዩን መስመር ለማስያዝ እያሳየ ያለውን እንዝህላልነት ለፅንፈኛ ብሔርተኞቹ የልብ ልብ እየሰጠ ድርጊታቸው ሁሉ መስመር እያለፈ ህዝቡ አድዋን የመሰሉ ብሔራዊ በዓላትን እንኳ በሚፈልገው መንገድ ማክበር እንዳይችል አድርጎታል፡፡ በዚህም መታለፍ የሌለበት ቀይ መስመር ታልፏል፣ በቃ ልንል ይገባል!

ኢዜማ ከአባላቱ፣ ከደጋፊዎቹ እና ያገባኛል ብለው ከሚያስቡ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የሚደርስበት ትቸት ድርጅቱ ላይ ካለ እምነት እና ሊወጣ ይገባል ተብሎ ከሚታመነው የአመራር ኃላፊነት የሚመነጨ እንደሆነ ለአፍታም አይዘነጋውም፡፡ ድርጅታችን የሚይዛቸው የፖለቲካ አቋሞች እና ትንታኔዎች መሰረት የሚያደርጉት የሰከነ አስተሳሰብን እንጂ ጊዜያዊ ድጋፍን ለማግኘት በሚል የህዝብ ብሶትን እያቀጣጠለ፣ ወቅታዊ ጩኸትን እንዲሁም ወጀቡን ተከትሎ በመንጎድ ሲመሰረት ጀምሮ ካስቀመጠው የጠራ የትግል ሥልት እና ግብ ወደጎን የሚወጣ ድርጅት አይደለም፡፡

ድርጅታችን ኢዜማ በፍጥነት ተለዋዋጭ የሆነው የሃገራችንንም ሆነ የቀጠናውን ጂኦ ፖለቲካ በሀገራችን ላይ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ እየተነተነ፣ ሁኔታው የሚፈልገውን አቋምና ውሳኔ በመረጃ ላይ ተመስርቶ ውሳኔዎች እያስቀመጠ እና የትግል ስልቱንና የዓላማ መዳረሻውን እያጤነ የሚጓዝ ድርጅት ነው፡፡

በኢዜማ እምነት እንደሀገር የገባንበት ከፍተኛ አደጋ ከስሜታዊነት እና ከወገንተኝነት በፀዳ መልኩ፣ በወቅታዊ ክስተቶች ላይ ብቻ ተመስርተን ሳይሆን በዘላቂነት የሃገራችንን መፃዒ እድል እያሰቡ፣ ተከታታይነት ያላቸውን ማህበረሰቡን እረፍት የነሱ ክስተቶች በተናጠልና በድምርም በሃገራችን ላይ ጥለው የሚያልፉትን ጠባሳ እያሰቡ መንቀሳቀስ ያስፈልጋል፡፡

የብሔር፣ የሃይማኖት፣ የማንነት እና ሌሎች የልዩነት መሰረቶች ላይ ቆሞ በዘላቂነት የሃገራችንን ፖለቲካ ወደተረጋጋ ሥርዓት የሚያደርሰንን መፍትሄ ማግኘት የሚታሰብ አይደለም፡፡ መንግሥትም ሆነ በተቃውሞ ጎራ የተሰለፉ የልዩነት ፖለቲካ አራማጅ ኃይሎች በሚያሳድሩት ቅጥ አልባ መጓተት እና ፍጭት ዛሬ ሀገራችን የሰፈነው የሥጋት ድባብና አጠቃላይ የማኅበረ-ፖለቲካ ምስቅልቅል የመጨረሻው ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡

በመንግሥት (በገዢው ፓርቲ) ውስጥ በገሃድ የሚታይ የብሄርተኞች የእርስ በእርስ መጓተት፣ በተቃዋሚ ጎራ ያሉ ፅንፈኛ ኃይሎች አመፅ በመቀስቀስ ሃገሪቱን ወደከፋ ትርምስ ውስጥ እንድንትገባ የሚያደርጉ እንቅስቃሴዎችን ማስቆም አለመቻል የሚያስከትለውን መዘዝ ኢዜማ በትክክል ይረዳል፡፡ ለአባላት ለደጋፊዎች እና ለመላው ህዝብ ማሳወቅ የሚፈልገው ዋነኛው ቁም ነገር ሀገራችንን እየተፈታተኑ ያሉ ነባር ውስብስብ ችግሮችንም ሆነ አንገብጋቢ ወቅታዊ ሁኔታዎችን በጥንቃቄ እያየን እንጂ በዝምታ እና በቸልታ ኃላፊነት እንደሌለበት ፓርቲ ሁኔታዎቹን ዳር ላይ ቆመን እየተመለከትን እንዳልሆነ ነው፡፡ ሁኔታውን ተረድተን፣ ችግሩ እንዲቀረፍ የመሪነት ድርሻና ኃላፊነታችን መወጣት ታሪካዊ ግዴታና አደራ እንዳለብን ምንም አይነት ብዥታ የለንም፡፡

ኢትዮጵያዊነትን አስቀድማችሁ ሰለ ሀገር አንድነት በፅኑ የምትታገሉ የብሔር ፖለቲካ ምን ውስጥ አንደከተተን ተገንዝባችሁ በኢትዮጵያዊነት ከልብ የምታምኑ ሁሉ ከምንጊዜውም በላይ የሚከፋፍሉ አጀንዳዎችን እና ጥቃቅን ልዩነቶችን ከማጉላት በመቆጠብ አንድነትና ህብረት ላይ በማተኮር ከገባንበት አዘቅት ውስጥ መውጣት የሚያስችሉ የትብብር ስራዎች ላይ ማተኮር፤ ወቅታዊ የፓለቲካ ሁኔታውን ልብ ብሎ በማስተዋል በአንድነት ስም የተሰባሰበው ሀይል ቆም ብሎ ቀድሞ ሲጓዝበት ከነበረው አፍራሽ መንገድ በመውጣት እርስ በእርስ ከመጓተትና ከመጠላለፍ በመራቅ ፅንፈኛ ብሔርተኝነትን በጋራ መታገል እንደሚያስፈለግ አምኖ በሰከነ መንገድ ለመተባበር ካሁን በኋላ የምናባክነው ተጨማሪ ጊዜ መኖር እንደሌለበት በዜግነት ፖለቲካ ለሚያምኑ ሁሉ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

ኢዜማ ኢትዮጵያ ከገባችበት ችግር እንድትወጣ መፍትሄው እኩልነት ላይ የቆመ የፖለቲካ ሥርዓት መገንባት መሆኑን በጽኑ እንደማመኑ፣ ይህን የምትጋሩ በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን፣ እንደዚሁም ይህንን የምትጋሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ከጎናችን እንድትሰለፉ አደራ እንላለን፡፡ ከዚህ በፊት እንደሆነው በጎንዬሽ መጓተት ጊዜ የምናጠፋ ከሆነ አያት ቅድም-አያቶቻችን ዋጋ ከፍለው ያቆዩዋትን ሀገር ዓይናችን እያየ ብሄርተኞች ያፈርሷታል፡፡ እኛም ይህ እንዳይሆን ቢያንስ በሚያግባቡን መሰረታዊ የሀገር ህልውና ጉዳዬች ላይ አብሮ ለመስራት እና ኢትዮጵያችንን ለማዳን በጋራ በመቆም ህዝባችንን ለመምራት ባለመተባበር ከሃገር አፍራሽ ብሄርተኞች እኩል በታሪክ የምንጠየቅ መሆኑን ማስገንዘብ እንወዳለን፡፡

በገዢው ፓርቲ ውስጥ ያላችሁ የሀገርን አንድነት እና ሉዓላዊነት ከምንም ጉዳይ በላይ ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ ፅኑ እምነት ያላችሁ ሁሉ በድርጅታችሁ ውስጥ ያሉ መጓተቶች ሀገራችንን ውድ ዋጋ እንደሚያስከፍላት በመገንዘብ ታሪካዊ ሃላፊነት እንዳለባቸሁ ተረድታችሁ ከሀገራችሁ ጎን መቆማችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

ኢዜማ ሀገራችን ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ የተጋረጠባትን የህልውና አደጋ በሥፋት ለማጥናት፣ በተጨማሪም እንደሀገር እየሄድንበት ያለውን የፖለቲካ አካሄድ እና በተደጋጋሚ እየተከሰቱ ያሉ ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታን ቆም ብሎ በመገምገም ቀጣይ የትግል አቅጣጫዎቻችንን ማስመር እንዲቻል ብሔራዊ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው የጥናት ግብረ ኃይል እንዲቋቋም፣ ግኝቱንም በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

ግብረ ኃይሉ የሃገራችንን የአምስት ዓመት ጉዞ በስፋትና በጥልቀት በመፈተሽ እንደዚሁም ኢዜማ ከተመሰረተ ጊዜ ጀምሮ ያለፈበትን አራት የትግል ዓመታት እንደሀገር አሁን ከደረስንበትና ከተደቀኑብን አደጋዎች አንፃር ሊሆኑ የሚችሉ ክስተቶችን በሰከነ መንፈስ ተንትኖ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን በማሳየት የትግል መስመሩን ያመላክታል፤ ይህንንም ለሁሉም ባለድርሻዎች የምናቀርብ ይሆናል፡፡

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ብሔራዊ የሥራ አሥፈፃሚ ኮሚቴ

_
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ : ኦነግ ኦነግ የሚሸተዉ ብልጽግና ሊጸዳ ይገባዋል።

Ethiopia _ news _

ይበቃል ያረጋል ረታ

መጋቢት 2 ቀን 2ሺ15 ዓ.ም.

ከአምስት ዓመት በፊት በጉጉት እና ተስፋ ታጅቦ የተጀመረዉ ለዉጥ፣ ከብዙ ዉጣ ዉረድ በኋላ፣ ይዘቱ እና አካሄዱ የበለጠ ግልጥ እየሆነ መጥቷል። በሂደቱም የተረዳነዉ፤ ከዘር ፖለቲካ ስሌት ሳይላቀቅ በጠቅላይ ሚንስትሩ ተወጥኖ የሚቀነቀነዉ መደመር የሚለዉ ጽንሰ ሃሳብ፣ በተጓዳኝ መቀነስን አዝሎ በመምጣቱ የተጠበቀዉን ያህል ዉጤት አላመጣም። ከዚህም የተነሳ፣ በመደመር ላይ የተመሰረተዉ የብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ራዕይ ተግባራዊነቱ ጥያቄ ላይ እንዲወድቅ ሆኗል። ስለዚህም፤ የገዢዉ ፓርቲ አካል በሆኑት፣ በተለይም በኦሮሞ እና በአማራ ብልጽግና ፓርቲዎች መካከል ከጊዜ ወደ ጊዜ በግልጽ እየታየ የመጣ ከረር ያለ ቅራኔን ፈጥሯል። በሁለቱም ወገኖች እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች እና እየተስጡ ያሉ መግለጫዎች እንደሚያመለክቱት፣ ክስተቱ ሀገሪቱን ወደ ከፋ ደረጃ ሊወስዳት ይችል ይሆናል የሚል ስጋትን ፈጥሯል። 

የዚህ ስጋት፣ መንሰዔዉን እና ምንነቱን ለመረዳት፣ ሁለቱ ፓርቲዎች ከሁለት ሳምንት በፊት ገደማ በማከታተል ያወጧቸዉን ተጻራሪ መግለጫዎች ማየት እና ማጤን በቂ ግንዛቤ ይስጠናል። የሁለቱም መግለጫዎች ዋና ፍሬ ሃሳብ እና ማጠንጠኛ የፖለቲካ አቋም በጥቅሉ የሚከተሉት ሁለት የፖለቲካ ህሳቤዎች ናቸዉ፣

  • የገዢዉን ፓርቲ በበላይነት እየመራ ባለዉ በኦሮሞ ብልጽግና የሚቀነቀነዉ፣ ኦሮሟዊ ስነልቦና ያላት አዲስ ኢትዮጵያን ለመፍጠር እና ለመስራት የሚደረገዉ ጥረት እና ምኞት አንደኛዉ ሲሆን።
  • በተቃራኒዉ ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ከብዙ ዘመናት በፊት የተሰራች፤ የነበረች እና ያለች ሆኖም ግን፤ መስተካከል የሚያስፈልጉ ጉዳዮችን አስተካክሎ፣ የጎደላትም ካለ አሟልቶ እንድትቀጥል የሚመኘዉ የአማራ ብልጽግና ፓርቲ አቋም ነው።

ከዚህ በመነሳት የዚህ ጽሑፍ ዋነኛ አላማ፣ ከላይ የሰፈሩትን ሁለት ተጻራሪ የፖለቲካ አቋሞች መነሻቸዉ፣ መዳረሻቸዉ ብሎም በኢትዮጵያ ላይ ሊያስከትሉ የሚችሉትን አሉታዊም ሆነ አዎንታዊ ተጽዕኖዎች ለመዳሰስ ይሞክራል። በተጨማሪም፣ ለተከስቱት ችግሮች መፍትሄ ቢሆን ይረዳል የምንለዉንም ምክረ ሃሳብ ለማቅረብ ነዉ።

የችግሩ መነሻ፤

እንደሚታወቀዉ ይህ የዛሬ አምስት ዓመት የተጀመረዉ ለዉጥ፣ እዉን እንዲሆን ከፍተኛዉን ሚና የተጫወተዉ “ኦሮማራ” በመባል የሚታወቀዉ በቀድሞዉ የኢህአዴግ አባል በነበሩት በኦህዴድ እና በብአዴን አባላት ስዉር ጥምረት የተካሄደዉ ትግል ነዉ። ይህ ስዉር ጥምረት አላማዉን አሳክቶ እራሱን በአደባባይ አዉጥቶ ለሥልጣን ከበቃ በኋላ የተከተለዉ የፖለቲካ ሂደት ዛሬ ለተፈጠረዉ ቅራኔ ዋነኛ መንስኤ ነዉ። ይህ የኦሮማራ የጋራ ጥምረት ካስገኛቸዉ ድሎች በዋነኛነት ሊጠቀስ የሚገባዉ ከኦህዴድ ፓርቲ፣ ዶ/ር ዐብይን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አድርጎ ማሾሙ ነበር። ይህ ሹመት፣ በወቅቱ በአብዛኛዉ ኢትዮጵያዊ ከፍተኛ ተቀባይነትን ያገኘ፤ ሀገሪቱንም ለከፍተኛ ዉድቀት እና አንድነቷን ስጋት ላይ የጣለዉ በዘር ላይ የተመሰረተዉን አስከፊ የፖለቲካ ስሪት ማክተሚያ የመጀመርያዉ ምዕራፍም ተደርጎ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበት ነበር። 

ሆኖም ግን ብዙም ሳይቆይ፣ ኦሮማራ የሚለው ጥምረት ወደ ቅራኔያዊ ዉጥረት እየተለወጠ በመምጣቱ፤ የጥምረቱ መነሻ ዋነኛ ምክንያት ነዉ ተብሎ በብዙዎች ዘንድ ይታመን የነበረዉ የአንድነት ምልክት ጥያቄ ላይ ወደቀ። ቀስ በቀስ፣ በሀገሪቱ ላይ  የሚታየዉ የሰላም እጦት፣ በስፋት እየተካሄደ የመጣዉ የዘር ተኮር ጥቃት፣ እንዲሁም በግልጽ የሚታየዉ የኦሮሞ ተርኝነት፣ የተፈጠረዉን ልዩነት አጉልቶ አሳይቷል። ዛሬ እራሱን ብልጽግና ብሎ ሀገሪቱን የሚመራዉ የገዢዉ ፓርቲ፣ ከኢሕአዴግነት ስሙን ቀይሮ መጠነኛ ጥገናዊ ለዉጥ በማድረግ በኦሮሞ ብልጽግና የበላይነት የሚዘወር መሆኑ፣ የኦሮማራ ጥምረት ሰለመክሸፉ ዋነኛ መገለጫ ነዉ።

ለዚህም በተቀዳሚነት ዋነኛ ምክንያት የሆነዉ፣ ሁለቱ የአማራ እና የኦሮሞ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተነሱበት የፖለቲካ አወቃቀር እና መሰረት በቅጡ ሳይመረመር እና ሳይታረቅ፣ ጊዜያዊ የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ከሚል አላማ ታስቦ የተኬደዉ ሂደት ዉጤት ነዉ። የኦሮሞ ፖለቲካ እንደ ሕወኃት በ 1960 ዎቹ በተሳሳተ ትርክት የተጀመረዉን የብሔር ፖለቲካ መሰረት አድርጎ፣ ሥልጣን ለመጨበጥ የተነሳ ሲሆን፣ ይሄዉም የኦሮሞን ብሔር ተጨቋኝ፣ የአማራን ብሔር ጨቋኝ፤ አድርጎ በመፈረጅ፣ ኦሮሞን ከኢትዮጵያ የመገንጠልን ፖለቲካዊ እቅድ ይዞ የተመሰረተ እንቅስቃሴ ነዉ። በአንጻሩ ደግሞ፣ የአማራ ፖለቲካ እንደሌሎቹ የብሔር ፖለቲካ ፓርቲዎች ቀደም ብሎ የተመሰረት አይደለም። እራሱን ከኢትዮጵያ ለይቶ በብሔር አጥር ያልከለለ፣ ሆኖም ግን በሀገሪቱ በተዘራዉ የሐሰት ትርክት የተነሳ በአማራዉ ላይ የሚደርሰዉን ዘር ተኮር ጭፍጨፋ እና ፍረጃ ለመቃወም በሚል በ ፕ/ሮ  አስራት ወልደየስ መሪነት ለመጀመሪያ ጊዜ የመላዉ አማራ ሕዝብ ድርጅት በሚል ስያሜ በዘመነ ሕወኃት የተጀመረ ነዉ።

ሆኖም ግን ብዙም ሳይቆይ፣ አማራዉ በራሱ ተነሳሽነት የመሠረተዉ የአማራ ድርጅት፤ ሕወኃት በኢትዮጵያ ላይ ለማስፈን ላቀደዉ የዘር ፖለቲካ እንቅፋት አንደሚሆንበት ሰለተረዳ፤ በራሱ አምሳል ጠፍጥፎ የሰራቸዉ ኦህዴድ እና ብአዴን የሚባሉ፣ ከስማቸዉ በስተቀር የኦሮሞንም ሆነ የአማራን ሕዝብ የማይወክሉ ድርጅቶችን መስረተ። በተጓዳኝም፣ መንግስት ያለዉን የሃይል እና የገንዘብ አቅም በመጠቀም በተቀነባባረ የሀሰት ክስ ፕ/ር አስራትን በማሰር እና በማሰቃየት ለሞት ሲዳርግ፣ ፓርቲያቸዉም እንዲዳከም ቢደረግም፣ ፓርቲዉ ከብሔር ፓርቲነት ወደ መላዉ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የሚባል ሀገራዊ ፓርቲነት ተቀይሯል። ሕወኃት ላለፉት ሠላሳ ዓመታት፣ በኦሮሞ እና በይበልጥም በአማራዉ ማሕበረሰብ ላይ ለፈጸመዉ ወንጀል እና ጥፋት በዋና መሳሪያነት የተጠቀመዉ    ብኦዴን እና ኦህዴድን ነዉ።

ከጊዜ ወደ ጊዜ ሁኔታዎች እየተቀየሩ በሁለቱም ድርጅቶች ዉስጥ እየታቀፉ በመጡ ወጣት አባላት፣ እንዲሁም በሕዝባቸዉ እና በአጠቃላይ በሀገሪቱ እየደረስ ያለዉን ጉዳት የተረዱ አንዳንድ ነባር አመራሮች፣ ዉስጥ ዉስጡን በመደራጀት ብሎም ከዉጭ ካሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በስዉር በመቀናጀት የዉስጥ እና የዉጭ ትግሉን አፋፋሙ። ይህ ትግል፣ እየጎለበተ መጥቶ፣ ኢሕአዴግን ከዉስጡ በመቦርቦር አዳክሞት ለውድቀቱ ዋነኛ ምክንያት በመሆን ለዉጡ እንዲመጣ አድርጓል። ለዉጡን ተከትሎ፣ የዶ/ር ዐብይ መንግስት በሀገርም ሆነ በዉጭ ላሉ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ባደረገዉ የስላም ጥሪ መሰረት የገቡት ፓርቲዎች ለኦሮማራ ጥምረት መዳከም እና ብሎም መፍረስ ቀላል የማይባል አስተዋጽኦ አድርገዋል። ለዚህም ከፍተኛዉን ድርሻ የሚወስዱት፣ የኦሮሞ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሲሆኑ፣ በተለይም ነባር የኦነግ መስራች አባላት በኦህዴድ ዉስጥ የነበራቸዉ ጉልህ ሚና እና ያሳድሩት የነበረዉ ተጽዕኖ አሁን ላለዉ የኦሮሞ ብልጽግና እርሾ ሆኖታል። በአንጻሩ ደግሞ፤ አማራዉን የሚወክል ቀደም ብሎ የተደራጀ የፖለቲካ ፓርቲ ባለመኖሩ፣ የቀድሞዉ ብአዴን የቀደመ ግብሩን ሳይተዉ ስሙን ብቻ ቀይሮ ለኦሮሞ ብልጽግና አጃቢ ስር ሚዜ ሆኖ መጣ። ይህ የተዛባ ውህደት ከጊዜ ወደ ጊዜ ቅርጹን እየቀየረ በመሄዱ፣ ይጠበቅ የነበረዉ ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ለዉጥ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ከሸፈ። 

የብልጽግና መዳረሻ፤

ለዉጡን ተከትሎ ኦህዴድ በኦሮሞ ብልጽግና ቢተካም፣ እንደ ኢህአዴግ ዘመን የህወኃት አጫፋሪ ሳይሆን እራሱ “የብልጽግናዉ ህወኃት” ሆኖ በመምጣቱ፣ የሀገሪቱን አጠቃላይ ፖለቲካ ለመቆጣጠር ችሏል። ይህን ታሪካዊ አጋጣሚ እና እድል በመጠቀም፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በበዓለ ሲመታቸዉ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የገቡትን ቃል እና የስጡትን ተስፋ ተግባራዊ እንደማድረግ፣ በእርሳቸዉ መሪነት፣ በኦሮሞ ብልጽግና አስፈጻሚነት የኦሮሞ ተረኝነት ሥጋ ለብሶ በየ አደባባዩ በገሀድ ይታይ ጀመር። ከላይ እንደገለጽነዉ የኦነግ መነሻ የፖለቲካ አቋም፣ ኦሮሞን ከኢትዮጵያ መገንጥል የሚል ቢሆንም፣ አመቺ ከሆነ እና

እድሉ እስከተገኘ ድረስ፣ በኦሮሞ ማንነት እና ስነ ልቦና የተቃኘች አዲስ ኢትዮጵያን መፍጠሩ የተሻለ አማራጭ ሆኖ ተወስዷል። የዚህም ማሳያዉ፣ የኢትዮጵያዊነት ስነ ልቦና መገላጫዎች ናቸዉ ተብለዉ የሚጠቀሱትን እንደ ሃይማኖት ተቋማት፣ ታሪክ፤ ቋንቋ፣ ሰንደቅ ዓላማ እና የመሳሰሉት ላይ በቀጥተኛ እና በተዘዋዋሪ መንገድ በመዝመት የማጥፋት እና የመተካት ስራዎች በግልጽ እየታዩ መጥተዋል። ይህንንም አስመልክቶ በአንድ ወቅት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በአንድ ስብሰባ ላይ ያደረጉት ንግግር ነዉ ተብሎ በተሰማ የድምጽ ቅጂ ላይ የተረኝነቱን አተገባበር በሚገባ ገልጸዉታል። 

እዚህ ላይ ሊስተዋል እና ሊጠቀስ የሚገባዉ ነገር ቢኖር፣ ከዛሬ 60 ዓመት በፊት በተማሪዎች ንቅናቄ የተጀመረዉ የለዉጥ እንቅስቃሴ የትግሉ ማጠንጠኛ በተሳሳተ ትርክት የተቀነቀነዉ የብሔር ጭቆናን መነሻ ያደረገ ነበር። ለዚህም እንታገለዋለን ለተባለዉ የ “ብሔር ጭቆና”፣ አማራ እና ትግሬ (የስሜን ኢትዮጵያ ክፍል ) ጨቋኝ፣ ደቡቡ ደግሞ ተጨቋኝ ተደርጎ ነበር በነ ዋለልኝ መኮንን ድርሰት የተፈረጀዉ። ሆኖም ግን፣ በተቀነባበረ የፖለቲካ ስልት፣ ትግሬ ከጨቋኝነት ማዕረግ ወደ ተጨቋኝ ብሔር ካምፕ ሲወርድ፣ አማራዉ ግን ወደ ብቸኛ ጨቋኝ ብሔር ከፍ ተደርጎ፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ መነሻዉም ሆነ መዳረሻዉም አማራ ለመሆን በቅቷል። ከዚህ የተነሳ እስከ አሁን ድረስ በሚያሳፍር እና በሚያሳዝን መልኩ፣ አማራዉ በማያዉቀዉ እና ባልሰራዉ ኃጢያአት መከራዉን ያያል። ይህን የጨቋኝ፣ ተጨቋኝ ትርክት እዋጋለሁ፣ ለብሔረስቦች እኩልነት እሞታለሁ ወዘተ… ሲሉ የነበሩ ፖለቲከኞች፣ በተለይም የኦሮሞ ፖለቲካ ፓርቲዎች እና ፖለቲከኞች፣ ዛሬ በአደባባይ የኦሮሞ የበላይነት በሀገሪቱ ላይ ገኖ ሲታይ ምነዉ ዝም አሉ? የሚለዉ ጥያቄ ተገቢ መልስ ያሻዋል። 

ዛሬ በገሀድ ለሚታየዉ የተረኝነት መገላጫዎች ከብዙ በጥቂቱ የሚከተሉት ናቸዉ። 

  1. የኢትዮጵያዊያን የጀግንነት፣ የአይበገሬነት እና የቆራጥነት ምሣሌ የሆነዉን የአንባሳ ምልክት፤ ሆን ብሎ ማንቋሸሽ እና በፒኮክ ምስል ለመተካት መሞከር። 
  2. ለብዙ ዘመናት የመላዉ ሀገሪቱ ሕዝቦች የእርስ በእርስ የመግባቢያ ቋንቋ ሆኖ ሲያገለግል የቆየዉን የአማርኛ ቋንቋ፣ በተጠና መልኩ ከሀገሪቱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ላይ ማዉጣት።
  3. የኦሮምኛን ቋንቋ ለማስፋፋት በሚል ሽፋን፣ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት መዝሙርን እና አርማ በአዲስ አበባ ከተማ ባሉ የሕዝብ ትምህርት ቤቶች ላይ በግድ ለመጫን የተደረገዉ ሙከራ።
  4. የአዲስ አበባ ከተማን ለማዳከም እና ብሎም ከተፈጥሯዊዉ የከተማ እድገት የተነሳ እንዳትሰፋ በማድረግ፣ ከቦ በማፈንና ዙሪያዋን ሸገር በሚል ስያሜ በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ሥር የሚተዳደር ከተማ በመመስረት ለመቆጣጠር መሞከር።
  5. የማያባራ የዘር ጭፍጨፋ የሚፈጸምበት እና መንግስት እራሱ አሸባሪ ሲል የፈረጀዉ ሸኔ፣ በጠራራ ፅሐይ የጦር አዉድማ ካደረጋት ከኦሮምያ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚመጡ ዜጎች፣ የዜግነት መብታቸዉ ተጠብቆላቸዉ መግባት ሳይከለከሉ፣ አንጻራዊ ሰላም ከሰፈነበት የአማራ ክልል የሚመጡ ዜግችን፣ ሰላም ማስከበር በሚል ከንቱ ምክንያት እንዳይገቡ መከልከል።
  6. በተለያዩ ክልሎች፣ በተለይም በኦሮምያ ክልል በመንግስት ሃይል በሚደገፉ አሸባሪዎች በሚጨፈጨፉ እና በሚፈናቀሉ ዜጎች ሆን ተብሎ የአማራን ክልል የስደተኞች ክልል በማድረግ፣ በክልሉ ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እንዲፈጠር፣ በሕዝብ ዘንድ ተቃዉሞ እንዲነሳ በማድረግ ክልሉን የማዳከም ሴራ። 
  7. በኢትዮጵያዊነትን ስነ ልቦና ለዘማናት ትዉልድን በማነጽ ታሪኩን፣ ባህሉን እና ሃይማኖቱን እንዲጠብቅ ያደረገችን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን፣ ከሀገራዊነቷ አዉርዶ፣ ክልላዊ በማድረግ የማዳከም ብሎም የማጥፋት ዘማቻ።
  8. አጼ ምንሊክን ከታላቁ አድዋ ለመነጠል እና ለማዋረድ የሚካሄደዉ ያላሰለሰ ዘመቻ።
  9. ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት የሚገኑበት የአደባባይ በዓላት ላይ ሕዝቡ አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን ስንደቅ ዓላማ ምስል ያለዉ ቀሚስ፣ ነጠላ፣ እንዲሁም የቀደሙ ነገሥታት ምስል ያለበት ማናቸዉ አልባሳት እንዳይለበሱ እና እንዳይሸጡ መከልከል።  
  10. ኢትዮጵያ የሚለዉን ስም ሲሰማ የሚያንዘፈዝፈዉ፣ አረንጓዴ ቢጫ ቀዩን ስንደቅ ዓላም ሲያይ የሚተናነቀዉ፣ አጼ ምንሊክ ሲነሱ የሚያስጓራዉ ነፍስ ካወቀ ጀምሮ እስክ እርጅና ዘመኑ ኢትዮጵያዊነቱን ሲጽየፍ የኖረ ኦነጋዊ፣ የህገሪቱ ስፖርት እና ባህል ሚኒስቴር ተደርጎ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲሾም ምን ለማስፈጸም እና ማሳካት እንደታሰበ ግልጽ ነዉ።
  11. እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት ተጨባጭ ሀቆች፣ ሀገሪቱ ወዴት እየሄደች እንደሆነ ለማሳየት ቀንጨብ ተደርገዉ የቀረቡ ቢሆንም፣ በሀገሪቱ ላይ እየመጣ ያለዉን ከፍተኛ አደጋም ቁልጭ አድርጎ ያሳያሉ። ሰለሆነም፣ ከችግሩ ግዝፈት የተነሳ ሊመጣ ያለዉን ሀገራዊ ቀዉስ ለማስቆም የሚከተለዉን ምክረ ሀሳብ እናቀርባለን።
  12. የመፍትሄ ምክረ ሐሳብ፤
  13. ከላይ በዚህ ጽሑፍ መግቢያ ላይ ለመግለጽ እንደሞከርነዉ፣  በአሁኑ ሰዓት በሁለት ጎራ ሆነዉ በሚፋለሙት የፖለቲካ ሃይሎች መካከል በሚደረገዉ ትንቅንቅ፣ የሀገሪቱ የወደፊት እጣ ፈንታ ምን እንደሚሆን ለማወቅ እና ለመረዳት አዳጋች እየሆነ መጥቷል። ሆኖም ግን፣ አሸንፎ የሚወጣዉ የፖለቲካ አስተሳሰብ የሀገሪቱን መጻኢ ዕድል ይወስናል። ከዚህ በመነሳት ባለፉት ጥቂት ዓመታት በገዢዉ ፓርቲ የሚቀነቀነዉ እና እየተተገበረ ያለዉ ኦነጋዊ አጀንዳ፣ ሀገሪቱን ወደማትወጣበት የእርስ በእርስ እልቂት ይከታታል። ይህን ችግር ከወዲሁ ትገንዝቦ፣ በብልጽግና ስር የተካተቱት የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ብልጽግና በፍጥነት አሰፈላጊዉን እርምት እንዲያደርግ መግፋት እና ማገዝ ይጠበቅባቸዋል። ይሄንንም ለማሳካት፣ ካለዉ የሕዝብ ብዛት እና ፖለቲካዊ መዋቅር አኳያ፣ የአማራ ብልጽግና ሃላፊነቱን በመዉስድ ሌሎች በብልፅግና ውስጥ ያሉ ፓርቲዎችን በማስተባበር ሀገራዊ ግዴታዉን ሊወጣ ይገባል።
  14. እንደሚታወቀዉ አሁን ባለዉ የፖለቲካ አሰላለፍ የገዢዉን ፓርቲ ሊገዳደር ቀርቶ በበቂ ቁመና ላይ ያለ የተቃዋሚ ፓርቲ ሰለመኖሩ አጠያያቂ ነዉ። ባለፈዉ ከተካሄደዉ ሀገራዊ ምርጫ በፊት በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ጎላ ያለ እንቅስቃሴ ያሳዩ የነበሩ እንደ ኢዜማ፣ አብን፣ ኦፌኮ፣ ባልደራስ፣ እናት፣ ኦነግ የሚባሉ ፓርቲዎች ነበሩ። ሆኖም ግን፣ አንዳዶቹ የምርጫዉን ሂደት ተቃዉመዉ ሳይሳተፉ ሲቀሩ፣ የተሳተፉት ደግሞ ከምርጫዉ በኃላ ሁሉም በሚባል ደረጃ ከተጠበቀዉ በታች ባገኙት አነስተኛ ዉጤት የበለጠ የተዳከሙ ይመስላል። ይህም ብቻ ሳይሆን፣ በደጋፊዎቻቸዉ ብዙ ተስፋ ተጥሎባቸዉ የነበሩት የኢዜማ እና የአብን ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ የገዢዉ ፓርቲ በወሰደዉ በማር የተለወስ መሰሪ የፖለቲካ ሂደት፣ የተቸራቸዉን የመንግስት ሥልጣን በመቀበላቸዉ፣ የፓርቲያቸዉን ህልዉና አደጋ ላይ እስከ መጣል ደርሰዋል። በተቃራኒዉ፣ ይህ የመንግስት ችሮታ፣ በተወሰነ መልኩ በሕዝብ ዘንድ አድናቆትን እና ሙገሳን አትርፎለታል።
  15. ይህም በመሆኑ፣ ብልጽግና እየተገበረ ካለዉ የኦነግ አጀንዳ የተነሳ፣ ሀገሪቱን ወደከፋ ደረጃ ይዟት እየሄደ ካለበት የቁልቁለት ጎዳና ለጊዜዉም ቢሆን ታኮ ሆኖ ለማስቆም፣ በወቅቱ ካለዉ ተጨባጭ ሁኔታ አኳያ፣ ያለዉ ብቸኛ ሰላማዊ እማራጭ የአማራ ብልጽግና የጀመረዉን ተቃዉሞ ማበረታታት እና መደገፍ ነዉ። ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ያካተተች እና የተሻለች ኢትዮጵያን ለመገንባት፣ የአማራ ብልጽግና ታሪካዊ አጋጣሚ እና እድል አሁን ተፈጥሮለታል። ይህንን እድል በአግባቡ ለመጠቀም፣ የአማራ ብልጽግና ከመሽኮርመም እና ከዳተኝነት ፖለቲካ በፍጥነት ተላቆ መንቀሳቀስ ይኖርበታል። የታሰበዉንም የፖለቲካ ግብ ለመምታት፣ የተቀሩትን የብልጽግና አባላት እንዲሁም ከብልጽግና ዉስጥ እና ዉጭ ያሉ ከዘር ፖለቲካ የተላቀቁ የኦሮሞ እና የትግሬ ፖለቲከኞችን በዙርያዉ በማሰባሰብ ሀገራዊ አጀንዳ በመቅረጽ የበሰለ ፖለቲካ ሥራ መስራት ይጠበቅበታል። በተጨማሪም፣ ትግሉ ፍርያማ እንዲሆን የሕዝብ ድጋፍ በተለይም የሚወክለዉን የአማራ ህዝብ አቅፎ እንዲከተለዉ ማድረግ ተቀዳሚ ስራዉ ሊሆን ይገባል። ይህም እንዲሳካ፣ ሕዝቡ እስካሁን ካየዉ እና ካለፈበት የሕይወት ተሞክሮ የተነሳ፣ በፓርቲዉ ላይ ያለዉን ጥርጣሬ እና አለመተማመን ለመቅረፍ የሚከተሉትን ወሳኝ እርምጃዎችን ከወዲሁ መወሰድ አለበት ብለን እንመክራለን።
  16. ለእስር የተዳረጉ፣ ሆኖም ግን በቂ ምክንያት እና ተጨባጭ ማስረጃ ያልተገኘባቸዉን የፋኖ እና የተቃዋሚ ፓርቲ አባላትን በፍጥነት አጣርቶ እና ለይቶ ያለ ቅድመ ሁኔታ መፍታት።
  17. ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ ሲሉ ለነፍሳቸዉ ሳይሳሱ በችግሯ ጊዜ የተዋደቁላትን የአማራ ልዩ ሃይል፣ ሚሊሻዉን እና ፋኖን ለይስሙላ ሳይሆን ተገቢዉን እዉቅና፣ ክብር እና ድጋፍ መስጠት።
  18. በአማራ ሕዝብ ላይ ለደረሰዉ እና ለሚደርሰዉ ግፍ፣ ስቆቃ እና በደል ሲታገሉ በክልሉ እና በፌደራል መንግስት ጥርስ ተነክሶባቸዉ ከሀላፊነታቸዉ እንዲገለሉ የተደረጉ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ወደ ቀደም ቦታቸዉ መመለስ። 
  19. የክልሉ መንግስት ለሚወክለዉ ሕዝብ፣ ፓርቲዉ ሊያሳካዉ የሚፈልገዉን የፖለቲካ አቋም እና ከሕዝቡም ምን እንደሚጠብቅ እዉነተኛ እና ግልጽ የሆነ አቅጣጫ ማስቀመጥ። 
  20. በሕገ መንግስቱ እንደተደነገገዉ አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዋና ርእሰ ከተማ ከመሆኗም በላይ የፌደራል መንግስቱ መቀመጫ ስለሆነች፣ የአማራ ክልልም እንደማንኛዉም ክልል በከተማዋ ላይ መብት እንዳለዉ በግልጽ ማሳወቅ ይኖርበታል። በተጨማሪም፣ የኦሮሚያ ክልል አመራሮች ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ የሚመጡትን ኬላ ላይ በመመለስ እንዳይገቡ ማድረጉን በአስቸኳይ እንዲያቆም ማድረግ አለባቸዉ።
  21. ማንኛውም ኢትዮጲያዊ በአገሩ በነፃ የመንቀሳቅስ መብቱ እንዲከበር መታገል አለባቸው።  
  22. በሀገሪቱ ዉስጥ፣ በተለይም በኦሮሚያ ክልል እየተፈጸመ ያለዉን የአማራ እና የኦሮሞ ሕዝብ ጭፍጨፋ የኦሮሚያ ክልል እና የፌደራል መንግስት እንዲያስቆም ግልጽ የሆነ ጥርስ ያለዉ አቋም መያዝ አለባቸው።
  23. ወልቃይት እና ራያን በተመለከት የክልሉ መንግስት የአማራ ማንነታቸዉን በሚያረጋግጥ መልኩ የማያወላዉል አቋም መያዝ አለባቸው።
  24. ከሁሉም በላይ፣ የዘር ፖለቲካ ለሀገራችን ኢትዮጲያ እንደማይበጅና ሕገ መንግሥቱም ይህንን በሚያንፀባርቅ መንገድ መሻሻል አለበት ብለው እንደሚያምኑ ግልፅ አቋም መያዝ አለባቸው።
  25. ይህን ከላይ የተዘረዘሩትን የክልሉ መንግስት እና የአማራ ብልፅግና ፓርቲው ቢያከናዉኑ፣ በሀገሪቱ ላይ የተደቀነዉን አደጋ ለመግታት ብሎም ለመቀየር ይቻላል። ይህንንም በማድረግ ኦነግ ኦነግ የሚሸተዉ ብልጽግና ፓርቲ ሊፅዳና የሀገራችንም ኢትዮጵያ እጣ ፈንታ ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና የእውነተኛ የብልፅግና አቅጣጫ የያዘ ይሆናል ብለን እናምናለን።   
  26. በመጨረሻም እስካሁን በሀገሪቱ፣ በተለይም በአማራ ሕዝብ ላይ ለደረሰዉ ሰቆቃ እና እንግልት ከፍተኛዉን ድርሻ ከመንግስት ቀጥሎ የቀድሞዉ ብአዴን የዛሬዉ የአማራ ብልጽግና ቢሆንም፣ እያንዳንዱ ዜጋ በማወቅም ሆነ በቸልተኝነት አስተዋጽኦ አድርጓል። ይህንን ከግንዛቤ በመክተት፣ ለአድዋ ጦርነት አጼ ምንሊክ ካስለፈፉት የክተት አዋጅ ላይ “ … ቂምህን በጉያህ ይዘህ ተከተለኝ …” የምትለዋን ሐረግ ዛሬ በመተግበር ትግሉ ለሚጠይቀዉ መስዋትነት እያንዳንዱ ዜጋ መዘጋጀት ይኖርበታል ብለን እንመክራለን። 
  27. ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር። አሜን። 

__

በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena 
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

ወደ ሰላም ወይንስ ወደ ቀውስ (አንዳርጋቸው ጽጌ)

አንዳርጋቸው ጽጌ
አንዳርጋቸው ጽጌ

ወደ ወገኖቼ! ብዙዎቻችሁ ጽሁፍህ ባይረዝም ትሉኛላችሁ። እኔም ባይረዝም ፍላጎት አለኝ። ስንፍናዬ የሚመኘው ማሳጠሩን እንጂ ማርዘሙን አይደለም። ግን የማነሳቸው ጉዳዮች ሰፋ ተደርገው መቅረብ ስላለባቸው ብቻ ነው ጽሁፌን የሚያረዝሙት። በሃገሩ ጉዳይ መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ ነኝ የሚል የተማረ ሃይል፣፣ ሞልቶ ክተረፈው ጊዜው ጥቂት ደቂቃዎችን ሰውቶ ጽሁፍ ማንበብ ሊከብደው አይገባም ባይ ነኝ። ሰፋ አድርገን ነገሮችን ማየት ካልቻልን እንዴት መግባባት በመረጃና በምክንያት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ መወሰን እንችላለን። በዚህ መንፈስ ይህን ፌስ ቡክ በሁለት ክፍል እንድከፍል ያስገደደኝን ጽሁፍ በትእግስት እንድታነቡ በትህትና እጋብዛችኋለሁ።

ቀን – መጋቢት 5 2015 ዓ .ም.

ወደ ሰላም ወይም ወደ ቀውስ፤ የትግራይ ኢትዮጵያ ጉዳይ

ማሳሰቢያ፣ ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ የሚከተለው ምክንያት እንደሆነ እንዲታወቅልኝ እፈልጋለሁ። ኢትዮጵያ ማለቂያ በሌለው ቀውስ እየታመሰች ነው። ከእነዚህ ቀውሶች መሃከል አንዱ በወያኔ የተቀሰቅሰው የሰሜን ጦርነት ነው። ይህ ጦርነት ለጊዜው ቆሟል። ሆኖም ግን በደንብ በታሰበበትና በጥንቃቄ ሁኔታው ካልተያዘ ይህ ያልጠና ሰላም በቀላሉ መደፍረስ የሚችል፣ እስካሁን ህዝብ ከቀመሰው መከራ በላይ የከፋ መከራ ሊያመጣበት እንደሚችል፣ ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ቀጠናው የሚያናጋ መዘዝ ሊያስከትል እንደሚችል በጊዜ ለማመላከት ነው። ከዚህ በተጨማሪም ጽሁፉ እንደሚያመላክተው በትግራይ ውስጥ ድምጻችን እየተሰማ አይደልም የሚሉ ለሰላም የቆሙ አካላት ድምጽ ባስችኳይ እንዲሰማ የማድረግ ግፊት በመፈጠሩ ነው።  አሳሳቢ የሆኑ ሌሎች ጉዳዮች የሉም ወይ? አዎ አሉ። ሞልተው ተርፈዋል። አቅሜ በፈቀደ መጠን ወደ እነሱ እመለሳለሁ።

  1. እንደ መነሻ!

ትንሽ እውቀት፣ ትንሽ ተመክሮ ያለው ራሱን የፖለቲካ ሰው አድርጎ የሚቆጥር ዜጋ፣ በዘርና በሃገር ጥላቻ፣ በነዋይ ፍቅር፣ በግል ስምና ዝና ስካር፣ በስነልቦና ቀውስ፣ በስልጣን ሱስ፣ በፍራቻ ቆፈን፣ ስንፍና በወለደው ግድየለሽነት እና  በሌሎችም የማሰላሰል እና የመተንተን አቅምን በሚገሉ እንከኖች እስካልተሰለበ ድረስ የአንድን ሃገር እውነታ በፍጹም ነጻነትና ገለልተኛነት ለማጤን የወደፊቱንም ለመተንበይ የሚቸገር አይሆንም።

እንደ አጋጣሚ ሆኖ በተከታታይ ስልጣን ከያዙት የቅርብ ጊዜ ሁለት መንግስታት፣ የወያኔ እና የብልጽግና መንግስታት  ወይም የመንግስት አመራሮች ጋር በነበረኝ ግንኙነት ሊመጡ ይችላሉ ብዬ የማስባቸውን ችግሮችና የሃገሪቱ ፖለቲካ ወዴት ሊያመራ እንደሚችል የሚመስለኝን  ከመጠቆም ወደ ኋላ ብዬ አላውቅም። በዚህ ጽሁፍ የቀረቡ መረጃዎችና እይታዎች በስልጣን ላይ ላለው መንግስት እንግዳ ይሆናሉ የሚል እምነት የለኝም። አቅሜ፣ ልምዴ እውቀቴ በፈቀደ መጠን ያለምንም ይሉኝታ፣ ግብዝነትና አድርባይነት በድፍረት ሃሳቤን በቃል፣ በጽሁፍ አቅርቤያለሁ። ህዝብ በአደባባይ ከሚያውቀው ይበልጥ በግል የሰጠኋቸው አስተያየቶች ይበዛሉ።

በተለይ ወያኔ ስልጣን እንደያዘ፣ ከወያኔ ሰዎች ጋር በተለይ ትግራይን በተመለከተ ያደረግኋቸው ክርክሮች “ከፓፓሱ በላይ ቄሱ እስኪሉኝ ድረስ” ከየትኛውም የኢትዮጵያ አርሶ አደር ይበልጥ ለማውቀው የትግራይ አርሶ አደር ወገንተኛነቴን አሳይቻለሁ።

የወያኔ መሪዎች የትግራይ ህዝብ ከደርግ ጋር በተደረገው ትግል የከፈለውን ከፍተኛ መስዋእትነት ለግል ስልጣናቸውና ጥቅማቸው እንዴት እየመነዘሩ እያባከኑት እንደሆነ፣ እንዴት የእነሱ መጨረሻ የማያማር እንደሚሆን፣ የትግራይም ህዝብ የእነሱ እብሪት ብልግና እና ዘረፋ የመጨረሻው እዳ ከፋይ እንደሚሆን ያለማታከት አስጠንቅቄያለሁ። አክረው ሲገፉት የነበረው የዘር ፖለቲካ ህዝብን ለመከፋፈል ጊዜያዊ ጥቅም የሚያስገኝላቸው ካልሆነ በስተቀር “በቁጥሩ አነስተኛ ለሆነው፣ በመላው ሃገሪቱ ተበትኖ ለሚኖረውና ለሚሰራው በኢትዮጵያዊነቱ ቀናኢ ለነበረው የትግራይ ህዝብ አይጠቅመውም” በማለት ተሟግቻለሁ። የቋንቋን እና የባህልን እኩልነት፣ ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄን በዘር የተደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ክልሎች ሳያስፈልጉ ተግባራዊ ማድረግ የሚቻል መሆኑን፤ የዘር ፖለቲካው ሁሉንም ዘሮች እርስ በርሳቸው እንዲባሉ አድርጎ ሃገር አውድሞ እንደሚጠቃለል ለማሳየት ሞክሪያለሁ።  የቪዲዮ የድምጽና የሰነድ መረጃዎቹ በወያኔና በወቅቱ ኢህዴን ተብሎ በሚጠራው በኋላ ብአዴን በተባለው ድርጅቶችና በየሚድያ ተቋማቱ እጅ እንደሚኖሩ እርግጠኛ ነኝ።  ይህን ያደረግሁት ወያኔ እየወደቀ ባላበት የመጨረሻው ሰአት ላይ አይደለም። ወያኔ ስልጣን ከያዘ ሳምንታት ባልበለጠ ጊዜ ጀመሮ ነበር። ከወያኔና ከተላላኪዎቻቸው የኢህዴንና የኦህዴድ ሰዎች ጋር ያደረግሁት ጭቅጭቅ ከአንድ አመት በላይ ቀጥሎ በመጨረሻም ከወያኔ/ ኢህአዴግ ጋር ለመለያየትና በ1985 አ.ም ለሁለተኛ ዙር የስደት ህይወት መጀመር ምክንያት ሆኖኛል።

ዛሬ በህይወት ያሉ ከወያኔዎቹ ወገን፣ እነተወልደ ወልደማሪያም፣ አለምሰገድ ገብረአምላክ፣ ከብአዴኖቹ እነበረከት ሰምኦን፣ እነተፈራ ዋልዋ፣ እነአዲሱ ለገሰና ታምራት ላይኜ፣  በምን ጉዳይ ምን እንደተነጋገርን ያውቁታል። ዝርዝሩ ብዙ ነው።

በተለይ ተወልደ የኢህአዴግ የድርጅት ጉዳይ ሃላፊና የወያኔ የፖሊት ቢሮ አባል በመሆኑና በወቅቱ የድርጅት ጉድይ ትልቅ ተጽእኖ በሃገሪቱ ላይ የሚያደርግ ስለነበር፣ እኔም የዛ ኮሚቴ አባል በመሆን ካየኋቸው ችግሮች በመነሳት የዛሬ ሰላሳ አመት፣ በ1984 አ.ም፣ ቀኑን እና ሰአቱን ባልረሳሁት አንድ ማክሰኞ እለት ከጠዋቱ 4.30 ላይ፣ ቢሮው ቀጠሮ በመያዝ የኢህዴን እና የኦህዴድ ድርጅቶች ደካማ መሆን ወያኔን ራሱን ለከፍተኛ አደጋ የሚዳርገው መሆኑን በማንሳት ሰፊ ውይይት አድርጌያለሁ። የክርከሬ ጭብጥ “የእነዚህ ድርጅቶች ደካማነት በጊዜያዊንት ለእናንተ የሚያመች ሊሆን ይችላል። ሆኖም ግን ስታጠፉ ማረም አለመቻላቸው፣ ድርጅታችሁ በስህተት ላይ ስህተት እየሰራ ገደል እንዲገባ ያደርጋል” የሚል ነበር። የተወልደ መልስ “ድርጅቶች በሰው ሃይል ደካማ እንደሆኑ እናውቃለን፤ ግን ነጻ ድርጅቶች ስለሆኑ ብቃት ያላቸውን ሰዎች ወደ ድርጅታቸው እንዲያመጡ ህወሃት ማዘዝ አንችልም” የሚል ነበር። በወቅቱ ይህ መልስ እንደማያሳምነኝ ነግሬው ተለያይተናል።

ከወያኔዎች ጋር ወልቃይትና ራያንም በተመለከተ ብዙ ተባብለናል። በተለይ ገብሩ አስራት በ1995 አ.ም እንግሊዝ ሃገር በመጣበት ወቅት ወልቃይትና ራያን በተመለከተ ያደረግነውን ውይይት ይረሳዋል ብዬ አላስብም። የወልቃይትና የራያ ጉዳይ ከፍተኛ ደም አፋሳሽ እልቂት እንደሚያስከትል፣ በመጨረሻም ወያኔዎች ተሸናፊ እንደሚሆኑ ነበር ለማስረዳት የሞከርኩት።

ያ ወቅት ገብሩና ጥቂት ጓደኞቹ በመለስ ዜናዊ ትእዛዝ ከህወሃት አመራርነት የተባረሩበት ነበር። እቤቴ እራት ጋብዠው በጫወታችን መሃከል ለገብሩ አንድ ጥያቄ አነሳሁለት።

“ያን ሁሉ ዘመን በረሃ ለበረሃ ተንከራታችሁ ይሄው አሁን መለስ ከድርጅቱ አባረራቸሁ ድካማችሁ መና ቀረ። ምን አተረፋችሁ?” አልኩት።

ለዚህ አባባሌ ገብሩ እንዲህ ብሎ መለሰለኝ። “መና አልቀረንም አንቀጽ 39ን በህገ መንግስቱ እንዲካተት አድርገናል።” 

ይህ መልሱ በጣም ስላስገረመኝ። በተናገረው ላይ ሌላ ጥያቄ ጠየቅሁት። “ለመሆኑ ትግራይ በህገ መንግስቱ አንቀጽ 39 አማካይነት የመገንጠል መብት ብታገኝ የትኛውን ድንበር ይዛ ነው ነጻ ሃገር የምትሆነው?” በማለት፤

ገብሩም መለሰ፣ “የድንበር ጉዳይ ችግር አይደለም። ትግራይ በህገ መንግስቱ የጸደቀ ድንበር አላት” አለኝ

እኔም “ይህ ህገ መንግስታዊ የምትለው ድንበር በጉልበት ከወሎና ከጎንደር የጠቀለላችሁትን ወልቃይትና እና ራያን የሚያካትት ከሆነ ችግር ይፈጠራል” አልኩት።

“ምን ችግር” አለኝ።

ለማስረዳትም እንዲህ አልኩት፣

“በአንድ ሃገር ውስጥ የአስተዳደር ወሰን አድርጎ ክልል መመስረትና የአንድ ነጻ ሃገር ድንበር መመስረት ሁለቱ ይለያያሉ። ትግራይ ኢትዮጵያ አካል ስለሆነች የወልቃይትና የራያ ነገር እስከ አሁን የሚገባውን ትኩረት አላገኘ ይሆናል። ግን ወልቃይትን እና ራያን የነጻ ትግራይ ሪፓብሊክ አካል አድርጌ ድንበር አሰምራለሁ ብለህ ስትነሳ ችግር ይፈጠራል” አልኩት።

ምን ችግር ? አለኝ በድጋሚ

“ጦርነት” አልኩት

የበለጠ ለማስረዳትም የኤትራን ጉዳይ አነሳሁ። “ኤርትራ ቅኝ ገዥዎች ያሰመሩት ግልጽ የሆነ ድንበር ኖሯት በባድመ ሰበብ የደረሰውን እልቂትና ውድመት አስበው። እንዲህ አይነት ግልጽ የሆነ ነባር ድንበር የሌላቸውን ትናንትና ወያኔ ክልሎች አድርጎ የፈጠራቸውን አካላት አስተዳደራዊ ወሰኖች ወደ ቋሚና ነጻ ድንበርነት እቀይራለሁ ብለህ ስተነሳ፣ አጎራባችህ ያለውና ከዛም ውጭ ያለው ህዝብ ዝም ብሎ የሚያይህ ይመስልሃል? ሁሉም ለእያንዳንዷ ሳንቲሜትር መሬት መዋጋቱ አይቀርም። ይህ ለትግራይ ብቻ ሳይሆን ራሱን ነጻ ሃገር አደርጋለሁ ብሎ ለሚያስብ የትኛውም ትልቅ ሆነ ትንሽ ክልል የሚሰራ ነው። ኢትዮጵያ እንደ ሃገር ከቅኝ ገዥዎችና ከሌሎች ወረራዎች ራሷን ተከላክላ የተረፈችውና የቆየቸውም ከሁሉም አካባቢ ዜጎቿ በሁሉም የሃገሪቱ ምድር ደማቸውን አፍሰው አጥንታቸውን ከስክሰው ነው። እንደ ብሄር ወይም ህዝብ ብቻውን ራሱን ከውጭ ወራሪዎች ተከላክሎ ያተረፈ ህዝብና ግዛት ኢትዮጵያ ውስጥ የለም። ኢትዮጵያ ሃገሬ ናት የትም ቦታ ሰርቼ መኖር እችላለሁ በሚል እምነት የህዝቡን ቁጥር በማይመጥን መሬት ላይ የተቀመጠው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝብ አጎራባች የሆነውን ሰፊ መሬት የኔ ነው ብሎ ለሚነሳ ተገንጣይ በህገ መንግስቱ መሰረት ያሻህን አድርግ ብሎ የሚተወው ይመስልሃል። ትግራይም የሚገጥማት ችግር ይህ ነው” አልኩት።

ዝምታ ሰፈነ

ቀጥዬም ወያኔዎች በጦርነት እንዴት ራሳቸውን እንደሚያዩ ስለማውቅ፣

“ግጭት የሚነሳ ከሆነ የምትዋጉት በሁሉም መንገድ የውጊያ ታሪክ አቅምና ስነልቦና ካለው የአማራ ህዝብ ጋር ነው።” አልኩት።

የራት ግብዣው በዚህ ቆምጣጣ ውይይት  ተዘግቶ ገብሩን ወደሚሄድበት ሸኘሁት።

በግንቦት 7 ንቅናቄ የጸሃፊነት ሃላፊነቴ “የወያኔ ቅጣ ያጣ እብሪትና ዘረፋ ሌላው ህዝብ የትግራይን ህዝብ በበጎ እንዳይመለከተው ማድረጉ አይቀርም” የሚል ስጋት ስለነበረኝ፣ በግሌ የትግራይ ህዝብና  የትግራይ ገዥ ጉጅሌ የሚል ስያሜ የሰጠሁትን የጥቂቶች ስብስብ ያላቸውን ልዩነት በየመድረኩ ለማሰረዳት ሞክሪያለሁ። በተለይ ከወያኔ ጋር ትስስር ያልነበራቸው የትግራይ ምሁራን  የወያኔን የግፍና የዘረፋ ስርአት በመቃወም ከፊተኛው እረድፍ ላይ ለምን መገኘት እንዳለባቸው በተደጋጋሚ ማብራሪያ በመስጠት ጥሪ አቅርቤያለሁ። “ህዝብ ሁሉም ትግሬዎች ወያኔዎች አይደሉም” የሚል ጠንካራ አቋም እንዲኖረው ማድረግ የሚቻለው  “እናንተ የትግራይ ልጆች ወያኔን በመቃወም ትግሉን ስትመሩት ብቻ ነው። እኔ የትግራይ ሰው ያልሆንኩት ከምናገረው እናንተ ብትናገሩት የበለጠ ተደማጭነት ታገኛላችሁ” ብያለሁ። በጣት የሚቆጠሩ ትግራዋይ ይህን ያደረጉ ቢኖሩም የእነዚህ ጥቂቶች ተሳትፎ ብቻውን እየገጠመን ከነበረው ፈተና ጋር ሲነጻጸር እርባና አልነበረውም።

በኢትዮጵያ ወያኔን ከስልጣን ያስወገደው ለውጥ ከመጣና እኔም ከእስር ከተፈታሁ በኋላም ከተለያዩ የሚድያ ተቋማት ጋር ባደረግኋቸው ቃለ መጠይቆች ህዝብ በወያኔ መሪዎችና በትግራይ ህዝብ መሃከል ያለውን ልዩነት እንዲያውቅ ስራዬ ብዬ ስለትግራይ ህዝብ የማውቀውን የህዝቡን ስብእና እና ደግነት የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲገነዘብ ለማድረግ የቻልኩትን ጥረት አድርጌያለሁ። ለብቻዬ ከሰው ሁሉ ተገልዬ በታሰርኩበት ቦታ ጠባቂዎቼ ተመርጠው ሁሉም የትግራይ ተወላጆች የነበሩ ቢሆኑም ከነሱ መሃከል ከፍተኛ ስብእና የነበራቸው፣ ወያኔ ከሰጣቸው መመሪያ ወጭ ወጥተው ደግነትና ርህራሄ  ያሳዩኝን እንደ ለተማርያም ያሉትን ሰዎች በአደባባይ ህዝብ እንዲያውቃቸው ያደረግሁት “የዘር መጥፎ የለውም የግለሰብ እንጂ” የሚል መልእክት ለተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ለማስተላለፍ በመፈለጌ ነበር።

በአንድ ቃለ መጠይቅ በኢትዮጵያ ደም መፋሰስን፣ የበቀል አዙሪትን ለማስቆም፣ ጌታቸው አሰፋን ጋር ተቃቅፌ ሰላም ለመባባል እንደማይቸግረኝ የተናገርኩት ጌታቸው በወያኔ ዘመን ለተፈጸሙ አሰቃቂ የስብአዊ መብት ጥሰቶች  ዋናው ተጠያቂ እንደሆነ አጥቼው አልነበረም። ሌሎችም የወያኔ አመራሮች ከኢትዮጵያ ደሃ ህዝብ የዘረፉት አስደንጋጭ መጠን ያለው ሃብት ለሚሊዮን ህፃናት በአጭር መቀጨት፣ በመቶ ሽዎች ለሚቆጠሩ እናቶች በወሊድ እንክብካቤ እጥረት መሞት፣ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ወጣቶች ስራ አጥነትና ተስፋ መቁረጥ፣ በሃገር ውስጥ በዜጎች መሃል እንደሰደድ እሳት ለተስፋፋው ሌብነትን ነወር አድርጎ የማያይ ባህል ተጠያቂ እንደሆኑ ጠፍቶኝ አይደለም። በሃገሪቱ ሰላም ከወረደ መጪው ዘመን ብሩህ ይሆናል ከሚል ተስፋ ብቻ ነው።

ከዚህ በተጓዳኝም የወያኔዎች አስተሳሰብና አካሄድ በደንብ ስለሚገባኝ በወቅቱ መጥቶ የነበረውን ለውጥ ሁሉንም ህዝብ በእኩልነት በሚታደግበት መንገድ መስመር ለማስያዝ፣ በተለይ ወያኔዎች ለውጡን በስጋት እንዳያዩትና ወደሌላ አላስፈላጊ መንገድ እንዳይጓዙ ለጻድቃን (ጄ/ል) ሆነ ለአበበ ተክላይሃማኖት ግንቦት 7 ንቅናቄ ወደ ኢትዮጵያ ከመግባቱ በፊት ነበር በአካል ተገናኝተን እንምከር የሚል ጥያቄ እራሴ ስልካቸውን አፈላልጌ የደወልኩላቸው። የስልክ ጥሪዬን በጨዋነት ቢመልሱልኝም ከዛ በኋላ ለመገናኘት ያደረግሁት ጥረት ከንቱ ሆኖ ቀርቷል።

በማአከላዊ መንግስትና በወያኔ መሃከል ያለው ግንኙነት እየሻከረ፣ ቱባ የወያኔ መሪዎችና ሌሎችም የወያኔ ሁነኛ ሰዎች ትግራይ ላይ ሲሰባሰቡ ወዴት ሊያመሩ እንደሚችሉ ወያኔዎችን በደንብ ለሚያውቃቸው ለኔ አይነቱ ሰው ከባድ አልነበረም።

ቀደም ብሎ በትግሉ ወቅትና በኋላም ከወያኔዎች ጋር በሰራሁባቸው የተወሰኑ ወራቶች የተረዳሁት፣ ወያኔዎች በተከታታይ የገጠሟቸውን ባላንጣዎች በውጊያ ስላሸነፉ “ከኛ በላይ ጀግና ተዋጊ፣ የሚሊተሪ ሳይንስና ስትራተጂ አዋቂ የለም” የሚል ሰለራሳቸው እጅግ የተጋነነ ግምት እንዳለቸው አውቅ ነበር። ከዛም አልፎ ወታደራዊ ድሎቻቸው የመጡት በበሳልና ሳይናሳዊ በሆነ የፖለቲካ አመራር ነው ብለው ከልባቸው ያምኑ ነበር።

ከወያኔ ጋር በሰራሁበት አጭር ጊዜ ወስጥ  በተደጋጋሚ በሚደረጉ ግምገማዎች፣ “አሸናፊነትና ተሸናፊነትን የሚወስኑ በርካታ ጉዳዮች ስለሆኑ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ብቃታችሁን ከሚገባው በላይ አጋናችሁ አትዩ። ከደርግ ጋር በተደረገው ትግል የሻብያ እርዳታ፣ ከደርግ ጋር ሆድና ጀርባ የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ደርግ ራሱን ሶሺያሊስት ነኝ በማለቱ እንዲፈርስ የሚፈልጉ የአሜሪካ፣ የአውሮፓና የአረብና የጎረቤት አገራት ድጋፍ ለድላችሁ የነበራቸውን ሚና አትርሱ። ከዛም በተጨማሪ በአንድ ወቅት የሰራ ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስትራተጂ በሌላ ወቅት ላይሰራ ይችላል። እንዲያውም ስልጣን ከያዛችሁ በኋላ በሀገር ውስጥና በድርጅታችሁ ውስጥ  የሚታየው ቀውስ ጨብጠናዋል የምትሉት ሳይንሳዊ የፖለቲካ አመራር እንደምትሉት ያልተጨበጠ መሆኑን የሚያሳይ ስለሆነ ልተፈትሹት ይገባል” በሚል ተሟግቻቸዋለሁ። በአንድ ግምገማ ላይ  ይህን አባባሌን ከምር እንመልከተው የሚሉ ደጋፊዎችም አግኝቼ ነበር። ጌዜው ሁሉም በድል አድራጊነት የስከረበት ወቅት ስለነበር የትም ሳይደርስ ቀርቷል።

ባለፉት ሁለት ንኡስ ምእራፎች ከጠቀስኳቸው ምክንያቶች በመነሳት ነበር የወያኔዎች  ሰዎች አዲስ አበባን እየተው መቀሌ ላይ መሰባሰባቸው ያሳሰበኝ። በተለይ ስዩም መስፍን እና ስዬ አብረሃን የመሳሰሉ ጉምቱ የወያኔ መሪዎች ከመቀሌው ድምጸ ወያኔ የትግራይ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጓቸው ቃለ ምልልሶች የሰጧቸው አስተያየቶች የወያኔ ሰዎች አሁንም ከድሮ የአዋቂነትና የጀግንነት የበላይነት ቅዥታቸው እንዳልተላቀቁ በሚያሳዩ ቃላቶች የተሞሉ መሆናቸውና በትግራይ የጦርነት ድግስ እየተደገሰ መሆኑን ግልጽ ያደረጉ ነበሩ። እነዚህ ቃለ ምልልሶች ጦርነት ቢከፍቱ የውጭ መንግስታት የሚያግዟቸው እንደሆነ ቃል የተገባላቸው እንደሆነ የሚያሳዩ አነጋገሮች ነበሩባቸው። “ጦርነት ከተነሳ ቀጠናዊና አለምአቀፋዊ ሃይሎች የሚሳተፉበት ይሆናል የሚለው” የስዬ እና የስዩም አባባል ከጎናቸው ከሚቆሙ የውጭ ሃይሎች ጋር ስምምነት መድረሳቸውን ያሳይ ነበር። በዚህ ላይ የወታደራዊ ሰልፉ፣ የትጥቅ ማስጣቱ (ኤግዚብሽኑ)፣ የፉከራውና የቀረርቶው ጉዳይ ሲታከልበት ሁኔታው ወደ ጦርነት እንደሚያመራ ገሃድ ሆኖ ነበር።

በዚህም ወቅትም ቢሆን፣ ስዬ አብረሃ ከ28 አመት በፊት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ላይ በሰጠው ቃለ ምልልስ ላይ የተጠቀመባቸውን ቃላቶች ሳይቀይር “ጦርነት መስራት እንችልበታለን፣ ክፍለጦር አፍርሰን ክፍለጦር መገንባት ሜካናይዝድ አፍርሰን ሜካናይዝድ መገንባት እናውቅበታለን።” የሚል በእብሪት የተሞላ ንግግር በትግራይ ቴሌቪዥን ሲናገር በሰማሁብት ጊዜ ዝም ብዬ አላለፍኩም። የስዬና የጓደኞቹ የዛን ወቅት አነጋገርና አስተሳሰብ፣ የተቀየረውን የአለም፣ የቀጠናውን፣ የሃገርና የትግራይም ሁኔታ በደንብ ያላገናዘበ፣ የትግራይን ህዝብ ለከፋ ችግር ሊዳርግ የሚችል መሆኑን የሚገልጽ መልእክት እንዲደራሳቸው በአደባባይ የስዬን ስምና ንግግሩን ጠቅሼ መልእክቴን አስተላፌያለሁ። “ተው ይህ የጦርነት መንገድ አያዋጣም” ብያለሁ።

ለራሳቸው በሰጡት የተጋነነ የአይበገሬነትና የአዋቂነት ቅዥትና በውጭ ደጋፊዎቻቸው ቃል በተገባላቸው ድጋፍ ታውረው ወያኔዎች ጦርነት ከፈቱ። ለትግራይ ህዝብ ይህን ጦርነት ለምን እንደከፈቱ “የሰጡት ማብራሪያ የትግራይን ህዝብ ከጥፋት ለማዳን” የሚል ማጭበርበሪያ ብቻ ነው። በተሳሳተ የራስ ጥንካሬና የሌላው ደካማነት ትንተና እና በአሜሪካ የዴሞክራቲክ ፓርቲ ውስጥ ባሉ ከረጅም ዘመን ጀመረው በገንዘብ በገዟቸው ባልስልጣናት ሸሪኮቻቸው አበረታችነትና የአሜሪካ ጥቅም ለማስከበር የተከፈተ ጦርነት እንደሆነ ለትግራይ ህዝብ አልነገሩትም። የወያኔ መሪዎች አብይን ከአራት ኪሎ ቤተመንግስት በቀላሉ አሽቀንጥረው ከጃቸው ያመለጠውን ስልጣን በዚህ ስልጣን አማካይነት የተቀዳጁትን የመዝረፍ መብት መልሶ መያዝ ይቻላል በሚል የጀብደኝነት ስሌት የተጀመረ ጦርነት እንደሆነ ለትግራይ ህዝብ የነገረው የለም። ስልጣን ተይዞ ምን ሲሰራበት እንደነበር የሚያውቀው የትግራይ ህዝብ ይህን ሃቅ አውቆ ቢሆን ኖሮ ለሶስተኛ ዙር ልጆቹን የመስዋትነት ጭዳ በማድረግ የወያኔ መሪዎችን ህልውና  እና የኢትዮጵያን ጠላቶች ጥቅም ለማስከበር ሆ ብሎ አይነሳም ነበር። የትግራይ ህዝብ እንደርሱ በድህነት ተቆራምደው በሚኖሩ ደሃ የአማራ እና የአፋር ወንድሞቹንና እህቶቹ ላይ በአረመኔያዊ ጭካኔ አይዘምትም ነበር።  

አሁንም በዚህ ሰአት ይህ የወያኔዎች የጦርነት አጀማመር ትርክት ከአንድ ጉዳይ በስተቀር ብዙም  የተቀየረ ነገር የለውም።  በአደባባይ ጦርነቱን በመብረቃዊ ጥቃት ጀመርነው ብለው እንዳልተናገሩ፣ ዛሬ ወያኔዎች ጀማሪዎቹ እነሱ እንዳልሆኑ አድርገው እያቀረቡት ነው። “የትግራይን ህዝብ ከጥፋት ለማዳን” የሚለው የሃሰት ትርክት ግን ዛሬም በወያኔ አባላት መሃከል ብቻ ሳይሆን በመላው ትግራይ እንደታመነ እንዲቀጥል አድርገዋል።  ይህን ትርክት ለማስቀጠል እንዲቻል ወያኔዎች ከጦርነቱ በፊት ለአለም አቀፍ ማህበረሰቡ የዲፕሎማሲ ስራቸው ግብአት እንዲሆን የተዘጋጁበትን የጄኖሳይድ ትርክትና ሰበብ በማጠናከር፣ የጄኖሳይድ ኮሚሽን አቋቁመው በትግራይ ውስጥ ብቸኛው ስራ የሚሰራ፣ በቂ በጀት የተመደበለት የመንግስት ተቋም አድርገው ገንብተውታል።

ኮሚሽኑ ወያኔዎች ከመደቡለት በጀት በተጨማሪ፣ አለም አቀፍ የትግራይ ምሁራን ድርጅት በሚያሰባስበው ገንዘብና ራሱ የኢትዮጵያ መንግስት በሚያቀረበው ገንዘብና እርዳታ ተደግፎ የኢትዮጵያንና የኤርትራን መንግስት በአለም ፊት የሚያሳጣ፣ ምእራባውያኑ መውሰድ ለሚፈልጉት ጸረ ኢትዮጵያና ኤርትራ እርምጃ ሽፋን የሚሆን በሚገባ የታቀደና የተደራጀ፣ ወደፊት ወያኔ ለሚያደርገው የዲፕሎማሲ ዘመቻ የሚያገለግል የተቀነባበረ ሰነድ በማዘጋጀት ላይ ይገኛል።  

ኮሚሽኑ በየቤቱ ሰራተኞቹን እየላከ ለጄኖሳይድ ክስና ለካሳ ማሰባሰቢያ የሚሆን መረጃ እየሰብሰብኩ ነው በማለት የትግራይ ህዝብ ጄኖሳይድ ሊፈጸምብኝ ተሞክሮ ነበር በሚል እምነት ውስጥ እንዲኖር እያደረገው ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን “አሁንም የትግራይን ህዝብ ከወያኔ ውጭ ከጄኖሳይድ የሚያተርፈው የለም የሚል” ሰበካውን ቀጥሎበታል። አሁንም የወያኔ መሪዎች የሰላም ስምምነቱ በጦርነት አስገድደው ያገኙት ድል አድርገው ለትግራይ ህዝብ እያቀረቡለት ነው። ህዝቡ “የዚህ ድል ባለቤት ወያኔ ስለሆነ፤ ከህልውና ጥፋት የታደገህ ወያኔ ስለሆነ፤ እጣህን ከወያኔ ጋር አቆራኝተህ መቀጠል አለብህ” እየተባለ ነው።

ወያኔዎች ያሻቸውን ቢሉ ይህ አላስፈላጊ የነበረ ጦርነት በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ የሃገሪቱን የደሃ ልጆች ህይወት ቀጥፎ የዚችን ደሃ ሃገር ሃብትና ጥሪት አራቁቶ በነሱ ወታደራዊ ሽንፈት ለጊዜው ቆሟል። ከጦርነት ጋር በተያያዘ የሆነው ሁሉ ጸሃይ የሞቀው ጉዳይ ስለሆነ ብዙ ማተት አያስፈልግም። ከዚህ በላይ ያቀረብኩት መንደርደሪያ ከዚህ ቀጥሎ የሚመጣውን ዘመን በጥንቃቄ እንድንመለከት የእይታ ማእቀፍ ለመስጠት ብቻ ነው። የወያኔ መሪዎችን እና ከእነዚህ መሪዎች ጋር የተጣበቀውን የትግራይ ልሂቅ የአእምሮ ውቅር በሚገባ  ማወቅ፣ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እውነተኛ ሰላም ለኢትዮጵያ ህዝብ፣ የትግራይን ህዝብ ጨመሮ ከዛም አልፎ ለቀጠናው እንዲያመጣ ከተፈለገ በስርአት መሰራት ያለባቸውን ነገሮች ለመዘርዘር ያግዛል በሚል እምነት ነው።

ከዚህ ቀጥሎ አሁናዊ የትግራይ አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ ምን ይመስላል? ይህ ሁኔታ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ላይ ምን ተጽእኖ ያሳድራል፣ የሰላም ስምምነቱ አንኳር በሆኑት የስምምነት ነጥቦች ዙሪያ በምን ደረጃ ይገኛል? እውነተኛ ሰላም በትግራይ ሆነ በተቀረው ኢትዮጵያ ለማስፈን ምን መደረግ ይኖርበታል? የሚሉ የተለያዩ ጉዳዮችን በማንሳት መንግስት ሆነ የፖለቲካ ድርጅቶች ጉዳዩ በዋንኛነት ለሚመለከተው ህዝብ መስጠት የሚገባቸውን ነገር ግን እያደረጉት ያልሆነው ምልከታ ለማቅረብ እሞክራለሁ።

  • የወቅቱ የትግራይ የፖለቲካ ሁኔታ ከሰላም ስምምነቱ ጋር በተያያዘ፤

በትግራይ ውስጥ የሰላም ስምምነቱ ከመፈረሙ ከወራት በፊት ወያኔ የጀመረው ጦርነት በትግራይ ህዝብ ላይ ያሳደረውን እልቂትና ጥፋት የሚቃወሙ የተለያዩ በራሪ ወረቀቶች በከተማው ጎዳናዎችና በየቤተክርስቲያኑ ይበተኑ ነበር። (የሰንድ ማስረጃዎች አሉ)  ይህ የተቃውሞ እንቅስቃሴ በጥቂት ሰዎች የሚደረግ ቢሆንም በራሱ በወያኔ ውስጥ ያሉ ጦርነቱ እንዲቆም በሚፈልጉ የአመራር አካላት ጭምር የሚደገፍ ነበር።

ይህ እንቅስቃሴ ያሳሰባቸው የወያኔ አመራሮች “ከዚህ እንቅስቃሴ ጋር ግንኙነት አላቸው፣ የወያኔ መሪዎችን ለመግደል አሲረዋል፤ እንዲሁም መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ አስበዋል  ” በሚል በወዲ ሃጎስ የምትመራዋን በመቀሌ ዙሪያ ለጥበቃ የተመደበች ወደ አምስት መቶ የሰራዊት ብዛት የነበራትን አሉላ የተባለች ብርጌድ ላይ እርምጃ ወስደዋል። ወዲ ሃጎስ ለእስር ተዳረገ። በመፈንቅለ መንግስት ክስ ተከሶ ዛሬም እስር ቤት ነው ። የሰራዊቱ አባላት ትጥቅ አውርደው መቀሌ ቢዝነስ ኮሌጅ ውስጥ በተሃድሶ ስም በጥበቃ ላይ ነበሩ። ይህ ሁሉ ሲሆን እንዴት አታውቅም በሚል የመቀሌው የፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ተስፋዬ ከስራው ተነስቶ ለቁም እስር ተዳርጎ ነበር። ኮሚሽነር ኪሮስ የተባለው የጸጥታ ሃላፊም ተመሳሳይ እጣ ገጥሞት ነበር። የመቀሌው ከንቲባ ዶ/ር ገብረመድህን ከሃላፊነቱ በማንሳት ለእስር ተዳርጓል።  በወያኔ ውስጥ ጦርነቱን የሚቃወሙ የአመራር አካላት ቁጥራቸው እየተበራከተ በማእከላዊ ኮሚቴ ውስጥ አቅም እየፈጠሩ በመሄድ ላይ ነበሩ።

በዚህ ወቅት በጦር ሜዳ በኩል የሎጂስቲክ ችግር እያደገ፣ በሰራዊቱ ውስጥ የመንደርተኛነት ክፍፍል እየሰፋ፣ ወያኔ በገፍ በቅርቡ ያሰባሰባቸው ወጣቶችና ከእስር ፈትቶ ወታደር ያደረጋቸው ወንጀለኞችና የድርጅቱ የቆዩ አባላቶች ተጣጥመው መስራት እየተሳናቸው በሰራዊቱ ውስጥ ለጋራ አላማ መሰለፍ አዳጋች የሆነበት ሁኔታ በስፋት መስተዋል ጀመሮ ነበር። በርካታ የሰራዊት አባላት ሰራዊቱን እየከዱ ወደ ቤተሰቦቻቸው የሚመለሱበት ሁኔታ ተከስቶ ነበር። እነዚህን ተመላሾች ስራዬ ብሎ እያሳደደ የሚለቅም በኮማንድ ፖስት በኩል ሰፊ የተደራጀ ስራም ተጀምሮ ነበር። የሰራዊቱ መሪዎች የሙስና ድርጊት እየባሰበት፣ ሙስናው የሰራዊቱን ቀለብ ከመሸጥ አንስቶ እንዲሁም አብዛኞቹ ወታደራዊ መኮንኖች (እንደወዲ እምበይትይ የመሳሰሉ ጀነራሎች) ወደ ትግራይ የሚያስገቡ ኬላዎች እየዘጉ ከአፋር ፌዴራል ሃይሎች ጋር በመመሳጠር ከፍተኛ በሆነ የጨው ንግድ በመስማራታቸው በሰራዊቱ ውስጥ ትልቅ መከፋፈል ተፈጥሮ ነበር፡፡ ከአማራና ከአፋር ክልል የተዘረፈውን ሃብት የግል እስከማድረግ ድረስ የሚያካትት ነበር። ከዚህ ጋር ተያይዞ ራሱ ወያኔ፣ ኮነኔል ጉና (ገብሩ) የአዋሽ አርባ አዲስ ራእይ ማሰልጠኛ ሰራ አስኪያጅና በነበረው በሌሎችም ወታደራዊ አመራሮች ላይ የእስራት እርምጃ እስከመውሰድ ደርሶ ነበር።

በራሱ በወያኔ ማእከላዊ ኮሚቴ ውስጥ ትግራይ ለገባችበት አሰቃቂ ሁኔታ ተጠያቂዎች መሆን የሚገባቸውን ሰዎች ለይተው ሊጠየቁ ይገባል የሚል ድምጻቸውን ማሰማት የጀመሩ አባላት ብቅ ያሉበት ሁኔታ ተፈጠሮ ነበር። ወያኔ ይህን አስቸጋሪ ሁኔታ ጠጋግኖ “አልሞትኩም ብዬ አልዋሽም” ለማለት ነበር የሶስተኛ ዙር የወረራ ጥቃቱን በአማራና በአፋር ህዝብ ላይ የከፈተው። የሶስተኛው ዙር ወረራ አላማ ቀደም ብሎ እንደታሰበው አዲስ አበባ ለመግባትና የመንግስት ስልጣን ለመቆጣጠር ሳይሆን ከወያኔ መሪዎች አቅምና ቁጥጥር ውጭ እየወጣ የነበረን መጨረሻው የማያምረውን የወያኔን የውስጥ ድርጅታዊ እና የትግራይን  ፈተናዎች ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመደራደር ለመፍታት የሚያስችል የተወሰነ የመደራደሪያ አቅም ለመፍጠር የተደረገ ነበር። የትግራይ ህዝብና ወጣት የወያኔ አመራሮች ለጦርነቱና ለእልቂቱ የወያኔን ነባር መሪዎች ተጠያቂ እንዳያደርጋቸው ከመስጋት የተደረገ የማደናገሪያ ወረራ ነበር።  ወረራው ወያኔዎች እንዳሰቡት ሳይሆን የኢትዮጵያ ጦር ሰፊ የትግራይን ክልል ተቆጣጥሮ ጭራሽኑ ትግራይ ወስጥ ገበቶ መቀሌን በቅርብ ርቀት የሚያይበት ሁኔታ ተከሰተ።

ይህ ወታደራዊ ሽንፈት በአንድ በኩል ወያኔ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የፕሪቶሪያን ስምምነት እንዲቀበል ያደረገው ቢሆንም ከዚሁ ያልተናነሰ ጫና ያሳደረው በራሱ በወያኔ ውስጥ የተነሳው ነባር መሪዎቹን ሊበላ ወደሚችልበት ደረጃ እያደገ በመሄድ ላይ የነበረው የውስጥ ትግል መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል።

ወያኔዎች ከአሜሪካን መንግስት ባላስልጣናት ጋር በቅርበት እየተመካከሩ የሚሰሩ በመሆናቸው ወታደራዊ ሁኔታውን የተረዳው የአሜሪካ መንግስት የወያኔ መሪዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመደራደር ራሳቸውን ከጥፋት እንዲያድኑ ተጸእኖ ሳያደርግባቸው እንዳልቀረ መገመት ከባድ አይሆንም። የአሜሪካ ተጽእኖ በወያኔ ላይ ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ መንግስትም ላይ የተደረገ ለመሆኑ ፕሬዚደንት ኢሳያስ በጥር 2015 በሰጠው ቃለ ምልልስ ጥቆማ ሰጥቶናል። በሌላ መንገድም ይህ ተጽእኖ ቀላል እንዳልነበር መረዳት ተችሏል። ይህም ሃቅ እንዳለ ሆኖ የወያኔ የውስጥ ሽኩቻን ያሳደረውን ከፍተኛ ተጽእኖ አሳንሰን ማየት አይገባንም። 

የውስጥ ሽኩቻው ከሰላም ስምምነቱ በፊት በወያኔ ማእከላዊ ኮሚቴ ውስጥ በነባር አመራሮችና በወጣት አመራሮች መሃከል ይካሄድ ነበር። ሽኩቻው ወጣቶች በጎደሉ የስራ አስፈጻሚ አባላት ምትክ አዳዲስ አባላት እንሙላ ሲሉ፣ ነባሮቹ ወቅቱ አዲስ አባላት ለመሙላት አይፈቅድልንም የሚል ነበር። ወጣቶቹ አዲሶቹ አባላት ከወጣት መሪዎቹ ጎን ይቆማሉ ብለው ስለሚያስቡ ሃሳቡን ሲገፉ ነበር። ነባሮች ይህን ስላወቁ ሃሳቡን ሲቃወሙ ነበር። ሌላው የሽኩቻ ነጥብ በስልጣን የሚታየው ያልተቀየረው የአሻአ (የአክሱም ሽሬ እና አድዋ)  ሰዎች በፖለቲካውም፣ በአስተዳደርም በወታደራዊ መስኮች የነበራቸው የበላይነት አሁንም በከፋ መልኩ እየቀጠለ ከመሆኑ ጋር ተያያዞ የሚነሳ ነበር። በተደጋጋሚ በማእከላዊ ኮሚቴው ውስጥ ይህ ጉዳይ እየተነሳ ያወዛግብ እንደነበር ይታወቃል። ማወዛገቡ ብቻ ሳይሆን ሰዎች የመጡበትን አውራጃ እየጠቀሱ በታማኝነት በከሃዲነት የመፈረጅ ንትርክ ጭምር የተለመደ ሆኖ ነበር። 

ከሰላም ስምምነቱ በፊት በነበሩ ጥቂት ወራት በአጠቃላይ በወያኔ አመራር ካምፕ ውስጥ የነበረው ክፍፍል ለተፈጸመው ሁሉ በተጠያቂነት እንያዛለን የሚሉ ጥቂት አመራሮችና ሊጠየቁ ይገባል በሚሉ በርካታ አባላት መካከል እያደገ የመጣ ክፍፍል ነበር። እጣቸውን ከተጠያቂነት ጋር የሚያስተሳስሩ መሪዎች ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ራሳቸውን ለማዳን ሴራ በመሽረብ፣ እቅድ በማውጣት ነበር።

በዛን ወቅት የማእከላዊ ኮሚቴው ለሁለት እንደተከፈለ ሁሉ የሰራ አስፈጻሚውም ለሁለት ተከፈሎ ነበር። ጌታቸው ረዳ እና ደብረጽዮን በአንድ ወገን፣ ጌታቸው አሰፋና ፈትለወርቅ አለም ገብረዋህድ በሌላው ጎራ ቆመው ነበር። የጌታቸው ረዳ ነገር መቼም አስገራሚ ነው መባሉ አይቀርም።  በዚህ የውስጥ ሽኩቻ በትግራይ ውስጥ ከሚገኙ ከ35ቱ (ከ37ቱ ሁለቱ ውጭ ሃገር ናቸው) የወያኔ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት መሃል በየቀኑ አቋማቸው የሚለዋውጡ አስራ አራት አባላት ያሉት ሲሆን የተቀሩት በሁለት ጎራ ተከፍለው የእነዚህ የ14 ኮሚቴ አባላት ድጋፍ በማሰባሰብ የሚተናነቁባቸው ሁኔታዎች ውስጥ ነበሩ።

የውስጥ ሽኩቻው የደረሰበት ከፍተኛ ደረጃ  የሚያሳየው ሃቅ በጥር 2015 ውስጥ ተከስተ። የወያኔ ማእከላዊ ኮሚቴ እና ከእያንዳንዱ አርሚ ሶሶት ሶሶት ሰው የተወከለበት በደጀን የርእሰ መስተዳደሩ ቢሮ፣ ከጥር 7 እስከ ጥር 10 በተደረገው ስብሰባ ኮሚቴው በወሰነው ውሳኔ መሰረት ደብረጽዮን ገብረሚካኢኤል፣ ፈትለወርቅ  ገብረእግዚአብሄር፣ ጌታቸው አሰፋ፣ አለም ገብረዋህድና ጌታቸው ረዳ፣ ሁሉም የህወሃት የስራ አስፈጻሚው ኮሚቴ አባላት፣ በትግራይ ለሆነው ሁሉ  ተጠያቂዎች ናቸው በሚል ከስልጣናቸው ታግደው እንዲቆዩ እስከመወሰን እና  ይህ ውሳኔ በምክር ቤት እንዲጸድቅ ጥያቄ እሰከማቅረብ ደርሶ ነበር።

የሰላም ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ የጥቂት የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት የአቋም መገለባበጥ ከሚታይበት ሁኔታ በስተቀር በወያኔ ውስጥ በትግራይ ለውጥ እንዲመጣ በሚፈልጉ እና በማይፈልጉ፣ የሰላም ስምምነቱን በሚደግፉና በሚቃወሙ ሁለት ዋና ቡድኖች የማእከላዊ ኮሚቴው እንደተሰነጠቀ ነው።

አንዱ ቡድን የሞንጀሪኖ ቡድን በመባል የሚታወቀው ሲሆን የውናትና የባይቶና (በስም የተቃዋሚ ድርጅቶች ናቸው ነገር ሁኔታዎች ሲከፉ ከዚህ ቡድን ጋር የሚለጠፉ እንደሆነ ይታወቃል) ድጋፍ ሲኖረው፣ ከወታደራዊ ተቋሙም ጋር ከተወሰኑ አካላት ጋር ቁርኝት ያለው ቡድን ነው። የዚህ ቡድን አባላት ጌታቸው አሰፋ ራሷ ሞንጀሪኖ (ፈትለ ወርቅ ገ/እግዚአብሄር )አለም ገብረዋህድ፣  አልማዝ ገ/ጻድቅ የክልሉ የትራንስፖርት ሃላፊ፣ ገነት አረፈ የማህበራዊ ጉዳይ ሃላፊ፣ ሃጎስ ጎድፋይ ጤና ቢሮ ሃላፊ ( አሁን የፕሬዚደንቱ ጽ/ቤት ሃላፊ)፣ ፍስሃ ሃፍተፅዮን ፣ ሃዱሽ ዘነብ ፣ አማኑኤል አሰፋ ፣ ይትባረክ አምሃ የመቀሌው አዲሱ ከንቲባ፣ አርአያ ግርማይ፣ ዶ/ር አማኑኤል ሃይሌ፣ ሊያ ካሳ የደቡባዊ ምስራቅ ዞን አስተዳዳሪ፣  እነዚህ የሰላም ስምምነቱ በመቃወም በጋራ የቆሙ ሲሆን፤ በሌላ ወገን ከጌታቸው ረዳና ሌሎች ሰላሙን የሚደግፉ አባላት፣ ብርሃነ ገብረየሱስን፣ የአሁኑ የምእራብ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ ነጋ አሰፋ፣ የህብረት ስራ ማህበር የክልሉ ሃላፊ፣ ሰብለ ካህሳይ የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊ፣ በየነ ሙክሩ የፋይናንስ ሃላፊ፣ ሃብቱ ኪሮስ ቆይቶ የተቀላቀለ የደቡብ ዞን አስተዳዳሪ፣ ዶ/ር አትንኩት መዝገበ፣ ረዳኢ ሃለፎም የትግራይ ኮምኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ፣ ጌታቸው ረዳ፣ ለምለም ሃድጉ ባህልና ቱሪዝም ሃላፊ የሰላም ስምምነቱን በመደገፍ በወያኔ ማእከላዊ ኮሚቴ ውስጥ ተከራክረው ያሸነፉ ናቸው። አንዲሁም ከተለያዩ አርሚዎች የተወከሉ የጦር መሪዎች አብዛኞቹ  የሰላም ስምምነቱን በመደገፍ ከእነዚህ የለውጥ ሃይሎች ጋር በመሆን የቆሙ ነበሩ፡፡ በዚህ ስብሰባ ጌታቸው አስፋ አሞኛል በሚል ሰበብ ስብሰባውን አቋርጦ አስከመሄድ ደርሷል። በተጨማሪም ጄነራል ወዲ እምበይተይ በስብሰባው ሊገኝ አልቻለም ፡፡

ይህም ሆኖ የሰላም ስምምነቱን ያልተቀበለው ቡድን በጁ ባለው የገንዘብና አሰተዳደራዊ አቅም እና በሰራዊቱ አመራር ውስጥ ባለው ድጋፍ የተለያዩ እንቃስቃሴዎችን ማድረጉን አላቆመም። ይህን አቅም በመጠቀም ጥር 24 እና 25 /2015 ከመላው ትግራይ የቡድኑ ደጋፊዎች ናቸው የሚላቸውን እስከ 600 የሚደርሱ ወጣት ካድሬዎች መቀሌ በሃውልት ሰማእትታ አዳራሽ በማሰባሰብ፣ “ህወሃት ታሪካዊ ድርጅት ነው መፍረስ የለበትም፣ ይህን ታሪካዊ ድርጅት ለማፍረስ ከሚሰሩ ተንበርካኪዎች ጋር  መታገል አለብን” የሚል አጀንዳ መወያያ እንዲሆን አድርጓል። በዚሁ አጋጣሚ ተንበርካኪዎች በሚባሉ ግለሰቦች ላይ የግድያ፣ የግድያ ሙከራ መፈጸም መጀመሩን፣ ወደፊት ይህ የወንጀል ድርጊት እየጨመረ እንደሚመጣ መታወቅ አለበት። በዚህ ስብሰባ ላይ ሁሉም የማእከላዊ ክሚቴ አባላት ተገኝተው ነበር። አላማው ለውጥ ፈላጊ አመራሮችን ለማሸማቀቅ ከተቻለም ከዚህ በፊት በ1993 መለስ ዜናዊ ተቃዋሚዎቹን በካድሬዎች አማካይነት አዋክቦ ከድርጅቱ እንዲባረሩ ያደረገውን አሰራር ለመድገም ነበር። እንዲህም ሆኖ ስብሰባው ለወጥ በሚፈልገው ወገን አሸናፊነት ተጠናቋል።

ይህ መንገድ አላዋጣ ያለው ጸረ ሰላም ቡድን ከለውጡ በኋላም ስምምነቱን የማጨናገፍ በኢትዮጵያ ደረጃም ሃገር የማናጋት እቅዱን በስራ ለመተርጎም የራሱን እንቅስቃሴዎች ማድረጉን ቀጥሏል። ለስራ ገንዘብ ያስፈልገናል በሚል 350 ሚሊዮን ብር ለማሰባሰብ አቅድ አውጥቶ ይህን ገንዝብ የመቀሌን ከተማ መሬት በመቸብቸብ ገንዘቡን ማሰባሰብ ችሏል። የመቀሌን መሬት የገዙት ግለሰቦች ከአማራና ከአፋር ክልል እንዲሁም ከራሱ ከትግራይ ህዝብ ገንዘብና ንብረት የዘረፉ የሰራዊቱ መሪዎችና ቤተሰቦቻቸው ናቸው።

ይህን ገንዘብ በመጠቀም ለውጥ የማይፈልገው ቡድን ሰራዊቱ ውስጥ ካሉት አጋሮቹ ጋር በመሆን በልዩ ሁኔታ ለተመለመሉና ለሚያስለጥናቸው እስከ 7000 የሚደርሱ የሽብር ስራ በመላው ኢትዮጵያ ለማካሄድ ለሚሰለጥኑ  ሴትና ወንድ አሸባሪዎች ማሰልጠኛ በተግባር ላይ እያዋለው ነው(የመሰልጠኛ ቦታው ይታወቃል)። የአሰልጣኝነት ሚና የወሰዱት ግለሰቦች የልዩ ኮማንዶ አሰልጣኞች ብቻ ሳይሆኑ በከፍተኛ ደረጃ የሰለጠኑ የቀድሞ የኢትዮጵያ የደህንነት አባላት ጭምር ናቸው። እነዚህ ወጣቶችን እስራኤል ጠላቶቿን በተለያዩ ሃገሮች ውስጥ ለማጥፋት እንደምታሰማራቸው የጥቃት ቡድኖች እንጠቀምባቸዋለን በሚል ሂሳብ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር የተለያዩ የሽብር ስራዎችን የሚያከናውኑ ተደርገው እየተቀረጹ ነው።

ከዚህ ውጭም ወያኔዎች በኢትዮጵያ ሰላም እንዳይኖር ለመጠቀሚያነት ሲያዘጋጇቸው የነበሩ በተለይ አዲስ አበባ ገብተን ስልጣን እንይዛለን ባሉበት ወቅት እንደ መናጆ ሊገለገሉባቸው አሰባስበዋቸው የነበሩ የተለያዩ ነጻ አውጭ ድርጅቶች ሰራዊቶች ስልጠና እንዲቀጥል ተደርጓል። በመቀሌ አካባቢ ብቻ እስከ 8000 ቁጥር ያለው የኦነግ ሰራዊት አሁንም ያለ ሲሆን፣ በሮማይ ኪሮስ የሚመራ የአገው ነጻ አውጭ  ታጣቂዎችን ሳምረ በሚባል ቦታ ማሰልጠኑን  አሁንም አላቆመም። የአፋርና የሌሎችም ነጻ አውጭዎች ነን የሚሉ ድርጅቶች አሁንም ሰላም ከማይፈገው ቡድን ጋር ተቀራርበው እየሰሩ ነው።

የእነ ጌታቸው አሰፋና የነሞንጀሪኖ ቡድን፣ በአስተዳደርና በወታደሩ ውስጥ ካለው ጉልበቱ በላይ፣ በጁ የገባው ሃብት የሰላም ስምምነቱን የራሱን ቡድን ጥቅምና ፍላጎት ለማሳካት እየተጠቀመበት ይገኛል። መንግስት ከጦርነቱ በፊት ወደ ትግራይ  ልኮት የነበረው ገንዘብና የወያኔ የዶላር ክምችት አሁንም ያለው በዚህ ቡድን እጅ ነው። የተወሰነ ዶላርና ብር በተቀበረበት ብል በልቶት ቢገኝም፣ አሁንም ከፍተኛ ክምችት ያለው ገንዘብ በእዚህ ቡድን እጅ በተለያዩ ግለሰቦች ቤት በአደራ ተቀምጧል። ከኤፈርት ካምፓኒዎች አንዱ የሆነው በኢዛና የማእድን ኩባንያ ቀድሞ ሲወጣ የነበረና በጦርነቱም ወቅት እየወጣ የነበረው ወደ አምስት ኩንታል የሚሆን ወርቅ በተመሳሳይ መንገድ የሰላም ስምምነቱን በማይደገፍው ቡድና ቁጥጥር ስር ሆኖ በግለሰቦች እጅ ተቀምጧል። 

በጦርነት ወቅት ይደረግ እንደነበረው ዛሬም ወርቅና ሳፋየር በእርድታ ማስተባበሪያ መኪናዎች፣ በተለይ በአፋር፣ በአፍዴራና ሶርዶ ኬላዎች በአባዲ አፍሮ መኪናዎች  ከትግራይ እየወጣ ኢትዮጵያ ውስጥና ጅቡቲ እየተሸጠ ነው። በጦርነቱ ወቅት ሲሸጥ የነበረው ወርቅና ሳፋየር ብቻ ሳይሆን፣ ለትግራይ ህዝብ በእርዳታ የገባ መድሃኒት ወደ አፋርና አማራ ክልል እየወጣ ይሸጥ እንደነበር የራሱ የወያኔ የግምገማ ሰነድ አመላክቷል። ይህ የእርዳታ መድሃኒት ዛሬም በዘመድ በተሳሰሩ የትግራይ መድሃኒት ቤቶች ውስጥ መሸጡን እንደቀጠለ ነው ። ለምሳሌ መድሃኒቱ ሲሸጥባቸው ከነበሩ ቦታዎች መካከል ፋሚሊ ፋርማሲ ፣ ሂወት ፋርማሲ ሲሆኑ እነዚህ መድሃኒትቶችም ከEPSA ፣ ከዓይደር ሆስፒታል እና ከመቀሌ ሆስፒታል በአቶ አለማየሁ የ EPSA ስራ አስኪያጅ፣ ዶ/ር ሃጎስ ጎዲፋይ፣ ዶ/ር ፊሊሞን የመቀሌ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ አማካኝነት እየወጡ ይሰራጩ እንደነበረ በሚስጥር የተያዘው፣ ጉጅለ ሰለስተ በተባለው / የወያኔ ኢንተለጀንሲ ሰርቪስ በ3/12/2014 ለሁለተኛ ጊዜ የቀረበ ሪፖርት ያመለክታል ፡፡ 

በጦርነቱ ወቅት የትግራይ ዳያስፖራዎች ለቤተሰቦቻቸው ይልኩት የነበረው ዶላር ጅቡቲ ውስጥ የወያኔ ተባባሪዎች በከፈቱት አካዎንት እየገባ ብሩ ትግራይ ውስጥ እየተከፈለ ነበር።  በዚህ ስራ የተሰማሩ ግለሰቦች የትግራይ ዳያስፖራ ለቤተሰቦቹ ከሚልከው ገንዘብ እስከ 50 ከመቶ የሚደርስ ኮሚሽን ያስከፍሉ እንደነበር ይታወቃል። 30 በመቶ ኮሚሽን የተከፈለባቸው የሰነድ መረጃዎች በእጃችን አሉ። ይህን ስራ ትግራይ ውስጥ የሚቆጣጠረው ሰላም የማይፈልገው ቡድን ሲሆን፣ ከትግራይ ውጭ ደግሞ ስራ የሚያስተባብሩ ከወያኔ ጋር የሚሰሩ በስም የምናውቃቸው ትግራዋይ ያልሆኑ የኢትዮጵያ ባለሃብቶች ጭምር አሉ። ሌሎችንም ከወያኔ ጋር የተያያዘ ከፍተኛ ሃብት የነበራቸውን ግለሰቦችን ሃብት የሚያንቀሳቅሱ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ንብረት እየሸጡ ገንዘቡን በዶላር የሚያስተላልፉ፣ ዛሬ የወጭ ምንዛሪ ዶላር ከመቶ ብር በላይ በጥቁር ገበያ እንዲዘረዘር ያደረጉ ሰዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔዎች ተክተው እየተንቀሳቅሱ ነበር፤ አሁንም አልቆመም። በትግራይ የባንኮች መከፈት በጅቡቲ ወስጥ ከፍተኛ ኮሚሽን በመውሰድ ይደረግ የነበረውን የዶላር ምንዛሪ ያስቀረው ቢሆንም በሌላ በኩል ከየትኛዎቹም ክልሎች ይበልጥ ከባንክ ውጭ ትግራይ ውስጥ በጸረ ሰላም ሃይሉና በግለሰቦች እጅ የሚገኘውን ጥሬ ገንዘብ በትግራይና በሌላውም የኢትዮጵያ ግዛት የዶላር ምንዛሬውን ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ዘርዛሪዎቹ ከሞንጆሪኖ ቡድን ጋር ተቀራርበው የሚሰሩ ግለሰቦች ሆነዋል። ህገወጡን ምንዛሬ እስከ 120 ብር አድረሰውታል።

በትግራይ ውስጥ ያለውን በለውጥ ፈላጊና ለውጥ በማይፈልጉ ሃይሎች መሃከል ያለውን ሽኩቻ ከዚህ በላይ የተቀመጠውን ሃተታ ከጀርባ በማድረግ ስንቃኘው ነው ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ፖለቲካው የሚሄድበትን መንገድ መረዳት የምንችለው።

የሰላም ስምምነቱ በፖለቲካ መስኩ ያስቀመጠው መፍትሄ በትግራይ የሽግግር መንግስት እንዲሚቋቋም፣ ይህን የማቋቋም ሃላፊነት የኢትዮጵያ መንግስት እንደሚወስድ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት በስምምነቱ መሰረት የተሰጠውን ስልጣን ምን እያደረገበት እንደሆነ ባናውቅም ከላይ የጠቀስናቸው ሁለት ቡድኖችና በሶስተኛ ደረጃ የተጨመረ የነጻድቃን ቡድን ታክሎበት የሽግግሩን ሂደት በበላይነት ለመቆጣጠር እየተራኮቱ ያሉበት ሁኔታ ይታያል።

የተጠያቂነት ፍራቻ ያለበት የሞንጀሪኖ ቡድን የመጀመሪያውን እርምጃ በመውሰድ የካቲት 3 /2015 ሶስት ከወያኔ ማእከላዊ ኮሚቴ፣ ሶስት ከወታደሩ ክንፍ፣ ሶስት ከምሁራን የተወጣጣ የጊዜያዊ መንግስት መስራች ኮሚቴ አቋቁሞ ነበር።  በዚህ ኮሚቴ ውስጥ ፈትለወርቅና ራሱ ጌታቸው አሰፋ ራሳቸውን ማስገባት ያልፈለጉት በህዝብ ተቀባይነት ስለሌለን ከጀርባ ሆነን በራሳችን ሰዎች የፖለቲካ እንቅስቃሴውን እንመራለን በሚል ስሌት ነው። የዚህ ኮሚቴ አባላት ከህወሃት ማእከላዊ ኮሚቴ ኢሳያስ ታደሰ፣ አማኑኤል አሰፋ፣ ዶ/ር ሃጎስ ጎድፋይ በሞንጀሪኖ ቡድን የተመረጡ ሲሆኑ፣ ከሰራዊቱ ታደሰ ወረደ (ጀ/ል) ተክላይ አሸብር (ጀ/ል)፣ ጉእሽ ገብረ (ጀ/ል) በተመሳሳይ ያለ ሰራዊቱ እውቅና እንዲካተቱ የተደረጉ፣ እንዲሁም ከምሁራን፣ ሙሉ ኪዳነ ማሪያም፣ መረሳ ጸሃዬ፣ ሃንሳ ረዳ በቡድኑ በተመሳሳይ መንገድ የተመረጡ ናቸው። ከምሁራኑ፣ የተመረጡት ሙሉ ኪዳነ ማሪያም፣ መረሳ ጸሃዬ፣  ሁለቱ የፌደራል መንግስቱ ያልተቀበለው በትግራይ የተደረገው ምርጫ አስፈጻሚ ኮሚሽን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመነበር ሆነው በወያኔ ተሹመው የነበሩ ናቸው። ይህ ኮሚቴ በፍጥነትና በዚህ መልኩ የተዋቀረበት ዋናው ምክንያት የሽግግር ሂደቱን ነባሮቹና በተጠያቂነት እንያዛለን ብለው የሰጉት የህወሃት አመራሮች ለመቆጣጠር አስበው ነበር።

ይህን በነጌታቸው አሰፋ ውሳኔ ወደ ሽግግር መንግስት አሸጋጋሪ በሚል ስም የተቋቋመ ኮሚቴ ከህበረተሰቡ ቅቡልነት ለማግኘት ብዙ ጥረት አድርጓል። የተሳካለት ሊሆን አልቻለም። የካቲት 9 2015 ከሶስት በትግራይ ከሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ጋር በዘማሪያስ ሆቴል ለአሸጋጋሪ ኮሚቴው ድጋፍ ለማሰባሰብ የተጠራው ስብሰባ አብረው ፎቶ  ከመነሳት የዘለለ ሌላ ምንም ውጤት ሳያመጣ በተቃውሞ ተበትኗል። በተከታታይ ቀናትም በፕላኔት ሆቴል ከሙያ ማህበራት፣ ከጋዜጠኞች ማህበር፣ ከመምህራን ማህበር፣ ከነጋዴዎች ማህበር፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ማህበራት ጋር የተደረገው ስብሰባ ሃያ ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በተቃውሞ ተበትኗል። ከዚህ በኋላም ከመላው ትግራይ ከእያንዳንዱ ወረደ 3 ተወካዮች በመጥራት በደጀን የፕሬዚደንቱ ጽ/ቤት የተደረገው ስብሰባ የኮሚቴውን አባላት ማን መረጣችሁ በሚል ጥያቄ በማፋጠጥ ተበትኗል።

ከዚህ በተጨማሪ ከሰራዊቱ ተወክለዋል የተባሉትን ግለሰቦች ሰራዊቱ ያልመረጣቸው፣ እነ ጻድቃን እንኳን የማያውቋቸው በመሆናቸው ተቃውሞ ገጥሟቸዋል። ከዚህ ውዝግብ በኋላ ነው ጻድቃን የኮሚቴው አመሰራረት ትክክል እንዳልነበር እና ሁሉንም አካታች ሊሆን ይገባዋል የሚል ረጅም ሰነድ በእንግሊዝኛ ቋንቋ “አዘጋጅቶ”  ለአለም ያሰራጨው። በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተጻፈበት ምክንያት ሪፖርቱ ለአሜሪካ መንግስት እንዲቀርብ ታስቦ የተደረገ እንጂ የመጀመሪያው አድማጭ የትግራይ ህዝብ እንዳልሆነ የሚያሳይ ነው።  

ችግሩ እየተባባሰ በመምጣቱ ቅቡልነት ያጣው ኮሚቴ የካቲት 13 2015 ስራውን በተመለከተ ሪፖርት ለማቅረብና ግምገማ ለማድረግ በሚሉ አጀንዳዎች ሰበብ  የህዋሃት ስራ አስፈጻሚና የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ እንዲቀመጡ አደረገ። ይህን ስብሰባ ከጀርባ ሆኖ የሚመራው ያው ሰላሙን ተቃውሞ የቆመው ቡድን ነው። ይህ ስብሰባ የትም መድረስ ባለመቻሉ የካቲት 15 2015 የሴንትራል ኮማንድና ወታደራዊ ኮማንድ እንዲካተቱበት ተደርጎ ስብሰባው ቀጠለ።

በእዚህ እለት በተደረገው ስብሰባ ደብረጽዮን ከስልጣን እንዲወርድ ተጠይቆ ከስልጣን ከሚወርድ ሞቱን እንደሚመርጥ በፊት ለፊት በስብሰባው ላይ በመናገሩና ደብረጽዮን ከሞንጆሪኖ ቡድን ሰዎች በላይ በህዝብ ተቀባይነት ያለው በመሆኑ የሞንጆሪኖ ቡድን ሴረኞች አካሄድ ችግር ገጠመው። በዚህ ስብሰባ ላይ ደብረጽዮን አፉን ሞልቶ “ዶ/ር አብይ ከፈለግህ በፕሬዚደንትነት መቀጠል ትችላለህ” ብሎኛል በማለት ተናግሯል።   

አሁንም ከገባበት ችግር ለመውጣት የሞንጆሪኖ ቡድን አስቀድሞ የተዘጋጀበትን የተሳታፊውን ቁጥር ያበዛ በተከታታይ የተደረገ ስብሰባ ላይ ተቀመጠ። ስብሰባው ጉባኤ የሚል ስም የተሰጠውና በህዝብ ተወክለናል የሚሉ ነባር አመራሮች፣ የህወሃት የስራ አስፈጻሚና የማእከላዊ ኮሚቴ አባላት፣ የሰራዊቱ ኮማንድ እና የሴንትራል ኮማንድ አባላት የተሳተፉበት ነበር። የጉባኤተኞች ብዛት በጥቅሉ 401 ሲሆን 351 ድምጽ በመስጠት የሚሳተፉ፣ 50 ድምጽ መስጠት የማይችሉ ታዛቢዎች ነበሩ። በዚህ ስብሰባ ላይ ጻድቃን አልተሳተፉም ነበር ። ሆኖም ግን በምግበይና ወዲ አሸብር አሸማጋይነት ከሰአት በኋላ ተሳትፏል ። በጉባኤው ላይ ፣ ሰራዊቱ የመረጣቸው ተወካዮች፣ ከሙያ ማህበራት፣ ከሲቪክ ማህበራት ቢሳተፉም የተወከሉበት መንገድ ትክክል ባለመሆኑና ህወሃት የመረጣቻው በመሆናቸው በህዝቡ እና እንወክለዋለን በሚሉት አደረጃጀት ተቀባይነት ኣላገኙም ። የተቃዋሚ ፓርቲዎች ግን ሙሉ በሙሉ አልተሳተፉም።

የዚህ የጉባኤ አጀንዳና አካሄድ የሚዘውረው አሁንም የሽግግር ሂደቱን ከኋላ እየተቆጣጠረው ያለው የነጌታቸው አሰፋ ቡድን እንደሆነ በጉባኤው አጀንዳ አቅራቢና ተደራጅቶ በቀረበው ውይይት ባልተደረገበት አጀንዳ አጸዳደቅ የተረጋገጠ ሆኗል።  አጀንዳ አቅራቢው አለም ገበረዋህድ፣ የነጌታቸው አሰፋ ቡድን ቀኝ እጅ ነው። የመጀመሪያው አጀንዳ ጉባኤውን የሚመራ ፕሬዚደየም መምረጥ ሆነ። አሰቀድሞ ድርጅታዊ ስራ በተሰራበት መንገድ ዶ/ር ደብረጽዮን ሊቀመንበር፣ ታደሰ ወረደ ምክትል፣ ሊያ ካሳ፣ ዘውዱ ኪሮስ፣ ሙሉወርቅ ኪዳነ ማሪያም፣ አባላት አድርጎ መረጠ።   ምርጫውን በተመለከተ ጆን መዲድ(ጀ/ል) “አዲስ ፊት ያላየንበት አሳፋሪ ምርጫ ነው” በማለት በስብሰባው ላይ አስተያየቱን ሰጥቶበታል ።  

በዚህ ጉባኤ ላይ በአለም ገብረዋሃድ የተዘጋጀው የሽግግር መንግስት ሰንድ ላይ ውይይት ተደርጎ ስብሰባው ተበተነ። ሰኞ የካቲት 20/2015 አለም ገብረዋህድ የህወሃት ጽ/ቤት ሃላፊ የስራ አስፈጸሚ ኮሚቴ የማእከላዊ አባላት ስብሰባ ጠራ። በስብሰባው ላይም ፕሮፖዛል ይዞ መጣ። ፕሮፖዛሉ የሽግግር መንግስቱ መመራት ያለበት በወያኔ መሆኑን በማተት፣ ደብረጽዮን በፕሬዚደንት ይቀጥል፣ አቶ በየነ ምክሩ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ፣ ሊያ ካሳ የተፈጥሮ ሃብት ክላስተር አሰተባባሪ፣  ወ/ሮ የአለም ጸጋይ የኢንፍራ ስትራክቸር ክላስተር አስተባባሪ፣ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት የማህበራዊ ክላስተር አስተባባሪ፣ ዶር እያሱ እርሻ ቢሮ ሃላፊ ፣ ዶር አማኑኤል ሃይሌ የጤና ዘርፍ ሃላፊ ፣ ዶር ኪሮስ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ፣ ወ/ሮ ገነት አረፈ ታክኒክና ሙያ ስልጠና ቢሮ ሃላፊ ፣ ወ/ሮ አልማዝ ገ/ፃዲቅ ከተማ ልማት ቢሮ ሃላፊ ፣ ዶር ሃጎስ ጎዲፋይ ፕሬዚዳንት አማካሪ ፣ አቶ ዘበርህ የመሬት አጠቃቀም ሃላፊ፣ ወ/ሮ ምህረት የፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ በማድርግ አዲስ ካቢኔ እንዲቋቋም የሚያደርግ ሃሳብ ያቀረበ ነበር፡፡

ይህ ፕሮፕዛል ደብረጽዮንን ሊቀመንበር አድርጎ ብቻ በማቅረቡ እንደ ደብረጽዮን በማእከላዊ ኮሚቴው ውስጥ የሚዋልል አቋም ያላቸውን አባላት ድጋፍ ስላገኘ ጸደቀ። በዚህ ፕሮፕዛል ውስጥ የደብረጽዮን ጉዳይ አንዳለ ሆኖ ከበየነ ምክሩ በስተቀር የተቀሩት ስራ አስፈጻሚ አባላት ቀንደኛ የነጌታቸው አሰፋ ጸረ ስላም ቡድን አባላት ናቸው። የካቢኔው አባላትም በአለም ገብረዋህድ አቅራቢነት በመምጣታቸው ከነጌታቸው አሰፋ ቡድን ውጭ ይሆናሉ ብሎ ማሰብ አይቻልም። አስገራሚው ነገር ጉባኤ እንዲመሩ የተመረጡ ሰዎች እራሳቸው በሚመሩት ስብሰባ ላይ ተመልሰው መመረጣቸው ነው። ደብረጺዮን እና ሊያ ካሳ ጉባኤ መሪዎች ተበለው ተመርጠው ነበር።  

በእንዲህ አይነት ቅጥ አምባሩ በጠፋ የሴራ ሂደት የነጌታቸው አሰፋ ቡድን የሽግግር መንግስቱ ከወያኔ እጅ እንዳይወጣ በማድረግ የራሳቸው ሰዎች በበላይነት የሚቆጠጠሩት መንግስት አቁመው ለኢትዮጵያ መንግስት ውጤቱን አሳውቀዋል። በዚህ ስብሰባ ላይ የጌታቸው አሰፋ ቡድን ደጋፊዎች የተሰጡት አስተያየት፣ ይህን ወሳኔ የኢትዮጵያ መንግስት የማይቀበለው ከሆነ እስከመጨረሻው እንደሚታገሉትና ጉዳዩን ወደ አባሳንጆና ኡህሩ ኬንያታ እንደሚውስዱት ነው። ይህ ማለት ጉዳዩን ወደ አሜሪካ መንግስት በማቅረብ የአሜሪካ መንግስት በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ተጽእኖ በማድረግ የትግራይን ሽግግር መንግስት እንዲቀበለው ለማድረግ እቅድ እንደተያዘ የሚያሳይ ነው። አሁን ባላንበት ወቅት የኢትዮጵያ መንግስት ከትግራይ የቀረበለትን ፕሮፖዛል አልቀበልም ብሏል። ይህን ምላሽ የሰማው ህወሃት እንደገና ስብሰባ ተቀመጧል።  

ዛሬም በወያኔ ውስጥ ያሉ ጸረ ሰላም አመራሮች  አላማቸውን ማሳካት የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ ነው። የአመጽ እርምጃዎች ለመውሰድ ከሚያስችሉ ዝግጅት አንስቶ በተለያዩ ሰላማዊ የዲፕሎማሲና የኢኮኖሚ ስልቶች ፍላጎቶቻቸውን ለማስፈጸም እንደሚችሉ በሙሉ ልብ እየተናገሩ ነው። ብልጽግና ውስጥ በመግባት አብይን መስሎ አብይን ማሸነፍ፣ የአማራ ክልል መንግስትን እና የኤርትራ መንግስትን የሰላም ስምምነቱ የማይደግፉ ሃይሎች አድርጎ በማቅርብ ከማእከላዊ መንግስት መነጠል፣ አልፎም ከማእከላዊ መንግስት ጋር በመሆን መውጋት፤ ይህን ለማደርግ የሚያስችል በፕሪቶሪያው ስምምነት ውስጥ “ሌሎች ችግሮች በህገመንግስቱ መሰረት ይፈታሉ የሚለው አንቀጽ” እንደሚጠቅማቸው፣ የወልቃይት ጉዳይ በህገ መንግስቱ መሰረት የሚፈታ ከሆነ ህገመንግስቱ ወልቃይት የትግራይ ግዛት አድርጎ ስለሚያስቀምጥ በቅድሚያ ሌላ መፍትሄ ከመታሰቡ በፊት ግዛቱ ወደ ህገመንግስታዊ ባላቤቱ መመለስ አለበት የሚለው ጥያቄያቸው ፍትሃዊ ተደርጎ በፌደራል መንግስቱና በአሜሪካኖች እንደሚታይ፣  ይህ የማይዋጥላቸው የአማራ ክልላዊ መንግስትና  የኤርትራ መንግስት ተቃውመው እንደሚቆሙ፣ ይህን ተቃውሞ ምክንያት በማድረግ በሰላም ስምምነቱ ማስከበር ስም ሁለቱን ታሪካዊ ጠላቶች መውጋት እንደሚቻል፣ በአማራ ህዝብና በኤርትራ ህዝብ መሃል የተፈጠረውን ግንኙነት መበጠስ፣ በኢትዮጵያ መከላከያ ውስጥ ተመልሰን መግባታችን እና ሹመት ማግኘታችን የማይቀር በመሆኑ እንዲያውም በቅርቡ ሹመቱ ይመጣል በማለት ይህን ሹመት ትልቅ ተጽእኖ አሳዳሪ ጉልበት በመከላከያው ውስጥ እንደሚሰጣቸው፣ የፌደራል መንግስቱን መከላከያ አመራሮችን ከዚህ ቀደም ሲያደርጉት እንደነበረው በወያኔዎች እጅ ባላው ከፍተኛ ሃብት የወያኔ ፍላጎት ፈጻሚዎች ማድረግ እንደሚቻል፣ የሰሜን ጦር ከመጠቃቱ በፊትና በተጠቃበት እለት ከኢትዮጵያ የሰራዊት  አመራሮች መሃል በጥቅማ ጥቅም የገዟቸውን፣ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላም በሚሊዮኖች ገንዝብ ስጥተው ማስከዳት የቻሏቸውን ዛሬ መቀሌ ተቀመጦ የኦነግ ሰራዊት አደራጅ የሆኑት አንዳንድ የጦር መሪዎች መመልመል እንደቻሉ ሌሎችንም መመልመል እንደሚቻል እቅድ እያወጡ ይገኛሉ።

በዲፕሎማሲ መስኩ ለሚያደርጉት ስራ አለም አቀፍ የትግራይ ምሁራን ድርጅት እና በውጭ የሚገኙ የስርአቱ ደጋፊዎች በሚያሰባስቡት ገንዘብና መንግስት በሚያቀረበው ገንዘብና እርድታ ተመስርቶ የኢትዮጵያን መንግስት ለማሳጣት  የሚያስችል ዝርዝር የሆነ በሰብአዊ መብት ጥሰትና በጦር ወንጀለኛነት መንግስትን ሊያስፈርጅ የሚያስችል ስራ እየተሰራ ነው። በኢትዮጵያ መንግስት በኩል በተመሳሣይ ግን በወያኔ በትግራይና በሌሎች ክልሎች በራሱ በወያኔ ሃይሎች የተፈጸሙ የአስገድዶ መድፈር የግድያ፣ ሌሎችንም ዘግናኝ ወንጀሎችን በተመለከተ በተደራጀ መንገድ መረጃ የሚያሰባስብ አካል አለመኖሩ የሚያስገርም ነው። 

  • የሰላም ስምምነቱ ከወታደራዊ ጉዳዮች አንጻር

የሰላም ስምምነቱ ሌላው አካል፣ ወያኔ ሁሉንም ትጥቆቹን ያወርዳል ሰራዊቱንም በካምፕ ያስገባል የሚል ነው። ከትግራይ የሚሰብሰው መረጃ የሚያሳየው በአጉላ እና በአካባቢው የነብሩ ተተኳሽ ያለቀባቸው የተበላሹ ጥቂት ታንኮችና መድፎች ማስረከባቸውን ነው። ከዚህ ውጭ በመረጃ ስማቸው በሚታወቁ ከእይታና የትራንስፖርት መግቢያ የሌላቸው፣ ሚስጥር በመጠበቅ የማህበረስቡ አንድ ወጥ አሰፋፍር ባላቸው በርካታ ቦታዎች ላይ በርካታ ከባድና የቡድን መሳሪያቸውን አስቀምጠዋል።

ሰራዊቱ በካምፕ መሰብሰብን በተመለከተ፣ በመንገድ ዳር ከሚገኙ በቀላሉ በሚታዩ በመቀሌ ዙሪያ፣ ገረብ ግባ፣ምላዛት፣ ሳምረ፣ አዲ ጉደም፣ አራአ ሰገዳ፣  እና በቆላ ተንቤን ወረዳ በአግበ ከተማ ካሰባስቧቸው የሰራዊት አባላት ውጭ በሌሎች በመረጃ ተደግፈው መቅረብ በሚችሉ ከመንገድ በራቁ ለትራንስፖርት አመቺ ባላሆኑ በርካታ ቦታዎች ላይ ወታደራዊ ዝግጅቱ አሁንም እንደቀጠለ ነው። የውጊያ ስልት፣ የእግር ጉዞ፣ የወታደራዊ ጽንጸ ሃሳብ ትምህርቶች ያለፈው ውጊያ ግምገማዎች እየተካሄዱ ነው። ለትግራይ ህዝብ  የተላከወን የእርዳታ እህል ወያኔዎች ይህን ሰራዊት ለማሰልጠኛነት እየተጠቀሙበት ነው።

ቀደም ተብሎ የተጠቀሰው ወያኔዎች ለሽብር ስራ እያዘጋጁት ካለው 7000 ከሚቆጠር ልዩ ሰልጣኝ እና በነጻ አወጭ ድርጅት ስም አሁንም ስለጠና እየሰጧቸው ያሉትን የኦሮሞ፣ የአገው፣ የአፋርና ሌሎችንም ነጻ አውጭ ሰራዊትን ስንጨምርበት ወያኔዎች እውን ለሰላም እየተዘጋጁ ነው የሚል ጥያቄ የሚያስነሳ ይሆናል። ሌላው በከፍተኛ ጥንቃቄ መታየት የሚገባው ጉዳይ ወያኔዎች በጃቸው ያለውን ከፈተኛ ሃብትና ከዚህ ቀደም ሰዎችን በሙስና የማጥመድ ችሎታቸውን በመጠቀም በቅርብ ጊዜ ውስጥ የማእከላዊ መንግስት ወደ ትግራይ የላካቸው የመከላከያ፣ የፖሊስ የደህንነት አባላት በጥቅም በገንዝብ በሌሎችም ዘዴዎች የመያዝ ስራ መጀመራቸው ነው። ይህ የሙስና ስንሰለት የት ድረስ ሊዘረጋ እንደሚችል በተለይ በሃገሪቱ ውስጥ ከሰፈነው የሙስና ባህል አንጻር መገመት ከባድ አይደለም። በጦርነቱ ወቅት የወያኔ የመረጃ ሃላፊ የነበሩ፣ በረሃ ገብተው ሲያዋጉና ሲዋጉ የነበሩ በወያኔ ዘመን በከፍተኛ ደረጃ የሰለጡኑ ሰዎች አንዳንዶቹ በቻርተር አይሮፕላን ሲንቀሳቅሱ የነበሩ ዛሬ አዲስ አበባ ከተማ መሃል በነጻነት የሚንቀሳቅሱበት ሁኔታ እያየን ነው። በመንግስት የሚያሳምን መግለጫ እስካልተሰጠበት ድረስ እንደዚህ አይነት ግለሰቦች ያለምንም ስጋት በአዲስ አበባ ከተማ የሚንቀሳቅሱበት ምክንያት የወያኔዎች የሙስና የስራ ውጤት ከመሆን አይዘልም። በወንጀል ሊጠየቁ የሚገባቸው ግለሰቦች የመቀሌን ኤርፖርት ብቻ ሳይሆን በቦሌ ኤርፖርት ጭምር ወደ ውጭ ሃገር የወጡበት ሁኔታ እንዳለ መረጃዎች አሉ። ከሰላም ስምምነቱ በኋላ ምን ያህል ሰዎች ወያኔ ወደፊት ላቀደው የኢኮኖሚና የሽብር ስራ ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ገብተዋል ሌላው መንግስትን እና ህዝብን ሊያሳስብ የሚገባ ጉዳይ ነው።

  • ኢኮኖሚያዊና ሁኔታዎች በተመለከተ

በመሰረተ ልማትና በተቋማት ውድመት ደረጃ በትግራይ ውስጥ ወያኔ እራሱ ካደረሳቸው ጥፋቶች፣ ለምሳሌ በአክሱምና በሽሬ፣ የአውሮፕላን ማረፊያዎችን የኢትዮጵያ መንግስት እንዳይጠቅምባቸው ለማድረግ ከተከናወኑ ጥፋቶች ውጭ ወያኔዎች በአማራና በአፋር ክልል ሆን ብለው ያወደሙትን አይነት የመሰረተ ልማትና የተቋማት ውድመት በትግራይ ውስጥ አልደረሰም። በተቋማት ውስጥ የነበሩ ንበረቶች በተለያዩ አካላት የተዘረፉ ቢሆንም ዘረፋው የተወሰኑ ቦታዎችን የሚመለከት እንጂ በአፋርና በአማራ ክልል ወያኔዎች ሆን ብለው የህዝቡን የመንግስትን ተቋማትን ንበረት በዘረፉበት ደረጃ የተዘረፈ አንዳልሆነ መረጃዎች ያመላክታሉ። ለምሳሌ ከኮመቦልቻ ደሴ በርካታ ማሽነሪዎች ፣ ጀነሬተሮች በገብረሊባኖስ የተባላው የሞንጀሪኖ ባል እንደዘርፈ እና እንደሽጣችው በሰኔ 15/2014 በአክሱም ሆቴል በነበረው የአመራር ስብስባ ላይ ተገምግሟል፡፡  እንዳውም አንዳንዶቹ ተቋማት በራሱ በወያኔ ትእዛዝና በወያኔ ተባባሪዎች ንብረቱን ለጦርነቱ በግብአትነት እንዲያስረክብ ተደርጓል። ዶ/ር ፋና ሃጎሰ የቀድሞ የትግራይ ክልል የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት የነበረች እና ፌዴራል መንግስት መቀሌን ሲቆጣጠር የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ሆና የተሾመች  ቀንደኛ የእነ መንጆሪኖ ደጋፊ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንትነቷ የዩኒቨርስቲዎን የምግብ ማብሰያዎች፣ ፍራሾችና ኮምፕዩተሮች እና ሌሎቸ ንብረቶች ለሰራዊቱ አሰርክባለች። ባሁኑ ወቅት መቀሌን ዩኒቨርስቲ ምንም አይነት የማስተማሪያ ግብአት የሌለው ሲሆን ሃላፊዋ መንግስት ዩኒቭርስቲውን መልሶ እንዲያደራጅ አይኗን በጨው ታጥባ ትምህርት ሚኒስቴርን እየወተወተች ነው ። ሌሎችም መንግስታዊ የሆኑና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም የግል ድርጅቶች ከኤሌትሮኒክስ እቃ አንስቶ እስከ ሌሎች ቁሳቁሶች ለጦርነቱ መሳለጥ እንድያዋጡ በደብዳቤ ተጠይቀው በርካቶች አስተዋጽኦ አድርገዋል።

በትግራይ ውስጥ ያለው የኢኮኖሚ ችግር ጦርነቱ ምርት አንዳይመረት በማስተጓገል የእህልና የጥራጥሬና ሌሎችም የምግብ ፍጆታዎች እጥረትና ዋጋ ማሻቀብ ነው። የሰላም ስምምነቱ ከተደረሰ በኋላም የምግብ እርዳታ በገፍ ቢገባም ህዝብ ከምግብ እጥረት ጋር የተያያዘው ችግሩ አሁንም አልተፈታለትም። በተለያዩ ቦታዎች የእርዳታ እህል በተለያዩ መጋዘኖች ተከማችቶ ይታያል። ህዝብ እርዳት ሲጠይቅ የሚሰጠው መልስ “እህሉ ለከፉ ቀን የተያዘ ነው” የሚል ሆኗል። በወታደራው መስኩ ትግራይ ውስጥ ካለው ሁኔታ በመነሳት ክፉ ቀን ማለት ምን ማለት እንደሆነ መገመት ከባድ አይሆንም።

ሌላው በትግራይ ውስጥ ትልቅ ችግር የሆነው ጉዳይ በአንዳንድ ግልሰቦች እና ባለስልጣኖች እጅ  የሚንቀሳቅሰው ከፍተኛ ብዛት ያለው ጥሬ ገንዘብ ነው። ይህ ጥሬ ገንዝብ ጦርነቱ አንድ ቀን ሲቀረው፣ ለትግራይ ንግድ ባንክ ተልኮ የነበረውን በወያኔዎች እጅ የወደቀውን በቢሊዮኖች የሚቆጠር ብር ጨምሮ፣ ከአማራና ከአፋር ህዝብና ባንኮች ወያኔዎች በመዝረፍ የሰበስቡት ተደምሮበት እንዲሁም በቅርቡ የኢትዮጵያ መንግስት ለባንኮች የላከው 5 ቢሊዮን ብርና ከዚህ ውጭ የተለያዩ አለም አቀፍ ድርጅቶች በየወሩ ወደ ትግራይ የሚልኩት ከ1 ቢሊዮን እስከ 1.5ቢሊዮን የሚደርስ ጥሬ ገንዝብ ነው። በተለይ ገንዘቡን የያዙ ግለሰቦች ከ20 እስከ 50 % የሚደርስ ወለድ በማስከፈል ለህዝቡ ብድር የሚሰጡ ሲሆን የህዝቡን ስቃይና መከራ እያባባሱበት ይገኛሉ ፡፡

በባንክ የሚደረግ የክፍያ ስርአት ፈጽሞ የለም፣ ገንዘብ ያገኘ ሰው ገንዘብ በእጁ ይዞ የሚዞርበት ከፍተኛ ግብይቶች ሳይቀሩ በካሽ የሆነበት ሁኔታ ተፈጥሯል ። አለም አቅፍ ድርጅቶ የሚልኩት ገንዝብ ለደሞዝና ለሌች ስራዎች ወጪ ተደርጎ በካሽ መልኩ ሆኗል ህብረተሰቡ ውስጥ የሚበተነውና የሚከማቸው። በትግራይ ውስጥ ያሉ ባንኮች ከሞላ ጎደል ሁሉም ባዶ ናቸው። ይህን ችግር ለመቅረፍ በሳምንት አምስት ችህ ብር በግለሰብ ደረጃ ወጪ እንዲደረግ ቢወሰነም ውሳኔው በዘምድ አዝማድ፣ በምልጃ በጉቦ ተፈጻሚ መሆን አልቻለም። ይህ የጥሬ ገንዝብ ዝወውር ብዛት በትግራይ ውስጥ ከየትኛውም የሃገሪቱ ክልል በላይ የዋጋ ግሽበት በማስከተል የተራውን ህዝብ ኑሮ  የከፋ እንዲሆን አድርጎታል።  ይህ ብር ቀደም ተበሎ እንደተገለጸው ከትግራይ አልፎ በተቀሩት የኢትዮጵያ ግዛቶች ውስጥ መበተን በመጀመሩ የውጭ ምንዛሪ የጥቁር ገባያ የሚያጠናክር፣ የደሃውን ህዝብ ህይወት የከፋ የሚያደርገውን ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ የሚያባባስ እየሆነ እየሄደ ነው። በተጨማሪም እነዚህ ግለሰቦች በራማ በኩል በዶላር እስከ 120 ብር ድረስ እንዲመነዘር በማድረግ ብሎም ብሩ የተለያዩ ንብረቶች እና የመሬት ግዥ ላይ በማዋል የአገሪቱ የመግዛት አቅም በማዳከም ላይ ይኛሉ ፡፡ በዚህም መሰረት እነሞንጀሪኖን ጨምሮ በትግራይ ውስጥ ከፍተኛ ብር ከዝነው ያሉ ግለስቦች፣

1 አባዲ ግርማይ { አዋሽ ትራንስፖርት }

2 ሃይለ ላምባ ፣ ትራንስፖርት እና ማደያ

3 ሃይለ አስፍሃ { ማይ ሱር ትራንስፖርት {

4 ሃይላይ ደስታ ሃደራ [ ትራንስፖርት

5 ሙሴ መርሳ

6 እንዳ ሃድጉ ቤተስብ

7 ራሄል ጣፍ

8 አብረሃ ተክለሃይማኖት

9 ሌሎችም

ሌላ ከኢኮኖሚው ጋር መጠቀስ ያለበት ጉዳይ የእነጌታቸው አሰፋ ቡድን በጁ ካስገባው ወርቅና ሳፋያር እንዲሁም ከእነዚህ ማእድኖች ጋር በተያያዘ ከሚያኪሂደው ሽያጭ በተጨማሪ የመቀሌን ህዝብ አገልግሎቶች ለምሳሌ እንደ መብራት አገልግሎት አይነቶቹን ገቢ በቀጥታ የሚቆጣጠር መሆኑ ነው። በቅርቡ በመብራት ክፍያ ላይ 15 ከመቶ ጭማሪ በማድረግ የመቀሌ ህዝብ አፍንጫውን ተይዞ ክፍያ እንዲከፍል እየተደረገ፣ ክፍያው በጥሬ ገንዝብ ብቻ እየተሰበሰበ፣ በሞንጆሪኖ ቡድኖች እጅ በየሰው ቤት የሚቀመጥ ሆኗል። ይህን ክፍያ የሚያሰባስበው የመብራት ሃይል ሃላፊ የሞንጀሪኖ ቤተሰብ ነው ። በሌላው መልኩ ከአንዳንድ የወያኔ ወዳጅ ሃገራትና ከትግራይ ዳያስፖራ ለጸረ ድሮንና ለጦር መሳሪያ መግዢያ በሚል የተሰበሰበው ብዙ ሚሊዮን ዶላር በሞንጀሪኖ አካውንት መግባቱ በወያኔ ግምገማ የተደረገበት ጉዳይ ቢሆንም እስካለነበት ሰአት የተቀየረ ነገር ባላመኖሩ ዶላሩ አሁንም በሞንጀሪኖ አካዎንት ይገኛል።  

ተመሳሳይነት ያላቸው የማፍያ አይነት፣ የወያኔ አመራሮች በቀጥታ እጃቸውን የሚያስገቡባቸው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ተበራክተዋል ። በቅርቡ የመስቦ  ሲሚንቶ ፋብሪካ ስራ እንዲጀምር የቀረበውን ሃሳብ ተፈጻሚ ለማደርግ ፋብሪካው የሚያስፈልገውን የከሰል ድንጋይ ከደቡብ አፍሪካ እና ከአገር ውስጥ አስመጭዎች የሰራዊቱ አመራሮች እንዲሆኑ በወያኔ ተወስኗል ። ፋብሪካው ሲጀመር መቀጠር የሚችሉ ሰራተኞች  የቅጥር መስፈርት የካቲት 25 2015 በ/ገሚካኤል ገብሩ  ፊርማና ማህተም በወጣው ማስታወቂያ ላይ፣ በቁጥር 4) መታገሉን ከትግራይ ሰራዊት ማምጣት ይሚችል፣ 5) ባላፈ ሁለት አምት ውስጥ ራሱን እና ቤተሰቡን ያታገለ 6)  ቅድሚያ የሚሰጠው ከአንድ ቤት ሁለት እና ከዛ በላይ ላታገለ የሚሉ መስፈርቶች ተካተውበታል። የወያኔ መሪዎች በኢኮኖሚ መልኩ ለ27 አመት ያካባተቱን ሃብት በመጠቀም በትግራይ ውስጥ ህዝቡ እነሱ የፈለጉትን ነገር እንዲፈጽም ማድረግ እንደሚችሉ ሙሉ እምነት ያላቸው ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብም ላይ ተመሳሳይ ተጽእኖ ማድረግ እንደሚችሉ ተማምነው እየተንቀሳቅሱ ናቸው።

  • ማህበራዊ ሁኔታን በተመለከተ

ትግራይ ውስጥ የሰላም ስምምነት ይደረግ እንጂ ማህበረስቡ ሰላምና መረጋጋት እንደራቀው ነው።  በጦርነቱ የተነሳ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች አሁንም በችግር ላይ ናቸው። በመሳሪያ የተደገፈ ዘረፋ፣ የመሳሪያ ሽያጭ፣ ጾታዊ ጥቃት የመሳሰሉት ወንጀሎች እንደቀጠሉ ናቸው። በመቀሌ ከተማ በአንድ ሳምንት ብቻ 31 ሰዎች በጩቤ ተወግተው አይደር ሆስፒታል ለህክምና ገብተዋል። ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ ማህበረሰቡ በተለይ ህጻናት ሴቶች አረጋውያን የገቡበት የስነልቦና ቀውስ ለመገመት ከሚቻለው በላይ ነው። የልጆቻቸው መኖርና አለመኖር ሃቁ ያልተነገራቸው ወላጆች በመርዶ ይደርሰኛል ስጋት በሰቀቀን እየኖሩ ነው። ከጦርነቱ ጋር በተያያዘ እጅና እግሩ የተቆረጠው አይኑ የጠፋው ሌላም የአካል ጉዳት የደረሰበት በርካታ ወጣት በከተሞች ማየት ራሱን የቻለ የስነልቦና ችግር ፈጣሪ ሆኗል።

ወያኔ በጀመረው ጦርነት ህይወቱን ያጣው፣ አካሉ የጎደለው የትግራይ ወጣት ብዛት በውል አይታወቅም። በልጆቻቸው ድጋፍ የሽምግልና እድሜያቸውን በሰላም እንገፋለን ያሉ በርካታ ወላጆች ያለ ጧሪና ቀባሪ ቀርተዋል። ስጋትና ፍራቻ የህዝቡ የቀን ተቀን ህይወት ድርና ማግ ሆኗል። እድል ቢያገኝ ከትግራይ ነቅሎ ለመውጣት የሚፈልገው ሰው ብዙ ነው። የተቻላቸው በተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ ሰዎች ቤታቸውን እየሸጡ ጉቦ በመስጠት በተለያዩ አቅጣቻዎች በአየርና በመኪና ከትግራይ እየውጡ ነው። በዚህ ላይ በጦርነቱ ወቅት የቆሙ የትምህርት የጤና ሌሎችም  መንግስታዊ አጋልግሎቶች ስራ አልጀመሩም። ባጭሩ የሰላም ስምምነት ይፈረም እንጅ የትግራይ ህዝብ ሰላም አላገኘም። በፖለቲካውና በወታደራዊ መስኩ የሚታየው የፀረ ሰላም ሃይሎች እንቅስቃሴ የትግራይ ህዝብ ሰላም እንዲህ በቀላሉ የሚያገኝ አይመስልም።

በህዝቡ ውስጥ ወያኔ ችግሬን ይፈታልኛል የሚል እምነት እየተመናመነ መሄዱን የሚያሳዩ በርካታ ምልክቶች አሉ።  በፖለቲካ መስኩ የትግራይን ችግር የፈጠሩና ያባባሱ የፖለቲካ ሰዎችን ለማስወገድ ከተጀመረው ጥረት በተጫማሪ ህዝብ ወያኔ የተመሰረተበትን የካቲት 11ን እንዲያከበር ተጠይቆ ይህ በአል የኔ አይደለም በሚል በመላው ትግራይ በበአሉ ባለመገኘት አቋሙን ገልጿል። በወያኔ ጥሪ የተደረገላቸው ከዚህ ቀደም ወያኔ ዝለሉ ሲላቸው ስንት ሜትር በማለት ይጠይቁ የነበሩ ማህበራት ሳይቀሩ በበአሉ ላይ አልተገኙም። በአንዳንድ እንደ ሓሓይለ የመሰሉ የማእከላዊ ዞን ወረዳዎች ወያኔ በሹመት የላካቸውን አሰተዳዳሪዎች ህዝብ አንቀበልም ያለበት ሁኔታ ተፈጥሯል። በአጠቃላይ በአሁን ወቅት ስደት ፣ ህገወጥ የሰው ዝውውር ፣ ዝርፍያ ፣ የኑሮ ውድነት ፣ ፆታዊ ጥቃት እና የመሳሰሉት ችግሮች ከሰላም ስምምነት በኋላም ቢሆን ያልተፈቱ ችግሮች ሆነው ቀጥለዋል።

  • የዲፕሎማሲያዊ ሁኔታ በተመለከተ፣

ዝርዝሩ ብዙ ቢሆንም ዛሬ በትግራይ ውስጥ፣ ለውጥ በሚፈልገው የትግራይ ህዝብና የህወሃት ወጣት አመራርና በጸረ ስላም ሃይሉ የነጌታቸው አሰፋ ቡድን መሃል ያለውን ትግል በከፍተኛ ደረጃ ወደ ጸረ ሰላም ሃይሉ እንዲያዘነብል የሚያደርገው ጸረ ሰላም ሃይሉ በዲፕሎማሲ መስኩ ያለው ድጋፍ ነው። ይህ ድጋፍ የትግራይን ሰላም ብቻ ሳይሆን በጥንቃቄ ካልተያዘ የኢትዮጵያን እና የቀጠናውን ሰላም የማናጋት አቅም አለው። ይህ አቅም የተገነባው በሶስት መሰረታዊ ዋልታዎች ላይ ነው።

የመጀመሪያው፤ ረጅም ዘመን ያስቆጠረ ገና በትግሉ ጊዜ የጀመረ የወያኔ መሪዎች የአሜሪካን ጥቅም በምስራቅ አፍሪካ ለማስጠበቅ መሳሪያ ለመሆን ዝግጁነታቸውን ከገለጹበት ዘመን ይጀመራል።  ወያኔ ስልጣን ከያዘ በኋላ በሂደት እንደታየው የአሜሪካ መከላከያ ተቋም፣ የአሜሪካ እና የእንግሊዝ የስለላ ድርጅቶች ከወያኔ ጋር እጅና ጓንት ሆነው የሚሰሩበት፣ ወያኔ በምስራቅ አፍሪካ አካባቢ የአሜሪካንን ቆሻሻ ስራ ፈጻሚ የሆነበት ሁኔት ተፈጥሯል። ወያኔ የአሜሪካኖችን ጥቅም ለማስከበር ከፔንታጎን ጀነራሎች ጋር ተስማምቶ አንድን ሏላዊ ሃገር ሶማሊያን እስከመውረር ደርሷል። ከስለላ ድርጅቶቹ ጋር በመተባባር የግድያ የአፈና ስራ ሲሰራ ነበር። የወያኔ ጀነራሎች የፔንታጎን፣ የወያኔ ሰላዮች የሲአይኤና የእንግሊዙ ኤም አይ 6 ቤተኞች ነበሩ።  ለ27 አመት የአሜሪካንን እና የምእራባውያን ጥቅም በማስጠበቅ ወያኔዎች ለእነዚህ መንግስታት የዋሉትን ውለታ እነዚህ መንግስታት የሚረሱት አይደለም። በተለይ በምእራቡ አለም ቁልፍ የሆነውን የሰው ለሰው ግንኙነት ኔትዎርክ ወያኔዎች በ27 የስልጣን ዘመናቸው በሚገባ ያደራጁት በመሆኑ በየትኛውም የምእራብ መንግስታት ተቋማት ውስጥ ሊተባበሯቸው የሚችሉ በርካታ ወዳጆች አፍርተዋል። ይህ የግንኙነት መረብ ከነጩ ቤተመንግስት አንስቶ፣ በመከካከያ፣ በስለላ ድርጅቶችና በሚድያ ተቋማቱ የተዘረጋ ለመሆኑ ወያኔ የአንድን ነጻ ሃገር የመከላከያ ሰራዊት አጥቅቶ ጦርነት በኢትዮጵያ ላይ በከፈተበት ወቅት ከአሜሪካና ከምእራብ መንግስታ እንዲሁም ከሚድያ ተቋማቱ ካገኘው ምንም ይሉኝታ በሌለው ድጋፍ ተገልጿል።

ሁለተኛው፤ ለጸረ ሰላም ሃይሉ የዲፕሎማሲ አቅም የሚሰጠው በጁ ያለው ሃብት ነው። ብዙ ጊዜ ስለሃብት ሲወራ ሰዎች የሚጠቅሱት ወያኔ ስልጣን ከያዘ በኋላ ከሀገር በተጭበረበረ ሰነድ አማካይነት ከንግድ ልውውጥ ጋር ተያያዞ ከኢትዮጵያ ስለወጣው ዶላር ፍሮብስ የተባለው መጽሄት ያቀረበውን ሃተታ ነው። ፍሮብስ ወያኔ ስልጣን በቆየባቸው 17 አመታት 17 ቢልዮን ዶላር በህገ ወጥ መንገድ ከሃገር መውጣቱን አስነብቦ ነበር። ይህ በአመት አንዲ ቢሊየን ዶላር የሚደርስ ዘረፋ ከኢትዮጵያ ህዝብ ወያኔዎች የዘረፉትን ሃብት ብዛት በጥቂቱ ብቻ የሚገልጽ ነው። በተጭበረበረ ደረሰኝ ዶላር የሚያወጡት ሁሉም ወያኔዎች ስላልነበሩ 17 ቢሊዮኑ በወያኔዎች ብቻ ካገር የወጣ አድርገን ማየት አንችልም።

በሌላ መንገድ ግን በቀጥታ በወያኔዎች ተዘርፎ ካገር የወጣ ገንዝብ ከ50 እና 60 ቢሊዮን ዶላር በላይ ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል። ሁለቱን የዚህ ገንዘብ ምንጮች እንጥቀስ። ወያኔ ኢትዮጵያውያን ከመላው አለም ከባንክ ውጭ ገንዝብ ለዘመዶቻቸው የሚልኩባቸውን መንገዶች በሙሉ ለብቻው መቆጣጠር ችሎ ነበር። በአለም ባንክ ግምት የኢትዮጵያ ዳያስፖራ በአመት ከ3 እስከ 4  ቢሊየን ዶላር ወደ ሃገር ቤት እንደሚልክ ይነገራል። አብዛኛውን ገንዘብ ባንክ ከሚሰጠው በላይ ህገወጥ በሆነ መንገድ ሲመነዘሩ የነበሩ የወያኔ ባላስልጣናትና ሸሪኮቻቸው ነበሩ። ዛሬም አላቆመም።  ከዚህ ገንዘብ በአማካይ በአመት አንድ ቢሊዮን ዶላር መመንዘር ከተቻለ በ30 አመት 30 ቢሊየን ዶላር ወያኔዎች ወደ ውጭ ማሸሽ ችለዋል። በዚህ ላይ ስልጣናቸውን በመጠቀም ወያኔዎች በሱዳን እና በጅቡቲ በኩል ያለማንም ጠያቂ በቀጥታ እያወጡ የሸጡትን ሰሊጥ ወርቅና ሳፋየር ሲንደምርበት ዘረፋው ምን ያህል አስፈሪ እንደሆነ ያሳየናል።

በህገወጥ መንገድ እየወጣ ይሸጥ የነበረው ሰሊጥ ኢትዮጵያ ከቡና ከምታገኘው ከነበረው የውጭ ምንዛሪ የሚበልጥ እንደነበር ስለእዚህ ህገ ወጥ ንግድ እውቀት ያላቸው ሰዎች ይናገራሉ። ይህ በህገ ወጥ መንገድ በአውሮፓና በአሜሪካ ባንኮች የተከማቸ ገንዘብ ወያኔዎችና ዘርማንዘሮቻቸውን የድሎት ህይወት እንዲኖሩ ማስቻል ብቻ ሳይሆን፣ ገንዝብ ማንንም ምንም መግዛት በሚችልባቸው የምእራብ ሃገራት፣ የመንግስት ባላስልጣናትን ፖለቲከኞችን፣ የሚድያ ተቋማትና ጋዜጠኞችን ሌሎችንም ተጽእኖ ማሳደር የሚችሉ ግለሰቦችን መግዛት አስችሏቸዋል። የአሜሪካ መንግስት ለጥቅሙ ሲል ወያኔን በመደገፍ ከወሰደው ኢትዮጵያን የማጥቃት እርማጃዎች በተጨማሪ ወያኔዎች በጃቸው ያለውን ገንዘብ በመጠቀም የአሜሪካ መንግስት ይህን ውሳኔ እንዲወስን ተጽእኖ አሳዳሪ ግለሰቦችን በመግዛት የሚፈልጉትን ማስወሰን እንደቻሉ መታወቅ አለበት።

ሶስተኛው የትግራይ ዳያስፖራ ነው። የትግራይ ዳያስፖራ ስንል ወያኔ ስልጣን ላይ ከወጣ በኋላ ከወያኔ ጋር በቅርበት በተሳሰረ መንገድ የተፈጠረውን ዳያስፖራ ማለታችን ነው። ይህ አካል በውጭ ሃገር የተፈጠረለት የመማር፣ በድሎት የመኖር እድል በከፍተኛ ደረጃ ከወያኔ ጋር ተያይዞ የመጣ መሆኑ ይታወቃል። ቁጥሩ ቀላል ያልሆነ በቀጥታ ከወያኔ ከፍተኛ እና መካከለኛ ደረጃ መሪዎች ጋር በቀጥታ በቤተሰብነት በዝምድና የተሳሰረ ነው። ይህ አካል ከየትኛውም በውጭ ከሚኖር የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በላይ የገንዘብና የድርጅት አቅሙ የጎለበተ ነው። ወያኔ የከፈተውን ጦርነት በዲፕሎምሲና በገንዝብ ምን ያህል ለመደገፍ እንደሚንቀሳቀስ ታይቷል። የትግራይ ዳያስፖራ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ተቃውሞ ሰልፍ የወጣበት ምክንያት ውግንናው፣ ጸረ ሰላም ከሆነው ሰላም ፈላጊዎችን ተንበርካኪዎች በሚል ከፈረጀው የትግራዩ የወያኔ ቡድን ጋር ስለሆነ ነው። ዳያስፖራው የሰላም ስምምነቱን ተቃውሞ ያወጣው መግለጫ ላይ የሰላም ስምምነቱን የፈረሙትን ግለሰቦች “ተንበርካኪ” በሚል ቃል መግለጹ የተራ አጋጣሚ አይደልም።

ከላይ በተጠቀሱት ሶስት ዋልታዎች ላይ የቆመው የጸረ ሰላም ሃይሉ የዲፕሎማሲ ጉልበት ሊያስፈጽማቸው የተነሱት ግልጽ አላማዎች አሉት። እነዚህ አላማዎች ከአሜሪካ መንግስት ጋር በቅርበት በመነጋገር የተቀረጹ የአሜሪካንን መንግስት ድጋፍ የሚያገኙ ናቸው።

የመጀመሪያው ወያኔን እንደ ድርጅት አትርፎ፣ የትግራይ ህዝብና የኢትዮጵያ ህዝብ በተጠያቂነት እንዲቀርቡለት የሚፈልጋቸውን ነባር የፖለቲካ የደህንነትና ወታደራዊ አመራሮች ከተጠያቂነት ነጻ ማድረግ፣

ወያኔ በኢትዮጵያ ፖለቲካና ኢኮኖሚ ውስጥ የነበረውን ያልተገባ ድርሻ በአዲስ መልኩ ማስቀጠል በተለይ የወያኔ ባልስጣናት በዘረፋ በሃገር ውስጥ ያካበብቱ ሃብት እንዳይነካባቸው ማድረግ። ወያኔዎች ጥቃት ሰንዝረው መሳሪያውን በገፈፉትና ሰራዊቱን ባረዱበት የመከላከያ ተቋም ውስጥ መልሶ ማካተት፣

በኢትዮጵያ በኤርትራ መንግስት መሃከል ተፈጥሮ የነበረው መልካም ግንኙነት እንዲሻክር፣ እንደቀድሞው ኢትዮጵያና ኤርትራ በጎሪጥ የሚተያዩ፣ ቢቻልም ወደሌላ ጦርነት እንዲገቡ ማድርግ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በአሜሪካኖች ጉያ ውስጥ የተወሸቀ የአሜሪካኖችን ጥቅም አስከባሪ መንግስት እንዲሆን ነው። በመጪው ሳምንት ውስጥ የአሜሪካው መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኢትዮጵያን የሚጎበኘው እነዚህ ከላይ የተጠቀሱ አላማዎች ለማሳካት ነው። ለዚህ እንደካሮት የሚያገለግሉ የገንዝብ እርዳታ፣ ወደ አግዋ መመለስ የመሳሰሉ ጉዳዮችን ይዟል። በዱላ መልኩ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ቀውስ ማባባስ የሚችል መሆኑን መጠቆም ነው።   

  • እንዴት ከዚህ ችግር መውጣት ይቻላል።

በቅድሚያ ከትግራይ ጋር የተያያዘውና ትግራይ ውስጥ የሚታየው ችግር የትግራይ ህዝብ ብቻ ሳይሆን የተቀረው የኢትዮጵያም ህዝብም ችግር መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል። ጦርነቱና ከጦርነቱ ጋር የተፈጠረው መመሰቃቅል ሁሉንም ህዝብ ሁሉንም ክልል ያዳረሰ ነው። ሞትና መፈናቀል፣ መዘረፍ መዋረድ መደፈር መጠኑ ይለያይ እንጂ በሁሉም የሃገሪቱ ክልሎች ተከስቷል። የኢኮኖሚው ምስቅልቅልም፣ ህዝብን ለከፍተኛ ስቃይ እየዳረገ የሚገኘው የኑሮ ወድነት፣ እየተስፋፋ የሄደው ሌብነት ግርግር ለሌባ ይመቻል እንደሚባለው ጦርነቱ በፈጠረው የተመቻቸ ሁኔታ ወስጥ የተስፋፋ ነው። በዲፕሎማሲው መስክ እየመጣ ያለው ጫና ቀጠናውን ሌላ ትርምስ ውስጥ የሚከት ነው።  

ከጦርነቱ ርቆ በሃገር ውስጥና ከሀገር ውጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ይህ ጦርነት በሞት የቀጠፈው የሰው ህይወት ብዛት ትግራይ ውስጥ ደርሷል ከሚባለው በመቶ ሽዎች ከሚቆጠር እልቂት ወጭ ሌላ መረጃ የለውም። የሚሰጠው ስለሌለ። በሚገባ አልተነገረም እንጂ እልቂቱ በሌሎች ቦታዎችም አሰቃቂ ነበር። በቅርቡ በአማራ ክልል ከጦርነቱ ጋር በጦር ሜዳ ላይ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች መርዶ ለቤተሰባቸው ተነግሮ ነበር። በምስራቅ ጎጃም ብቻ የ8020 ሰዎች ሞት መርዶ ተነጓሯል።  ቀደም ብሎ የተነገረ በምስራቅ ጎጃም ዞን ውስጥ ከሸበል በረንታ ወረዳ ብቻ ከዘመቱ ሚሊሻዎች መሃል በአንድ እለት በአቀስታ ግንባር ዶባ ተራራ ላይ 19ኙ ተሰውተዋል። እነዚህ የሚሊሺያ አባላት ያለአባት ትተዋቸው የሄዱ የታዳጊ ልጆቻቸው ብዛት 96  ነው። በመላው ሃገሪቱ ከዚህ ጦርነት ጋር ብቻ በተያያዘ ያለቀውን የህዝብ ብዛትና ጥሎ ያለፈውን ሰቆቃ ከእነዚህ ሁለት መረጃዎች መገመት ይቻላል። በመሆንም የኢትዮጵያ መንግስት የሰላም ስምምነቱ ሂደት በተመለከተ ለህዝብ ወቅታዊ መረጃ የማቅረብ ግዴታ አለበት።   

የኢትዮጵያ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የሰላም እጦት ቀውሶች እርስበርስ የተቆራኙ ናቸው። ዝርዝሩ ወስጥ መግባት አያስፈልግም። የዚህ ጽሁፍ አላማ በትግራይ ውስጥ ባለው ችግር ላይ ያተኮረ በመሆኑ ወደዛው እመለሳለሁ።

የትግራይ ብሎም የኢትዮጵያ ህዝብ ከሚገኝበት ችግር እንዲወጣ ከተፈለገ የኢትዮጵያ መንግስት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት በተሰጠው ስልጣን የሚከተሉትን እርምጃ ቢወስድ በሚል ምክረ ሃሳቤን አቀርባለሁ። ምከረ ሃሳቡን ለትግራይ በጎ የሚመኙ በትግራይ ውስጥ የሚገኙ የትግራይ ወጣት ፖለቲከኞች እንደሚደግፉት ማሳወቅ እፈልጋለሁ።

ሀ) በፖለቲካ ዘርፉ

የፖለቲካው መፍትሄ በትግራይ ውስጥ ዛሬ የትግራይ ህዝብ ወያኔን እንዴት ያየዋል፣ በወያኔ አመራራ መሃከል ጸረ ሰላም የሆነው ሃይል ምን እየሰራ ነው፣ ሰላም እንዲስፍን የሚፈልገውስ አካል ምን እያደረገ ነው ከሚለው የወቅቱ የትግራይ ሁኔታ ጋር የተገናዘበ መሆን አለበት።

በፖለቲካ መስኩ፣ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሰረት የሽግግር መንግስት የማቋቋም ዋናው ሃላፊነት የኢትዮጵያ መንግስት ስለሆነ መንግስት የማቆሙን ስራ በተደራጀ መንገድ ለግልና ለቡድን ጥቅማቸው መቆጣጠር ከሚፈልጉ የተደራጁ አካላት ነጻ ማድረግ መቻል አለበት። እስካሁን የተሄደበት መንገድ ህዝብ አምሮ የሚጠላቸውን እና የሚቃወማቸውን በዚህ አጋጣሚ ከጫንቃው ላይ ሊያነሳቸው የሚፈልጋቸው የወያኔ አመራሮች የልብ ልብ የስጠ ለለውጥ የተነሳሳውን በወያኔ ውስጥ ያሉትን ወጣት አመራሮችና ህዝቡን እራሱን ተስፋ የሚያስቆርጥ አካሄድ ባስቸኳይ መቆም መቻል አለበት።

አሁን በትግራይ ያለውን ሁኔታ ለመቀየር በቅድሚያ በሽግግር መንግስቱ ፈጠራ ሂደት፣ ትልቁን ስልጣን እና መብት፣ የመከራው ዋናው ገፈት ቀማሽ የሆነው የትግራይ ህዝብ የሚቆጣጠረው እንዲሆን ማድረግ ይገባል። የኢትዮጵያ መንግስት ቀድሞ የሚያውቃቸውን ወይም እራሱ ያደራጃቸውን ወይም በራሳቸው የተደራጁ የጥቂት ግለሰቦችን እና ቡድኖችን ከማመን የትግራይ ህዝብን ማመን የተሻለ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልገዋል። የትግራይ ህዝብ ሰላምና ፍትህ እንዲያገኝ ከገባበት የህይወት መከራ እንዲወጣ በንጽህና ከሚታገሉ ወጣት ፖለቲከኞች ጋር ተቀራርቦ መስራት የሚኖረውን ጠቀሜታ መረዳት ያስፈልገዋል።

አሁን ባለው ሁኔታ የብልጽግና መንግስት ከዚህ ቀደም እንዳደረገው የራሱን የብልጽግና ሰዎች የትግራይ ጊዜያዊ አሰተዳዳሪዎች አድርጎ መሰየም አይችልም። የዚህ አይነቱ ሙከራ ተሿሚዎቹን እንደ ወራሪ ሃይል  አድርጎ ህዝብ እንዲያቸው በማድረግ ከዚህ ቀደም የተከሰተው የፖለቲካ ችግር እንዲከሰት ያደርጋል። ለጸረ ሰላም ወያኔዎችም ተቃውሞና አሻጥር የሚመች ሁኔታ ይፈጥራል።

በሌላ መልኩ የብልጽግና ሰዎች የቀድሞ ጓደኞቻቸውን መልሰው የትግራይ ጊዚያዊ መንግስት እንዲቆጣጠሩ የሚያደርግ ሂደት ከፈቀዱ በትግራይም ይሁን በተቀረው ኢትዮጵያ ሰላም የመጥፋቱ ሁኔታ እንዲቀጥል ከማድረግ እንደማይመለሱ ለማሳየት ሞክረናል። ከማያውቁት መልአክ የሚያውቁት ሰይጣን ይሻላል በሚል ብሂል የሚመራ የሚመስለው የማእከላዊ መንግስት አካሄድ ሰይጣን ሁል ጊዜም ሰይጣን መሆኑን መረዳት ያስፈልገዋል።

የፕሪቶሪያው ስምምነት መንግስት በሃገሪቱ የደሃ ልጆች እጃቸው በደም የተጨማለቁ ግለሰቦችን መልሶ ወደ ስልጣን ማምጣት የሚል አንቀጽ አልተካተተበትም። እነዚህ ግለሰቦች ድጋሚ እድል ቢያገኙ በሃገርና በህዝብ ላይ ከሚያስከትሉት ውድመት በተጨማሪ የጥፋት እጃቸውን በማን ላይ በቅድሚያ ለማንሳት ሲዶሉቱ እንደሚውሉ የአዲስ አበባው መንግስት አልሰማ ከሆነ ልንነግረው እንችላለን። በህጻናት ጓንቲ በሚያሽሞነሙኗቸው፣ ከዚህ ሁሉ እልቂትና ውድመት በኋላ ምንም እንዳልሆነ በሚያመስል ደረጃ በሳቅና በፈገግታ የሚያቅፏቸው የወይን ብርጭቋቸውን እያነሱ ለጤናቸው በሚጠጡላቸው የብልጽግና አመራሮች ላይ ነው። አሁንም በድጋሚ ሰላም ፈላጊው በወያኔ ውስጥ ያለው የአመራር አካል የሚያነሳው ጥያቄ “መቼ ነው የፌደራል መንግስቱ በፕሪቶሪያው ስምምነት የተሰጠውን የሽግግር መንግስት የማቆም ስልጣን ተጠቅሞ መብቱ የሌላቸውን የወያኔ አመራሮች ጊዜያዊ መንግስት የማቆም ሆነ ሂደቱን የማስጀመር መብት የላችሁም የሚላቸው? እነዚህ ሃይሎች እየተሰባሰቡ ደብረጽዮን ፕሬዚደንት ጻድቃን ምክትል አድርገናል እያሉ መግለጫ ሲያወጡ ዝም ብሎ የሚያያቸው እስከመቼ ነው? የሚሉ ናቸው?

በሌላ በኩልም የፌደራል መንግስቱ የትግራይን ጊዜያዊ መንግስት በወታደር እጅ ማስያዝ አይችልም ። በወታደራዊ ስሌት አደገኛ ነው።  ለከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ፣ ለወያኔ አመጽ የተመቻቸ ሁኔታ ፈጣሪ ስለሆነ ሊታሰብ አይገባውም።

ያለው አማራጭ አንድና አንድ ብቻ ነው። በየቀበሌው  ኗሪ የሆነው የትግራይ ህዝብ በአካል በማሰባሰብ በጊዚያዊነት የሚያስተዳድሩትን እየመረጠ በሁሉም እርከኖች እንዲሾማቸው ማድረግ።  ይህን አሰራር የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት በተቆጣጠረባቸው ቦታዎች በሙሉ በስራ ላይ መዋል የሚቻል ነው። እያንዳንዱን ቀበሌ በጊዜያዊነት የሚያስተዳደሩ፣ በወረዳ ደረጃ የሚወከሉ ሰዎቹን እየመረጠ፣  ወረዳቸዎችም  በዞን የሚወከሉትን እየመረጡ ዞኖችም ትግራይ የሚያስተዳድሩትን ሰዎች መምረጥ የሚችሉበትን ብዙ ወጪ ግዜና ጉልበት የማይጠይቅ አሰራር በስራ ላይ ማዋል ይችላል። ይህ አሰራር ወያኔ ስልጣን እንደያዘ በኢትዮጵያ ውስጥ ተግባራዊ ተደርጎ በጊዜያዊነት በደንብ ሰርቷል።

ከዚህ የአስተዳደር ስራ ጋር እያንዳንዱ ቀበሌ ሰላሙን የሚያስጠብቁለትን ራሱ የመረጣቸውን ማእከላዊ መንግስት የሚያስታጥቃቸውን ግለሰቦች እንዲመርጥ በማድረግ ማስታጠቅና ማሰልጠን ነው። ይህን አሰራር በመላው ትግራይ ለመፈጸም የሰላምና የደህንነት ችግር ካለ፣ ችግር በሌለባቸው ቦታዎች መጀመርና በሂደት ወደሌሎች ከባቢዎች ማስፋት ይቻላል። በዚህ መንገድ ለተመረጡ የአስተዳደር እርከኖች በጀት መልቀቅና በፍጥነት መንግስታዊ አገልግሎቶች እንዲጀመሩ ማድረግ ነው። ይህ ተግባር እንዲሳካ ለእውነተኛ ሰላም የቆሙ በወያኔ አመርራና ከዛም በታች ባሉ የድርጅቱ እርከኖች ውስጥ ያሉ ተባባሪዎችን ድጋፍ መንግስት በቀላሉ ማግኘት ይችላል።  የመከላከያ ሰራዊቱ ባልገባቸው ቦታዎች መግባት የሚቻልበትን ከፕሪቶሪያው ስምምነት ጋር ተያይዥነት ያላቸውን ወታደራዊ ውሳኔዎች ተፈጻሚ በማድረግ በመላው ትግራይ የጸጥታ ሃላፊነቱን መረከብ ነው። ይህን ለማድረግ፣

ለ) በወታደራዊ ዘርፉ መወሰድ የሚገባቸው እርምጃዎች

  • የወያኔ መሪዎች የትጥቅ መፍታቱን ስምምነት ጥሰው በተለያዩና በሚታወቁ ቦታዎች ያከማቿቸውን መሳሪያቸው በአፋጣኝ እንዲያስረክቡ ማድረግ
  • በተለያዩ በሚታወቁ ቦታዎች አሰባስበው አሁንም ስልጠና የሚሰጧቸውን የሰራዊት አባላት ስልጠና አቁመው እነዚህ የሰራዊት አባላት መንግስት በሚያዘጋጀው በቀላሉ በሚታዩና መደረስ በሚችሉ ካምፖች እንዲሰባሰቡ ማድረግ፣
  • ለሽብር ስራ መልምለው የሚያዘጋጇቸውን ሰዎች ስልጠና እንዲያቆሙና አባላቱ እንደሌሎች የትግራይ ሰራዊት በካምፕ እንዲገቡ፣
  • የትግራይን ሰላም ማረጋጋትና ህግ የማስከበር ስራ በሁሉም አካባቢዎች በህዝብ የተመረጡ የሰላምና መረጋጋት አባላት በሃላፊነት እንዲመሩት ማድረግ፣ በእነዚህ አባላት ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ በወንጀል የተካፈሉ የመከላለካይ የደህንነትና የፖሊስ አባላት መሳተፍ የሚችሉ መሆናቸውን ግልጽ መመሪያ ማስቀመጥ

ሐ) በኢኮኖሚ ዘርፉ መወሰድ የሚገባው እርምጃዎች

  • ህዝብ ጊዚያዊ አስተዳደር ባቆመባቸው አካባቢዎች በሙሉ የመንግስት አስተዳደር ማስጀመር የሚቻልበትን በጀት በቀጥታ በመመደብ ስራ እንዲጀምሩ ማድረግ። ጤና ጣቢያዎች ት/ቤቶች ስራ እንዲጀመሩ ጊዚያዊ መንግስቱ መቀሌ ላይ እስኪቋቋም መጠበቅ አያስፈልግም።
  • በትግራይ ውስጥ ህገ ወጥ በሆነ መንገድ የተሰበሰበ የውጭ ምንዛሪና የሃገር ውስጥ ገንዘብ ወርቅና ሌሎች ማእድናት ተሰብስቦ በጦርነት ለወደሙ አካባቢዎችና በጦርነቱ የተነሳ አሳዳጊ ላጡ ህጻናት እንዲሁም ጧሪ ቀባሪ ላጡ አረጋውያን ወላጆች በስራ ላይ እንዲውል ማድረግ። ይህ ሃብት ከዚህ አላማ ውጭ ለሌላ ተግባር ወደ ሌላ ቦታ የማይሄድ መሆኑን ለትግራይ ህዝብ ግልጽ ማድረግ።
  • ህገወጥ በሆነ መንገድ ጦርነቱን ሽፋን ተደርጎ፣ በተዘረፈ ገንዝብ የተገዙ የህዝብ መሬቶችን ወደ ህዝብ ማስመለስ።
  • በተቻለ ፍጥነት የገበያው ልውውጥ ለትንንሽ ግብይት ካልሆነ በስተቀር ሌላውን በባንክ በኩል እንዲሆን ማድረግ፣ ከተወሰነ ገንዘብ በላይ በካሽ ገንዘብ ይዞ መገኘት የሚያስጠይቅ ማድረግ፣

መ) በማህበራዊ ዘርፉ

በትግራይ ውስጥ የሚገኝ ሰላም ከማንም በላይ የሚመለከተው የሚጠቅመው ራሱን የትግራይን ህዝብ ስለሆነ የትግራይን ህዝብ ያገለለ የሰላምና መረጋጋት ስራ የህግ ማስከበር ስራ ሊኖር አይገባውም። በመሆኑም፤

  • በካድሬዎች የተሞላውና በጉቦ የነቀዘው ፍርድ ቤት በጊዚያዊነት አግዶ ፍትህ ከቀበሌ ጀመሮ ህዝብ በመረጣቸው የሸንጎ አባላት በሁሉም እርከኖች እንዲሰጥ ማድረግ፣
  • የህዝቡን ሰላምና መረጋጋት የማስጠበቁ ሃላፊነት ህዝብ በመረጣቸው የሰላምና መረጋጋት ኮሚቴ አባላት አማካኝነት በከፈተኛ የህዝብ ድጋፍ ተፈጽሚ በማድረግ ዘረፋን፣ ወሲባዊ ጥቃትን ሁከትና ግድያን ማናቸውም ህገወጥ የመሳሪያ የገንዝብና የሰዎችን ዝውውር መቆጣጠር፣
  • የፌደራል መንግስቱ አካል ሆነው በተለያዩ የስራ መስኮች የተሰማሩ አካላት በከፍተኛ ዲሲፕሊን እና ህዝብ አክባሪነት ከህዝቡ ጋር ተቀራርበው የሚሰሩበትን ሁኔታ መፍጠርና ስራዬ ብሎ እንቅስቃሴያቸውን መቆጣጠር። ካሁኑ የጀመረ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከቁጥጥር ውጭ ሊወጣ የሚችል ከማእከላዊ መንግስት በተመደቡ አካላት ዘንድ የሚታይ ጉቦኝነት ህዝቡን ከማስመረሩ በፊት በአጭር እንዲቀጭ ማድረግ።
  • በተለይ በሙስና ስራ የተካኑና ሙስንን በመጠቀም የመንግስት ባለስልጣናትን የማጥመድ ልምድ ካላቸው የወያኔ አመራሮችና ወኪሎቻቸው፣ የፌደራል መንግስቱ የመከላከያ፣ የደህንነትና የፖሊስ አመራሮች እንዲርቁ ጥብቅ መመሪያ መስጠትና መቆጣጠር። ካሁኑ እየታዬ ያለውን አደገኛ ከሆኑ አካላት ጋር የሚደረግ መቀራረብ ባስቸኳይ ማስቆም።
  • በፕሪቶሪያው ስምምነት የተቀመጠውን የሽግግር ሂደት ፍትህ የትግራይን ህዝብ ባካተተ መልኩ በፍጥነት ተግባራዊ የሚሆነበትን መንገድ አቅዶ መንቀሳቅስ። 

ሠ) በዲፕሎማሲ ዘርፉ

ትልቅ ጥንቃቄ የሚያስፈገው ዘርፍ ነው። በአለም ላይ የተፈጠረው አዲስ የሃይል አሰላለፍ፣ በተለይ አሜሪካንን ብቸኛ ለእለ ሃያል ሃገር ያደረገው ዘመን ማብቃት፣ አሜሪካኖችን የሚይዙትና የሚጨብጡትን እያሳጣቸው ነው። የአፍሪካ ቀንድ አንዱ ከተጽኖአቸው ውጭ እንዲወጣ የማይፈልጉት ስትራተጂክ ቀጠና ነው። ከወያኔ ጋር የሙጥኝ ብለው የተጣበቁበት አንዱ ምክንያት ወዳጃቸው ወያኔ ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ከወጣ በዚህ ቀጠና በሎሌነት የሚያገለግለን አካል አይኖረንም የሚል ስጋት ነው። የአሜሪካኖች አካሄድ ኢትዮጵያን በኢኮኖሚና በዲፕሎማሲ መስኮች እየጨመቁ ወያኔን በኢትዮጵያ ውስጥ ተጽእኖ ፈጣሪነቱ እንዲቀጥል ማድረግ ነው። አሜሪካኖች  በእርዳታ ስም የሚሰጡትን ገንዘብ ለመልቀቅ፣ ከአለም አቀፍ ተቋማት ኢትዮጵያ ብድር እንድታገኝ ወደ አገዋ እንደትመለሰ ቅደመ ሁኔታ ማስቀመጣቸው አይቀርም። ይህ ቅድመ ሁኔታ ደግሞ ወያኔን እንደ ድርጅት ማዳን ነው። ወያኔ የሚፈልገውን በተለይ ወልቃይትን በወያኔ አገዛዝ ስር መልሶ እንዲገባ ህገ መንግስቱን እያጣቀሱ መሞገት ነው። በኢትዮጵያና በኤርትራ መሃከል ያለው ግንኙነት እንዲሻክር ነው። ቢቻላቸው የኤርትራን መንግስት ቀድሞ ሲያደርጉት ወደነበረው አፈና ከበባ ውስጥ ማስገባት ነው። ኤርትራ ከሩሲያና ከቻይና ጎም በመቆም ለወሰደቻቸው አቋሞች ዋጋ እንድትከፍል ማድረግ ነው። በመጨረሻም ትልቅ ስትራተጂያዊ ጠቀሜታ ያላትን ኤርትራን መንግስቷን በመጣል የአሜሪካ አሻንጉሊት በሆነ መንግስት መተካት ነው።

የሚያሳስቡ ነገሮች እየታዩ ነው። አሜሪካኖች የሚፈልጉትን በመስጠት ኢትዮጵያ ከገባችበት ሁለንተናዊ ቀውስ ፋታ ታገኛለች በሚል የተሳሳተ ስሌት ሊሰራ የሚችል ነገር የከፋ አደጋ ይዞ ሊመጣ እንደሚችል መታወቅ ይኖርበታል። በአለም ላይ የተፈጠረው በሁለት የተከፈለው ጎራ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚሆነውን ሁሉ አሜሪካኖች በከፍተኛ ትኩረት እንዲከታተሉት እንዳደረገ ሁሉ የሩሲያውና የቻይናውም ጎራ ይከታተሉታል።

ቻይና እና ሩስያ በተከታታይ ምእራባውያኑ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ የኢትዮጵያ ጉዳይ እንዲነሳና በኢትዮጵያ ላይ ጎጂ ውሳኔ እንዲወሰን የተደረገውን ተደጋጋሚ ጥረት ኢትዮጵያን ወግነው አክሸፈዋል። ኤርትራ በክፉ ቀን ከኢትዮጵያ ጎን በመቆም መስዋእተነት ከፍላ አለኝታነቷን አሳይታለች። እነዚህ አካላት የኢትዮጵያ መንግስት ውለታቸውን ዘንግቶ የአሜሪካ ጉዳይ አስፈጻሚ ወደ መሆን ሲሄድ ዝም ብለው የሚያዩት አይሆንም። የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ አንዱን መምረጥ ይኖርበታል። አሜሪካኖች የአጭርና የረጅም ጊዜ ጥቅሞቻቸውን አስልተው ኢትዮጵያ እንድትፈጽም የሚፈልጓቸውን ነገሮች መፈጸም ወይም አሜሪካኖች የሚጠይቋቸውን ፍትሃዊ ያልሆኑ ጥያቄዎች አልቀበልም በማለት መከፈል የሚገባውን መስዋእትነት ለመክፈል መዘጋጀት።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ  የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ እየሄደበት ያለው መንገድ አሳሳቢ ነው። ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲ ስራዋ ሩቅ ካሉ ሃገሮች ይልቅ በአካባቢዋ ካሉት ጎረቤት ሃገሮቿ ጋር የሚኖራት መልካም ግንኙነት ዘለቄታ ጥቅሟን የሚያስከብር መሆኑን ማወቅ ይኖርባታል። ለአሜሪካኖች ተብሎ ከየትኛውም ሃገር ህዝብ በላይ የኢትዮጵያ ወዳጅ ከሆነ ከኤርትራ መንግስትና ህዝብ ጋር መቃቃር ለኢትዮጵያ ትልቅ ጉዳት የሚያስከትል ነው። ኤርትራ አሜሪካ ብቸኛዋ ልእለ ሃያል ሃገር በነበረችበት ወቅት ተገልላ ስትኖር ከነበረበት አፈና የሚያወጣ አዲስ የአለም ስርአት ተፈጥሮላታል። እሷም ጥቅሟን ግምት ውስጥ በማስገባት አዲስ በተፈጠረው የአለም ጎራ ውስጥ የወሰደቻቸው በብልሃት የተሞሉ አቋሞች ትልልቅ ሃያላን ወዳጆች እንድታፈራ አድርጓታል። ዛሬ አሜሪካኖች ኤርትራን ከዚህ ቀደም ሲያደርጉት እንደነበር ማድረግ የሚችሉበት ሁኔታ የለም። የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ይህን ሃቅ ግምት ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል። ዲፕሎማሲው አሜሪካ ላይ መለጠፍ ሳይሆን ከአሜሪካ ተጽእኖ እንዴት መላቀቅ ይቻላል በሚል ስሌት መመራት አለበት። ኢትዮጵያ በጦርነቱ ወቅት ከአሜሪካን ተጽእኖ ራሷን ለማላቀቅ ተፈጠሮላት የነበረውን እድል በማባከኗ ወደፊት የምናየው ይሆናል ብዙ ዋጋ ትከፍልበታለች። ሃቁ በአሜሪካ ተጽእኖ ስር ወድቀው የበለጸጉ፣ ሰላም ያገኙ፣ ዴሞክራሲያዊ ስርአት የገነቡ፣ የህዝባቸውን መብቶች ያስከበሩ ታዳጊ ሃገሮች ቀርቶ አንድም ሃገር የለም። ይህን ሃቅ አገናዝቦ ብልሃትና ጥበብ በተሞላው መንገድ የዲፕሎማሲ አቅጣጫቻን ማስተካከል ይገባል። ይህ ጉዳይ እራሶች አሜሪካኖቹ እንደሚሉት “እንደሚናገሩት ቀላል እንዳልሆነ” ይገባኛል። ከባድ ያደረግነው እኛው ራሳችን መሆናችንን መገንዘብ ግን ይገባናል።

አንዳርጋቸው ጽጌ

__

በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena 
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ግልጽ ደብዳቤ ለዶ/ር ዓቢይ አህመድ አሊ፣ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስቴር

ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ

አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
የካቲት 29 ቀን 2015 ዓም (March 8, 2023)

ለተከብሩ ዶ/ር ዓቢይ አህመድ

ለኢትዮጵያ ሀገራችን ትውልድና ታሪክ ተሻጋሪ የሆነ ለውጥ ያመጣሉ በሚል ተስፋ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ እርስዎንና መንግሥትዎን እስከዛሬ ድረስ በሙሉ ልብ ድጋፉን በመስጠት፤ ወደ እናት ሀገሩ የእርዳታ ገንዘብ በመላክ፤ መዋዕለ ንዋዩን በማፍሰስ፤ በድርቅና በግጭት በመፈናቀል ብዙ ጉዳት የደረሰባቸዉን ዜጎቻችንን በመርዳትና መልሶ በማቋቋም፤ በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት በሞያ የተደገፈ ምክር በመስጠትና በቁሳቁስ በማገዝ ዳያስፖራው ለሀገሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል። ከእነዚህ በተረፈ፣ ለዐባይ የህዳሴ ግድብ ስኬት ገንዘብ በማዋጣትና በዲፕሎማሲው መስክ ድጋፍ በመስጠት ሰፊ የሆነ ያልተቋረጠ እገዛ አድርጓል። ሀገራችን ኢትዮጵያ በሰሜኑ የትግራይ ጦርነት ሳቢያ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ በገባችበት ወቅትም ዳያስፖራው ከእርስዎ፣ ከኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከመከላከያና የጸጥታ ኃይሎች ጎን በመቆም፣ ሀገራችንን ለማዳን በተደረገው ከፍተኛ እርብርብ፣ በተለይም በዓለም አቀፉ መስክ ግንባር ቀደም በመሆን በዲፕሎማሲና ሕዝብ ግንኙነት ዙሪያ ዳያስፖራው ያደረገውን ታላቅ ተጋድሎና አስተዋጽኦ ምንግዜም ታሪክ አይረሳዉም።

በጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. (Nov 4, 2020) ህወሐት በሰሜን እዝ ላይ ድንገተኛ ጥቃት በመክፈት፣ በሺህ የሚቆጠሩ ንጹሀንን በተኙበት ሳይቀር ጨፍጭፎ፣ በአማራና አፋር ክልሎችም በዘመተበት ወቅት፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ አይታው የማታውቀው የዲፕሎማቲክ ዘመቻ፣ የኢኮኖሚ ማዕቀብ እና ከምዕራባውያን እና የአለም አቀፍ ሚዲያዎች ከፍተኛ ጫና ገጥሟት ነበር። ይህን ለመቋቋም በዓለም ዙሪያ ያለው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ከጫፍ እስከጫፍ በመነሳትና በየሲቪክ ማህበሮቻችን በመደራጀት፣ ከፍተኛ የሆነ የዲፕሎማቲክ እንቅስቃሴ አድርገን፣ የጥብቅና ዘመቻዎችን በማደራጀት፣ ዲፕሎማሲያዊ ድጋፍ በመስጠት፣ በተለይም የዩናይትድ ስቴትስ ኮንግረስን፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን እና ሌሎች አለም አቀፍ አካላትን ሎቢ በማድረግ ታላላቅ የዲፕሎማሲ ስኬቶችን አስመዝግበናል። በተጨማሪም ከሰላም ደጋፊ “ፓን-አፍሪካን” አጋሮቻችን ጋር በመተባበርና፤ ትግላችንን በማቀናጀት የ“#በቃ” (#NOMORE) ሰፊና ሕዝባዊ ንቅናቄ በዓለም ዙሪያ የህወሐትን የሀሰት ፕሮፓጋንዳ በማክሸፍ፤ የኢትዮጵያ ችግር የአፍሪካ ሁሉ ችግሩ ሆኖ እንዲታይ፤ የምዕራብ አለም ዜጎች አብረውን እንዲቆሙና ድምጽ እንዲሆኑ ታላቅ አስተዋጽዎ አድርገናል። በአምስት አህጉራትና ከሰላሳ ሁለት በላይ አገሮች ውስጥ ታሪካዊ ታላላቅ ሰለማዊ ሰልፎችን በማድረግ፣ ኢትዮጵያ በአለም አደባባይ የተነፈገችውን ትኩረት ድምጽ ልንሆንላት ችለናል።

እኛ፥ ከእዚህ ደብዳቤ በታች የፈረምነው ዓለም አቀፍ የዳያስፖራ ድርጅቶች፣ ግንባር ቀደም መሪ በመሆን ሌትና ቀን ያለእረፍት በመታገል፤ ለሀገራችን ኢትዮጵያ በምንችለው ሁሉ አቅም፣ በእዉቀት፣ በሞያ፣ በገንዘብ፣ በጉልበትና በጊዜ ከፍተኛ መስዋእትነትን የከፈልን ነን። በከፍተኛ ሀገር ፍቅር ስሜትም ተነሳስተን ይህን አስተዋጽኦ ለማበርከት በመቻላችን ልዩ ኩራት ይሰማናል። ይሁን እንጂ፣ ይህን ስናደርግ የእርስዎን “የብልጽግና ፓርቲ” አጠራጣሪ ታሪክ ማለትም፤ የህወሐትን (ኢህአደግ) ጠባብ የብሄር፣ የዘረኝነትና ከፋፋይ የፖለቲካ መስመርና፣ በሕዝብ ላይ የፈጸመውን ግፍና ደባ ለአፍታም ቢሆን በመርሳት አይደለም። ያንን ሁሉ በሆዳችን ይዘን፤ ሀገራችን ኢትዮጵያን ወደላይ ከፍ በማድረግ፤ ለሕዝባችን ነጻነት፣ ፍትሕ፣ እኩልነትና ብልጽግና የሰፈነበት ስርአት እንዲገነባ “እናሻግራታለን” ያሉንን ቃል ኪዳን ተስፋ በማድረግና በማመን ነበር ከጎንዎ የቆምነው። ይሄም በብዙዎች ዘንድ መደገፍ የማይገባውን ስርአት እንደደገፍን አስቆጥሮን ነበር። አሁን እርስዎና መንግሥትዎ በሕዝብ ላይ የሚያደርሱትን በደልና ግፍ ስናስተዉል ግን፤ እኛም ከሕዝባችን ጋር አብረን የተከዳን አይነት ስሜትና ቁጭት ነው የሚሰማን።

በሚያሳዝን ሁኔታ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ቃል ገብተው ባፈረሱት ቃል ኪዳን የተነሳ፣ በእርስዎ አመራር ላይ ያለን እምነት ከምንጊዜውም በበለጠ አዘቅት ወርዷል። ሀቁ እንደሚያሳየው፣ እርስዎ ከአምስት አመት በላይ በመንግሥት ሥልጣን መሪነት በቆዩባቸው አመታት ውስጥ፣ ሀገራችን ኢትዮጵያ እጅግ በሚዘገንን ሁኔታ ላይ ትገኛለች፤ በሺዎች የሚቆጠሩ ንጹሀን ዜጎች ተጨፍጭፈዋል፤ በሚልዮን የሚቆጠሩ ተፈናቅለዋል፤ የሕዝቡ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ከምንጊዜዉም በበለጠ ተጥሰዋል፤ መንግሥት እራሱ ህገ መንግሥቱን አያከብርም፤ የህግ የበላይነትና ተጠያቂነት የሚባሉት በሀገሪቱ ስማቸውም ተረስቷል፤ ሌብነትና ሙስና የኑሮ ውድነት ሕዝቡን አስመርሮታል፤ በሚልዮን የሚቆጠሩ ንጹሀን ዜጎች ለረሀብና ለስደት ተጋልጠዋል፤ ችግሩ ተዘርዝሮ አያልቅም!

ከእዚህ በታች ዋና ዋና የሚያሳስቡንን፤ ለሀገራችን ሠላም፣ ለሕዝባችን ደህንነትና ለህልውናዋ የሚያስጨንቁንንና፤ ሌትና ቀን ቁጭት የሚያሳድሩብንን ክስተቶች ለመዘርዘር እንሞክራለን፥

  • በሚዘገንን ሁኔታ እያየን ያለነው መግታት ያቃተዎት የሰብአዊ መብቶች መጣስ እጅግ አድርጎ ያሳስበናል፤ በእርስዎ አመራር ስር በዘር እየተለየ የሕዝባችን በገፍ መታሰርና መንገላታት፤ በጠራራ ጸሀይ መገደል፤ የመናገር፣ የመጻፍ፣ የመሰብሰብና ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፤ የማምለክ ነጻነት መገፈፍ፤ በነጻ ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብቶች ወዘተ መቆም፤ ከባድ የሆኑ በሰው ልጅ ላይ  እየተፈጸሙ ያሉ ወንጀሎች፤ ከመጠን በላይ ብቻ ሳይሆኑ፣ መንግስትዎ እያወቀ መሆናቸው፤
  • ጋዜጠኞች እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን ጨምሮ የተቃውሞ ድምጽ ያሰሙ ወይም የአገዛዙን ፖሊሲዎች የሚቃወሙ ታስረዋል። በመላው ኢትዮጵያ በግፍ የታሰሩ የህሊና እስረኞች ቁጥር፣ ከመብዛታችው የተነሳ፣ ይህ ነው ለማለት አዳጋች ነው፤
  • ሕዝቡ በእርስዎ አስተዳደር ላይ ተስፋ እየቆረጠ ነው፤ ሌላዉ ቀርቶ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን ወደጎን በመተው፣ ተቃዋሚ የሚባሉትን ጥቂት ድምጾች፥ ለስሙ እንኳን ሳያዳምጡ በአንገብጋቢ የሀገር ጉዳዮች ላይ እንደፈለጉ በግልዎ ዉሳኔ ይሰጣሉ፤
  • ህወሓት የፕሪቶሪያን የሰላም ስምምነት በግልፅ እየጣሰ የእርስዎ አስተዳደር የህወሀትን ወንጀለኛ ድርጅት መልሶ ለማቋቋም በትጋት ሲሰራ በከፍተኛ ስጋት እየተመለከትን ነው፤
  • ይህን ሁሉ ዓመት በኦሮሚያ ክልል በሰላማዊ ሕዝብ፤ በተለይም ዘራቸው እየተለየ በአማራ ዜጎች ላይ የሚደርሰዉን አስከፊ ጭፍጨፋ ለማስቆም ባለመቻልዎ፤ እንዲሁም የኦሮሞ ብልጽግና አባላትና የመንግስት ባለስልጣኖች በሀገሪቱ ፓርላማ “አሸባሪ” ተብሎ ከተሰየመው “ኦነግ ሠራዊት” ጋር መነካካታቸውን እያወቁ ባለማስቆምዎ እጅጉን አዝነናል፤
  • በሰዉ ልጆች ላይ አሰቃቂ ወንጀል ሲፈጸም፤ በደቦ ድብደባና ግድያ፤ ሴቶችን እናቶችንና ህጻኖችን መድፈር፤ ከእርጉዞች ጽንስ በሳንጃ እያወጡ ማረድ፤ ወንዶችን አንገታቸዉን መቅላት፣በአንድ ቤት ውስጥ በማጎር በእሳት በማጋየት፣እና ሌሎችንም ለጆሮ የሚዘገንንኑ ወንጀሎች እያዩ፣ ይህን ያህል ዓመት ድንግጥ ብለው በማዘን፤ የመንግሥትዎን ኃይል ከሕዝብ ጋር አስተባብሮ በጋራ በመጠቀም እንዳይቀጥል ማስቆም አለመቻልዎ፤
  • በተለይም በአማራ ኢትዮጵያውያንና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች፤ እንዲሁም በሌሎች ብሄረሰቦች በጉራጌና ጌዲኦ፣ እንዲሁም በሻሸመኔ ኗሪዎችና በመሳሰሉት የደረሰዉን ግፍ አለማስቆምዎና፤ ወንጀለኞችንም ለፍርድ ማቅረብ አለመቻልዎ፤
  • በምእራብ ኦሮሚያ (ወለጋ) በተለይ በደርግ ዘመን፣ 1970ዎቹ በተደረገው የድርቅ ሰፈራ ከሰሜን የመጡ አማራ ዜጎች ላይ እየተካሄደ ባለው የዘር ማጥፋት ወንጀልና ጭፍጨፋ ማንንም በህግ ተጠያቂ በማያደርግ መልኩ አሁንም እየቀጠለ በመሆኑ፤
  • በተለይም የክልሉ አስተዳደርና ፖሊስ፤ ወንጀለኞች ይህን የተደራጀ የዘር-ማጥፋት ግፍ ሲፈጽሙ ድንገት እንደተቀሰቀሰ የጎሳ ግጭት አድርጎ፣ አይቶ እንዳላየ ማለፍ፣ ወይንም ለሚያደርጉት ትብብር በኢትዮጵያና በዓለም ዙሪያ ያሉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ኃይሎችን እጅግ አስቆጥቷል፤
  • ህገ መንግሥቱን በመጣስ፤ የእርስዎ መንግሥት በተደጋጋሚ በኃይማኖት ጣልቃ እየገባና ፖለቲካ እየሰነቀረ፤ ብዙ ጉዳት እያደረሰና የሀገራችንን ሰላምና አንድነት በማናጋት ለህልውናዋም አስጊ እየሆነ በመምጣትና የኃይማኖት አባቶችንም መናቅና ማሰቃየት፤
  • በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የእርስዎ መንግሥት ኢላማ ለመሆኑ፤ በቅርቡ መንግሥት በኃይማኖት ላይ ጣልቃ በመግባቱ ሳቢያ ሲኖዶሱን ለሁለት በመክፈል፣ በሀገሪቱ አንዣቦ የነበረዉ አደጋና፤ በሕገወጥ በተሾሙ ጳጳሳት ምክንያት በሻሸመኔ የኦርቶዶክስ ምእመናን ላይ የተደረገው ጭፍጨፋ፤ እንዲሁም በቅርቡ የአድዋን ድልንና የቅዱስ ጊዮርጊስን በዓላት ለማክበር በወጡት ምእመናን ላይ የደረሰው ድብደባና ግድያ፤ በአስለቃሽ ጭስ መታፈን በቂ ምስክሮች ናቸው፤
  • ገና ዉጤቱ ያልታየዉንና ስኬቱ የሚያጠራጥረዉን “የብሄራዊ ምክክር ኮሚሽን” ከማቋቋም ባለፈ፣ መንግሥትዎ እስካሁን ድረስ በቅንነትና በቆራጥነት ተነሳስቶ፣ በህወሐት-ኢህአደግ የተመሠረተዉንና በብሄር ፖለቲካ ላይ የቆመዉን የዘረኝነት ሥርአትና፣ ህገ መንግሥቱን ለማሻሻል ወይም ለመቀየር ይህ ነው የሚባል እርምጃ ሲወስድ አይታይም፤
  • ከ3.6 ሚልዮን ዜጎች በላይ ከቀያቸው መፈናቀል፣ ኢትዮጵያን በሀገራቸው-ዉስጥ በተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር ከዓለም አንደኛ አድርጓታል፤
  • የከተሞች ልማት በሚል ሰበብ፤ በአዲስ አበባ ዙሪያ ለአመታት የኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ኦሮምኛ የማይናገሩ ዜጎችን፤ ያለምንም ማስጠንቀቂያ በማንነታቸው እየተለዩ ቤታቸውን በሌሊት በላያቸው ላይ በቡልዶዘር እያስፈረሱ፣ ህጻናትን፣ ሴቶችንና አዛዉንትን ለረሀብ፤ ለስደትና ለአዉሬ ሳይቀር መዳረግ ከፍተኛ የሆነ ኢሰብአዊ ግፍና ወንጀል ነው፤
  • አስተዳደርዎ ህገ መንግሥቱን ኢፍትሐዊ በሆነና በዘፈቀደ መንገድ እንደሚተገብር በበርካታ ምሳሌዎች ማስረዳት ይቻላል፤ ከእነዚህም በቅርቡ፤ በደቡብ ኢትዮጵያ ለአንድ ብሄረሰብ (ሲዳማ) አዲስ ብሄርን መሰረት ያደረገ ክልል ሲፈጠር፣ በተመሳሳይ መልኩ ለሌሎች ብሄረሰቦች፤ ለምሳሌ እንደጉራጌ እና ወላይታ ያሉት ግን መከልከል ብቻ ሳይሆን መብታቸዉን ለማስከበር ሰላማዊ ሰልፍ እንኳን እንዳያደርጉና ድምጻቸዉን እንዳያሰሙ እየታፈኑ፤ ለእስርና ለድብደባ ለእንግልት ተዳርገዋል፤
  • ሌላዉ ቀርቶ የመጠጥ ውሀ ለወራት በማጣት ጉዳት ደርሶብናል በሚል ድምጻቸዉን ለማሰማት በወልቂጤ ባዶ ጀሪካን በትከሻቸው ይዘው ለሰላማዊ ሰልፍ የወጡትን ንጹሀን ዜጎችና በሻሸመኔ ወደ ቤተ ክርስቲያን ለጸሎት የሄዱትን ዜጎች የጸጥታ ኃይሎች በግፍ ገድለዋል፤ እንደተለመደው ለጥያቄና ለፍርድም አልቀረቡም፤
  • እርስዎ የሚመሩት መንግሥት፤ ዓለም የሚያደንቃቸውን የሀገራችንን የረዥም ጊዜ ታሪኮችና ቅርሳቅርሶች እንደፈለገው እየበረዘ ደብዛቸዉን ማጥፋት፤ ብሄራዊ አርማዎችን፣ የባህል ተቋሞችንና፣ የጥንት ቅርሶችን ማፍረስ፤ በኅብረ ብሔርዊነት የሚታወቁ ትልልቅ ከተሞችን ወደ አንድ ብሔር የበላይነት መቀየር፣ ከኢትዮጵያዊነት ወደዘርና ጎሳ ደረጃ ማዉረድን ተያይዞታል፤
  • ለኢትዮጵያዉያን ብቻ ሳይሆን ለአፍሪካ ታላቅ ኩራት የሆነዉ የአድዋ ድል በዓል እየደረሰበት ያለው ፈተና ለእዚህ ጥሩ ምሳሌ ሊሆን ይችላል፤
  • አስተዳደርዎ ከመድብለ ባህላዊነት ይልቅ በአንድ የጎሳ የባህል-አብዮት ላይ አተኩሯል። የኢትዮጵያ መዲና እና የአፍሪካ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከል የሆነችውን የአዲስ አበባ ባለቤትነት ከአህጉራዊ እና አገራዊ ቦታዎ ዘቅጦ የአንድ ጎሳ የበላይነት ለመውሰድ የሚደረገው ጥረት አሳፋሪ ብቻ ሳይሆን፣ ማለቂያ ወደሌለው ደም መፋሰስና እልቂት ሀገራችንን እንድታመራ እያደረጋት ነው፤
  • አባቶቻችን ምንም አይነት የዘርና ሀይማኖት የጎጥ ልዩነት ሳያግዳቸው፤ ሀገራቸዉን ከጠላት ለማዳን ለነጻነቷ ሲዋደቁና በህይወታቸው መስዋእትነትን ሲከፍሉ፤ የአፍሪካ ሀገራትም ከቅኝ ግዛት ነጻ ለመዉጣት ሲታገሉ በኩራት ያነገቡትን አርማ፤ አርንጓዴ ቢጫ ቀይ ህብር የተላበሰዉን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ አታሳዩን እያሉ የመንግሥት ጸጥታ አስከባሪዎች ዜጎችን ሲያስሩና ሲደበድቡ ምንም ሳይባሉ ሲቀሩ፤ አሁን ጭራሽ የአድዋን ድልም በምኒልክ አደባባይ ልታከብሩ አትችሉም መባሉ እጅግ አሳዛኝ የታሪክ ጠባሳ ሆኖአል፤
  • በየካቲት 23 ቀን 2023 ዓም የአድዋ የድል በዓል በሚከበርበት እለት፤ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ታሪካዊዉን የቅዱስ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ግቢ በጉልበት ገፍተው ገብተው፤ በዓሉን በጸሎትና በወረብ በሚያከብሩት ካህናትና ምእመናን ላይ በድንገት በአስለቃሽ ጭስ ተኩስ ከፍተው፣ በብዙዎች ላይ ከባድ የመቁሰል ጉዳት ማድረሳቸው፤ በዚህም ዕለት ለበዓሉ የወጡ ንጹሐን ዜጎች በጥይት ተኩሶ በመግደል፣ በጭካኔ እንደ አራዊት በመደብደብ ይህ በሰላማዊ ዜጎች ላይ የተደረገው ግፍ፤ በሀገራችን ኢትዮጵያ ምን ያክል ፍትሕና የህግ የበላይነት እንደጠፋና፤ የፖሊስ አምባገነን አስተዳደር እየገነነ እንደመጣ በግልጽ የሚያሳይ ነው፤
  • ባለፉት አምስት አመታት በእርስዎና የመንግሥትዎ አገዛዝ ወቅት የሀገራችን ወሰንና ዳር ድንበር በተዳጋጋሚ ጊዜ እየተደፈረ ነው። በተለይም በሱዳንና ደቡብ ሱዳን አዋሳኝ ቦታዎች የመንግሥትና የሌሎች ኃይሎች ከጎረቤት ሀገር እየገቡ፤ ኢትዮጵያዉያንን ማጥቃት እየተለመደ ሄዷአል። በዚህም በርካታ ዜጎቻችን በየጊዜው ህይወታቸው ያልፋል፤ ንብረታቸው ይዘረፋል፤ ከቀያቸው እንዲፈናቀሉም ይደረጋል፤ የሀገራችን መሬትም እየተቀማ ለባዕድ ሀገራት መጠቀሚያ ሲሆን መንግስትዎ ዝም ብሎ ማየትን መርጦአል፤
  • ልክ ከእርስዎ በፊት እንደነበሩት መንግሥታት የእርስዎም አስተዳደር ለዜጎቹ የምግብ ዋስትና ለማምጣት እስከዛሬ አልቻለም፤ እንደ ተባበሩት መንግሥታት የሰባዊ እርዳታ ጉዳይ አስተባባሪ ቢሮ (OCHA) መረጃ ከሆነ ከ20 ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዉያን በህይወት ለመኖር ዛሬ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል፤ የቅርቡ በረሀብ ተጎጅዎች ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ዉስጥ በቦረና የሚኖሩት ኢትዮጵያዉያን ናቸው። ይህ ሁሉ ከባድ የረሀብ አደጋ በሀገራችን እያንዣበበ እያለ፤ እርስዎ ግን የአስተዳደርዎን “መልካም ገጽታ” ለመገንባት ሲሉ የስንዴ ምርት ወደዉጭ ሀገር ለመላክ፣ አንድን ጎሳ በዋስትና ለመሸንገል፣ ሽርጉድ ይላሉ፤
  • በመንግስት ውስጥ የተንሰራፋው ሙስና፤ የዋጋ ግሽበት እና ወገንተኝነት እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እየደረሰ ሲሆን፤ የእርስዎ መንግሥት ምን ያክል ማስተዳደር እንዳቃተው ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ፤

ለእነዚህና ሌሎች ዘርፈ-ብዙ ተግዳራቶች ከቀን ወደቀን እያደጉ ለመጡ የሀገሪቱ ዉስብስብ ችግሮች መፍትሄ ለመሻት ቁርጠኝነት ባለማሳየትዎ፤ በተለይም የፌደራልና የኦሮሚያ ክልል የጸጥታና አስተዳደር አካሎች ግፍ ሲፈጽሙ እያዩ እንዳላዩ፤ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ድጋፍ በማሳየትዎ፤ በኢትዮጵያ የስርአት አልበኝነት ባህል እንዲነግስና፤ የህግ የበላይነትና ፍትሕ እንዲጠፉ በሩን ከፍቷል። ለምን እና በማን ስልጣን እንደዚህ አይነት ችግር ያለባቸው ፖሊሲዎች አገሪቱ ተከተለች ለሚለው ጥያቄ ሃላፊነት በእርሶ ላይ ነው – የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የመንግስት ርዕሰ መስተዳድር እና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ እርስዎ ስለሆኑ።

አሁንም በቆራጥነትና በቅንነት ተነሳስተው፤ በማስተዋል ወሳኝ የሆኑ መፍትሄዎችን መውሰድና በቶሎ በሥራ ላይ ማዋል ካልቻሉ፤ በዓለም ላይ እራሷን ለማጥፋት የምትጓዝ ብቸኛ ሀገር ኢትዮጵያ ትሆናለች። ያኔ እርስዎና መንግሥትዎ በታሪክ ተወቃሽ ይሆናሉ። ስለዚህ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ድምፅ ለሌለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጽ የመሆን ግዴታ አለበት። ለኢትዮጵያ ሕዝብ ቃል የገቡትን ለማክበር፣ የአገዛዝዎ ብልሹ አሰራርን ማስተካከያ እድሉ አሁን ነው።

ይህንን አደገኛ አካሄድ በአስቸኳይ ለመቀየር እና ጥፋቶችን ለማረም፣ ዜጎችን ለመጠበቅ እና ቅሬታዎችን ለመፍታት ቆራጥ የማስተካከያ እርምጃዎች እንዲወስዱ እንጠይቃለን። ዛሬ የመንግሥት መቀጠል ብቻ ሳይሆን፤ የኢትዮጵያ እንደ ሀገር የመቀጠል ህልውና አደጋ ላይ ነው ያለው። አስተዳደርዎ ኢትዮጵያን ከአስገባት ከዚህ አጣብቂኝ ጨለማ ለማውጣት እድሉ በእጅዎ ነው። በሰከነና በእውነት መንፈስ የሚወሰዱ እርምጃዎች ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ባለድርሻ አካላት አሳትፎ ሀገራችንን ለማዳን በአስቸኳይ ስራ እንዲጀመር አጥብቀን እናሳስባለን።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ልጆቿን ይባርክ!!!

_
በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  
የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

በኢትዮጵያ “የብሄር ፖለቲካ” ምንጩ፤ ያስከተለው ጉዳትና መፍትሄዉ (ክፍል – 2  በዓቢዩ ብርሌ)

ዓቢዩ ብርሌ - የብሄር ፖለቲካ
ዓቢዩ ብርሌ (ፎቶግራፉ የተወሰደው ከአርትስ ቲ ቪ ቪዲዮ ላይ ነው)

ክፍል – 2  

መግቢያ፤  

ባለፈው ጽሁፌ (በክፍል-1) በቅርቡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተከፈተዉን ዘመቻ፤ ቀደም ብሎ ከነበሩት የተለየ እንደሆነና፤ በአገራችን ህልዉና ላይ ያንዣበበውንና “በብሄር ፖለቲካ” ተመርኩዞ የቆመዉን “የዘረኝነት ስርአት” አደገኛነት አጉልቶ የሚያሳይ መሆኑን ለማሳየት ሞክሬአለሁ፡፡ ባለፉት 30 ዓመታት፤ የእዚህ አስከፊ ስርአት መርዝ፤ በሀይማኖት ተቋሞች ብቻ ሳይሆን በሁሉም ዘርፎች በሚባል ደረጃ ማለትም፤ በፖለቲካዉ፤ በኤኮኖሚው፤ በማህበራዊ ኑሮ፤ በመንግሥት መዋቅር፤ በፍትህ፤ በትምህርት፤ በፋይናንስና በባንክ፤ በሌሎችም እንደተሰራጨ ግልጽ ነው፡፡ አገራችን ከድህነት ተላቃ እንዳታድግና እንዳትገነባ፤ ወደፊትም እንዳትራመድ ሰቅዞ እንደያዛት ምንም አያጠራጥርም፡፡ በዉስጧ ሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር በማድረግ፤ ለህልዉናዋም ጸር እንደሆነ፤ በቅርቡ በትግራዩ ጦርነት በደረሰባት አደገኛ ፈተና እንኳን ለመረዳት ይቻላል፡፡ 

ባለፈው ለእዚህ ሁሉ ዉስብስብ የአገራችን ችግር መፍትሄው ምን ሊሆን ይችላል? የሚል ጥያቄ ለአንባብያን አቅርቤ ነበር ጽሁፌን ያቆምኩት፤ ይህን ከባድ ጥያቄ ለመመለስ ቢያግዝ በሚልም የአቅሜን አስተያየት ለመስጠት በክፍል 2 እመለስበታለሁ ብየ ቃል ገብቸ ነበር፤ ይኸዉና ዛሬ ይህችን አጭር ጽሁፍ በትህትና አቀርባለሁ፡፡ የጽሁፌ ዋና ዓላማ በተለይም በእዚህ ከባድና ዉስብስብ በሆነው የአገራችን አንገብጋቢ የፖለቲካ ጥያቄ፤ “በብሄር ፖለቲካ” ላይ የቆመዉን “የዘረኝነት ስርአት” መዘዙን እንዴት እናስወግደው በሚለው፤ ከተቻለ ሰፊና ጠለቅ ያለ አገር አቀፍ ዉይይት “በብሄራዊ ምክክሩ” አማካይነት እንዲከፈት በትህትና ለማሳሰብም ነው፡፡ በተጨማሪ ሀገራቸዉን አፍቃሪ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ፤ በሚችሉት ሁሉ አቅም ሀሳባቸዉን እንዲያበረክቱ ለማበረታታትና፤ በጋራ መፍትሄ እንድናፈላልግ በትህትና ለማሳሰብና ድርሻየን ለማበርከት በሚል ነው ይችን አጭር ጽሁፍ የማቀርበው፡፡ 

የብሄር ፖለቲካ መነሾው ከየት ነው?  

በቅድሚያ ይህን የመሰለ በጣም አስቸጋሪና አወዛጋቢ አስተሳሰብ ያዘለ “የብሄር ፖለቲካ” ወይም “ርዕዮተዓለም” ሊባል የሚችል ዘይቤ ወደ አገራችን እንዴት ሊገባ ቻለ የሚል ጥያቄ በብዙ ኢትዮጵያውያን ስለሚነሳና፤ ያለፈውን ትዉልድ “እሱ የተከለው መርዝ”  ነው በሚል ብዙ ትችትም ስለሚቀርብ፤ ታሪኩን አጠር አድርጌ ለማብራራት እሞክራለሁ፡፡ በታሪክ አጋጣሚ ሆኖ “የብሄሮች እኩልነት በኢትዮጵያ” የሚለዉንና ሌሎችንም ዴሞክራሲያዊ ጥያቄወች፤ በዋነኝነት “መሬት ለአራሹን” እና “ሕዝባዊ መንግሥት” የሚሉትን አንግቦ፤ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ከድህነት፤ ኋላቀርነትና የባላባታዊ (ፊዉዳል) የግፍ አገዛዝ፤ እንዲሁም ከኢምፔሪያሊዝም የእጅ አዙር ተጽእኖ ነጻ ለማዉጣትና፤ ፍትሕ፤ እኩልነትና ነጻነት የሰፈነባት፤ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት ዓላማ በመከተል፤ ከፍተኛ ትግል ካደረገዉና፤ ከባድ መስዋእትነትም በህይወቱ ሳይቀር ከከፈለው ትዉልድ የወጣሁ፤ በዕድልና በታምር ሊባል በሚችል አጋጣሚም ከተረፉት ጥቂቶቹ አንዱ መሆኔን አስቀድሜ ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡ 

ይህንም የምገልጽበት ዋናዉ ምክንያት፤ ከሌሎች በተለይም በመስዋእትነት ከወደቁት በሽ የሚቆጠሩ፤ ሀገራቸዉን አፍቃሪ ጀግኖች ወጣቶች፤ የእራሴን ኢምንት ታሪክ አጉልቸ ለማሳየት ሳይሆን፤ ዛሬ አገራችን ለገባችበትና መዉጫዉ ለጠፋበት “የብሄር ፖለቲካ አዙሪት” የአሁኑ ትዉልድ በደፈናዉ፤ እኔ ያለፍኩበትን ትዉልድ ዋነኛ ተጠያቂ ስለሚያደርግ፤ ያንን የተሳሳተ አመለካከት ለማስተካከል ቢረዳ በሚል ነው፡፡ በመሠረቱ ማናቸዉም ትዉልድ ሀገሩን በየጊዜው ለሚያጋጥሟት ዉስብስብ ችግሮች፤ በስሜት ሳይሆን በዕዉቀት፤ በስማ በለው ሳይሆን፤ በጥናትና በምርምር ላይ የተመሠረተ መፍትሄ በማፈላለግ፤ በበኩሉ የእራሱን ድርሻ ማበርከትና፤ የአገሩንና የታሪክን አደራ ለመወጣት መጣር ይኖርበታል፡፡ ሁልጊዜ ያለፈዉን ትዉልድ በጭፍኑ ማዉገዝ ለአገራችን ችግሮች መፍትሄ አያመጣም፤ ለአገራቸው ሲሉ በህይወታቸው መስዋእትነትን እየከፈሉ፤ አገራችንን ተንከባክበው አቆይተው ያወረሱንን ወላጆቻችንና አያት ቅድመ አያቶቻችንን በደፈናዉ እያማረሩ መኖሩም ትክክል አይደለም፡፡ ጥፋትም ፈጽመው ከሆነ ከስህተታቸው በመማር፤ ጥሩም ከሰሩ፤ በእነሱ ስኬትና ተሞክሮ ላይ እየገነቡ፤ አገራችንን ለማሳደግ በመጣር ፋንታ፤ በቂም በቀል ባለፈው ትዉልድ፤ በአያት ቅድመ አያቶቻችን፤ ጥርስን እየነከሱ መኖሩ መፍትሄ አያመጣም፡፡ ስንፍናን፤ የአስተሳሰብ ድህነትንና አቅም ማጣትንም ያዳብራል፡፡ ዕድል ብሎላት ታዲያ አገራችን በተደጋጋሚ በትዉልዶቿ እየደረሰባት ያለውና፤ እስከዛሬም መዉጫ ያላገኘችለት የቀዉስ አዙሪት፤ በድህነትም ወደኋላ ያስቀራትና ብዙ ከባድ ዋጋ እያስከፈላት ያለው፤ አንዱም ይህ ጎጅና መጥፎ የፖለቲካ ባህል ነው፡፡  

የሆነው ሆኖ እኔ ያለፍኩበት ትዉልድ፤ “በብሄር ጥያቄ ላይ” የነበረው አመለካከት በጥቅሉ በሁለት ሊከፈል የሚችል ይመስለኛል፤ እርግጥ የሁለቱም ምንጭ በ60 ወቹ ካደገውና በአገራችን የፖለቲካ ህይወት ላይ ከፍተኛ ተጽእኖን ካሳደረው የተማሪወች ንቅናቄ ነው፡፡ አንደኛዉ አመለካከት፤ አገራችን ኢትዮጵያ ብሄሮቿ ወይም ብሄረሰቦቿ በእኲልነት የሚኖሩባት አይደለችም፤ ይህም የሆነበት ምክንያት ሕዝባችን በብሄር፤ በቋንቋ፤ በጾታ፤ በባህልና በሀይማኖት ቢለያይም፤ ሁሉንም እኲል የሚያይና የሚያስተናግድ ዴምክራሲያዊና ሰብአዊ ስርአት ባለመኖሩ ነው ይልና፤ ለዚህም መነሾው በህብረተሰባችን የመደብ ልዩነት ስላለ፤ የመንግሥት አዉታሩንየሚቆጣጠረው፤ ኋላ ቀሩና በሕዝብ ላይ ግፍ የሚያደርሰው የባላባታዊው (የፊዉዳል) ገዥ መደብ ስለተንሰራፋ ነው የሚል እምነት ነበረው፡፡ 

በእዚህ ገዥ መደብም ከአንድ ብሄር፤ ሀይማኖት፤ ወይም አካባቢ ብቻ ሳይሆን፤ ይብዛም ይነስም ከተለያዩ ብሄሮች የመጡ አባላት አሉበት ይልና፤ በአጭሩ በህብረተሰባችን የሰፈነው ዋነኛ ቅራኔም በመደቦች መሀከል ያለው እንጅ በብሄሮች መሀል ያለው አይደለም ብሎ ያምን ነበር፡፡ ይህን ኋላ ቀርና ፍትሕ የለሽ የባላባታዊ (ፊዉዳል) ስርአትም አስወግዶ፤ ለሁሉም ዜጎች፤ የብሄር፤ የቋንቋ፤ የጾታ፤ የሀይማኖትና የባህል እኩልነትን የምታስተናግድና፤ እንዲሁም ዴሞክራሲያዊና ሰብኣዊ መብቶቻቸው ተከብረውላቸው፤ በዴሞክራሲያዊ መንገድ በነጻ በሚመርጡት መንግሥት የምትተዳደር፤ ህብረ ብሄርና ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን በምትኩ መገንባት አለብን የሚል ዓላማ አንግቦ ነበር ትግሉን ያካሄደው፡፡ እርግጥ ይህ አስተሳሰብ የአጭር ጊዜ ግቡ ዴሞክራሲያዊ ስርአትን በአገራችን ለመገንባት ይሁን እንጅ፤ ለረዥም ጊዜ ግቡ መዳረሻ ግን፤ የሶሻሊስት ርእዮተ ዓለምን ዋና መመሪያው አድርጎና በዉስጡም ይዞ ነበር የሚጓዘው፤ በእዚህ አመለካከት ዙሪያ፤ በግንባር ቀደምትነት የሚታወቁት ኢሕአፓና ሜኤሶን የነበሩ ሲሆን፤ ሌሎችም የህብረ ብሄር የፖለቲካ ድርጅቶች ነበሩበት፤ እኔም የኢህአሰ (የአሲምባ ሠራዊት) መሥራች አባል እንደመሆኔ መጠን፤ የኢሕአፓም አባል ነበርኩ፡፡  

 በአንጻሩ የእዚህ ትዉልድ ሌላዉ ካምፕ፤ ዘግየት ብሎ ከተማሪወች ንቅናቄ የተወለደውና፤ በዋነኝነት በህወሐት የሚመራዉ፤ በአገራችን ዋናዉ ትግል በመደቦች ሳይሆን በብሄሮች መሀከል ያለው ነው የሚል እምነት ይዞ ነው ትግሉን የጀመረው፤ እንደዚህ አመለካከት፤ በህብረተሰባችን የሰፈነው ዋናዉ ቅራኔ በመደቦች ሳይሆን በብሄሮች መሀከል ያለው ነው፤ ትግላችንም የብሄር ጭቆናን ለማጥፋት መሆን አለበት የሚል ነው፤ በዚህ አስተሳሰብ፤ ህወሐት “ጨቋኝና ተጨቋኝ ብሄር” ብሎ የኢትዮጵያን ሕዝብ በጥቅሉ በሁለት በመክፈል ነበር የሚያየውና የትጥቅ ትግሉንም የቀጠለው፤ በኋላም የመንግሥት ስልጣን ላይ የተቆናጠጠው ይህን የተዛባ አመለካከት እንደያዘ ነው፡፡ ጨቋኝ ብሄር የሚለዉም በተናጠል አማራን ሲሆን፤ በተጨቋኝ ወገን ግን ሌሎችን በሙሉ (ትግራይንና ኦሮሞንም ጨምሮ) ያካትታል፤ በአማራ ብሄር ዉስጥ ያለው አብዛኛዉ ዳሀ ገበሬ ሕዝብም “ከጨቋኙ የአማራ ብሄር” ከሚለው ጋር ይጠቃለላል፤ ለህወሐት የመደብ ትግል የሚለው በሁለተኛ ደረጃ የሚታይ ሲሆን ለትግሉም ወሳኝ አልነበረም፤ እየቆየ ሲሄድ ግን እንዴት የአማራን ብሄር ወይም ደሀዉንና ሰፊዉን ሕዝብ በሙሉ ጨቋኝ ትላላችሁ? ሲባል፤ ሌላ ቃል መወርወር ጀመረ፤ “የአማራ ጨቋኝ ገዥ መደብ” የሚል፡፡ በእዚህ አባባል እኛ መጥተን እስክናድናችሁ ድረስ፤ የሀገሪቱን የመንግሥት ስልጣን የያዘው አማራ ብቻ ነው (እኛ ትግሬወች ወይም ሌሎች እንደኦሮሞ ያሉት) አልነበረንበትም ማለቱ ነው፡፡ በዚህም አለ በዚያ እስከዛሬ አገራችንን በእሳት ዉስጥ የከተታትና እያመሳት ያለው ይህ ከጅምሩ የተዛባ፤ በጥላቻና “በጠባብ የብሄር ፖለቲካ አስተሳሰብ” ላይ የቆመ መርዘኛና ከፋፋይ ርእዮተ ዓለም እንደሆነ፤ ባለፉት 30 አመታት የነገሰው የህወሐት “የዘረኝነት አገዛዝ” እራሱ በቂ ምስክር ነው፡፡ 

ምናልባት “የብሄር ጭቆና” የሚባል ካለም፤ ከኃ/ሥላሴና ደርግ ዘመነ መንግሥት ይልቅ፤ በበለጠ በህወሐት አገዛዝ ነው ስር የሰደደው ቢባል ከእዉነት የራቀ የሚሆን አይመስለኝም፤ ለምን ቢሉ ህወሐት ብሄርን ተገን አድርጎ ሁሉንም ዘርፎች፤ የሀገሪቱን የፖለቲካ፤ ኤኮኖሚ፤ ማህበራዊ ኑሮ፤ የሚሊታሪና ደህንነት፤ የክልል፤ የእምነት ተቋሞችንም ሳይቀር ከእራሱ ብሄር በወጡ ሹመኞችና ካድሬወች ይቆጣጠር ነበርና፤ ለእዚህ ታሪክ ምስክር ነው፡፡ ካላፉት መንግሥታት ግን ሌላዉ ቢቀር በአጭሩ ለማሳየት፤ የንጉሱን ባላባታዊ ስርአትና የደርግን መንግሥት ቁንጮ የያዙት፤ ኃ/ሥላሴና መንግሥቱ ኃ/ማርያም እንኳን ሙሉ በሙሉ አማራ አልነበሩም፡፡ 

የሚያሳዝነው፤ ህወሐት ለጊዜው ቢነቀልም፤ መርዘኛዉና ለአመታት ስር የሰደደው “የብሄር ፖለቲካ ስርአት” ግን ከአገራችን እስካሁን ሊነቀል አልቻለም፡፡ ልክ እንደህወሐት ሌላ ብሄርን ተገን አድርጎ በተራዉ፤ የአገሪቱን የፖለቲካና የኤኮኖሚ፤ የማህበራዊ ኑሮ፤ የመንግሥት መዋቅርና ተቋሞችን በሙሉ ለመቆጣጠር እየታተረ ያለ “የገዥ መደብ” ተተክቶአል፡፡ ለእዚህ ሁሉ መንስኤ፤ “ለብሄር ፖለቲካዉና ዘረኛው ስርአት” ስረ መሰረቱና ግንዱ ደግሞ ህወሐት የተከለው ህገ መንግሥት እንደሆነ ምንም አያሻማም፡፡ በነገራችን ላይ፤ ደርግ እንደወደቀ ሥልጣን ለመያዝ ህገመንግሥቱን ሲያረቅ፤ በተቻለው መጠን ሌሎችን ተቀናቃኝ ድርጅቶች አግልሎ ወይም በስሩ አድርጎ “የትግራይ ልሂቃንን” ወደ ሥልጣን እንዲያወጣ አመቻችቶ ነበር ያነጸው፤ ይህ እንዲሳካለት፤ ከመጥፋት በታምር የዳኑትን፤ የህብረ ብሄር ድርጅቶች ኢሕአፓንና ሜኤሶንን፤ የመንግሥት ስልጣን መጋራቱስ ይቅርና፤ ህገ መንግሥት በሚያረቀው ጉባኤ ላይ እንኳን እንዲሳተፉ አልፈቀደላቸውም፡፡ ሕዝቡም በአገር አቀፍ ደረጃ ሰፋና ጠለቅ አድርጎ አልተወያየበትም፡፡ 

ህወሐት የመንግሥት ስልጣን ላይ ከወጣም በኋላ፤ በተለይም በአማራ ብሄር ላይ ያለዉን የከረረ ጥላቻ በአገር ደረጃ የፖሊሲ መመሪያ በማድረግ ነው የቀጠለው፤ በሌሎች ብሄሮች፤ በተለይም በኦሮሚያ የተለያየ ስም፤ ለምሳሌ “ነፍጠኛ” “ወራሪ” የሚል ቅጽል እየተለጠፈበት፤ ምስኪኑ የአማራ ሕዝብ እንዲሸማቀቅ፤ በሕዝብ እንዲጠላና እንዲወገዝ፤ “መጤ” እየተባለም ወልዶና ተዋልዶ ተዛምዶ በሰላም ለአመታት ከኖረበት አካባቢው ዘሩ እየተቆጠረ ሳይቀር ተለይቶ እንዲፈናቀል፤ በግፍ እንዲጨፈጨፍ ነው የተፈረደበት፡፡ ዛሬ “ሸኔ” በሚል ስም የሚጠራዉ የኦነግ ክንፍም የአስተሳሰብ ምንጩ ከዚያ ሰይጣን አመለካከት ነው፤ ባጠቃላይ፤ ባለፉት 30 ዓመታት፤ ህወሐት በአገራችን በዘራዉ መርዘኛ “የብሄር ፖለቲካና” ባንሰራፋዉ “የዘረኝነት ስርአት” የተነሳ በብሄር፤ በመሬትና በሕዝብ ለሕዝብ ግጭትና መፈናቀል በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ ንጹሀን ኢትዮጵያዉያን፤ ከሁሉም ብሄሮችና ብሄረሰቦች አልቀዋል፤ ቀያቸዉን እየለቀቁ በበረሀ ተሰደዋል፤ ለእረሀብና በሽታ ለሞትም ተዳርገዋል፡፡

በተለይም በኦሮሚያ ክልል ለብዙ አመታት የኖሩት አማሮች በመጨፍጨፍና በመፈናቀል ብዙ ግፍ ተፈጽሞባቸዋል፤ የሚያሳዝነው ዛሬም በሁለቱ ክልሎች በተለይ በኦሮምያና በትግራይ “ጠባብ ብሄረተኞች” እና ጠባቂወቻቸው በተሰገስጉባቸው የክልል መንግሥታት፤ ይህ የዘረኛና ኋላ ቀር አስተሳሰብ መርዝ ሊገታ አልተቻለም፡፡ የአገራችንን ህልዉና እየተፈታተነ ይገኛል፤ የትግራይና የኦሮሞያ “ጠባብ ብሄረተኞችና ጽንፈኞች” በተለይ በአማራ ሕዝብ ላይ ያላቸዉን ጥላቻ ከህሊናቸው ጨርሰው ሊፍቁት አልቻሉም፤ ጭራሽ ባሰባቸው፡፡ የሚያሳዝነው አልሆንላቸው ብሎ ነው እንጅ፤ ለዘመናት ተስማምተውና ተግባብተው በሰላም የኖሩትን፤ ሶስት ታላላቅ ሕዝቦች (ኦሮሞ፤ አማራና ትግራይ) ለመነጣጠልና፤ በመሀላቸው አንድነት እንዳይኖር ለማድረግ፤ ብሎም አገራችን ኢትዮጵያን ለመሰነጣጠቅና ለማፈራረስ እስከዛሬ ያልሸረቡት ሴራና ያልቆፈሩት ጉድጓድ የለም፡፡ ህወሐት በቀሰቀሰው የትግራይ ጦርነት በአፋርና አማራ ሕዝብ ላይ የደረሰውን ግፍ እራሱ ታሪክ አይረሳዉም፡፡ በአጋሩ “ሸኔ” በኦሮሚያ በተለይም በወለጋ እስካሁን የሚካሄደው የአማራ ድሆችን ጭፍጨፋና ማፈናቀልም፤ ታሪክ ምንጊዜም ይቅር አይለዉም፡፡ ምስኪኑ የትግራይ ሕዝብም አልቀረለትም፤ ለእዚህ መርዘኛ “የብሄር ፖለቲካ” ሰለባ በመሆን በመቶ ሽህ የሚቆጠሩ ልጆቹን በጦርነቱ ገብሮአል፡፡ እንግዲህ የትኛዉን “ብሔር ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ” ነው “የብሄር ፖለቲካዉና ዘረኛ ስርአቱ” የጠቀመው? ከገዥወቹና የስርአቱ ጥቅም ተካፋዮች፤ ከሌቦችና ዘራፊወች በስተቀር!  

ህወሐት በዘረጋዉ “የብሄር ፖለቲካ” መርዝና “የዘረኝነት ስርአት” ሳቢያ፤ ባለፉት 30 አመታት (በተለይም በቅርቡ 5 አመታት)  በኦሮሚያና አማራ ክልል ብቻ ሳይሆን፤ በሌሎች ክልሎች የሚኖሩትም ዜጎች፤ በደቡብ፤ በሶማሌ፤ በአፋር፤ በጋምቤላና በቤኒሻንጉል፤ በክልል፤ በመሬትና በድንበር፤ በዘር ግጭት የተነሳ፤ በእርስበርስ ጦርነት፤ በጭፍጨፋና በመፈናቀል ምክንያት በብዙ ሽ የሚቆጠሩ አልቀዋል፤ ቀያቸዉን እየለቀቁ ተሰደዋል፤ በዚያ ሰቆቃ ላይ ድህነቱ፤ ሙስናና ዝርፊያዉ፤ የኑሮ ዉድነቱ ተደራርቦ ሕዝቡ ይሰቃያል፤ ይህ መጥፎ “የብሄር ፖለቲካና ዘረኛ ስርአት” ካልተቀየረ ወይም ካልተወገደ፤ በአገራችን ዘላቂ ሰላምና እድገት መቸም አይመጣም! ህወሐት በሕዝብ አመጽ ተነቅሎ በ“ብልጽግና” ተተክቶም እንደሚታየው መሰረታዊ ለዉጥ እስከዛሬ ድረስ አልመጣም፤ የሚያሳዝነው፤ “የብሄር ፖለቲካን” ያስቆማሉ በሚል ሕዝቡ ትልቅ ተስፋ የጣለባቸው የብልጽግና መሪወችም፤ ታሪክ ሊሰሩ ሲችሉ ዕድሉን እስከዛሬ  አልተጠቀሙበትም፡፡ ፓርቲያቸው ለእራሱ “በብሄር ፖለቲካ” ወገቡን ተተብትቦ፤ ያንን መፍታት አቅቷቸው፤ ወደፊት ለመራመድም አቅቶት መሀል መንገድ ላይ ቆሞ፤ ግራና ቀኝ እየተንገዳገደ፤ አገሪቱንም ይዟት እንዳይወድቅ እያሰጋ ነው፡፡ ከህወሐት ስህተት ተምሮ፤ አቅጣጫዉን ቶሎ እንደማስተካከል፤ እሱም በ”ኢህአደግ የቁልቁለት ጉዞ” በፍጥነት እየተንደረደረ ነው!  

በኢትዮጵያ የ“ብሄር ፖለቲካውና የዘረኝነት ስርአቱ” የማያባራው መዘዝ፤  

 በ60 ወቹ መጀመሪያ ላይ በኃ/ሥላሴ ዩኒበርሲቲ ስማር፤ ተማሮች በተለያዩ ጊዜአት የደቡብ አፍሪካን የነጮች ዘረኝነት ስርአት ተቃዉመው በስብሰባና በሰላማዊ ሰልፍ ሲያወግዙ፤ እኔም አብሬ ለመሳተፍ ዕድል አግኝቸ ነበር፤ በወቅቱ እናት አገራችን ኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካን የነጮች ዘረኛ ሥርአትና የምእራባዉያንን በአፍሪካ ቅኝ አገዛዝ በመቃወም አህጉሩን በመምራት ግንባር ቀደም ነበረች፡፡ በቅርቡ ከአማራ ክልል ወደ አዲስ አበባ ለመግባት ስንቱን በረሀና ዱር አቋርጠው መጥተው፤ ኦሮሚያ ድንበር ሲደርሱ፤ መታወቂያቸው እየታየ፤ ኦሮሞ የሆኑት እንዲገቡ ሲፈቀድላቸው፤ የአማራ መታወቂያ የያዙት ግን በክልሉ ፖሊሶች አትገቡም እየተባሉ ወደመጡበት እንዲመለሱ ሲገደዱ ሳይ ያ የረሳሁት ከ50 ዓመት በፊት በደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች ላይ በዘረኝነት ስርአቱ ይደርስባቸው የነበረው ግፍ በህሊናየ ድቅን እያለብኝ ዉስጤን ህመም ይሰማኝ ነበር፡፡ ከእዚህ ሁሉ ዓመት በኋላ፤ በ21ኛዉ ክፍለ ዘመን ያዉም በኢትዮጵያ የነጭ ሳይሆን የጥቁር በጥቁር ዘረኝነት አያለሁ ብየ በህልሜም ሆነ በዉኔ አስቤው አላዉቅም ነበር፡፡ እነዚያ ለሀገራቸው ነጻነትና ለሕዝባቸው ሰብአዊ መብት ሲታገሉ ህይወታቸዉን ለመስዋእትነት አሳልፈው የሰጡት በሽ የሚቆጠሩ ወጣቶች (የሁሉም ብሄር ልጆች) በታምር ከመቃብራቸው ተነስተው፤ ሀገራቸውን ዛሬ ምን እንደምትመስል ቢያዩአት ምን ይሉ ይሆን ነው ያልኩት፡፡ 

በደቡብ አፍሪካ በ1950 ዓም (በፈረንጅ አቆጣጠር) ዘረኛዉ የነጮች መንግሥት ባወጣዉ ህግ (Group Areas Act) መሠረት፤ በሁሉም የለሙ ከተሞች አካባቢወች የሚኖሩት ጥቁሮችና ህንዶች፤ በዘራቸው እየተለዩ ተነቅለው፤ ልክ እንደዛሬይቱ “አዲሲቱ ሸገር ከተማና አዲስ አበባ” እንዲሁም በ”ብሄርና በቋንቋ” የታጠሩት የኢትዮጵያ ክልሎች፤ ከነጮች እርቀው፤ እርስበርስ እንዳይገናኙም ተደርገው እንዲሰፍሩ ነበር የተገደዱት፡፡ ሰሞኑን በኦሮሚያ ክልል አስተዳደር “ሸገር” የሚል ስም በተሰጠውና፤ አዲስ አበባን እንደቀለበት ዙሪያዋን ባጠራት አዲሱ ከተማ፤ ኦሮሞ ያልሆኑት በዘራቸው እየተለዩ፤ ቤታቸው በሌሊት በግሬደር በላያቸው ላይ እየፈረሰ ወደሌላ ቦታ እንዲሰደዱና እንዲሰፍሩ እንደተደረጉት፤ የደቡብ አፍሪካ ጥቁሮቹም ተመሳሳይ እጣ ነበር የገጠማቸው፡፡ በተግባር ሲዉል የነበረው ጭካኔና፤ በንጹሀን የሰው ልጆች ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ ግን የኢትዮጵያው ይብሳል፡፡ ሌሎችንም በርካታ ምሳሌወችን የደቡብ አፍሪካዉን የዘረኝነት ሥርአትና በኢትዮጵያ አሁን የተንሰራፋዉን “በብሄር ፖለቲካ” ስም የቆመዉን “የዘረኝነት ስርአት” የሚያመሳስሉትን መጥቀስ ይቻላል፤ ለጊዜው ግን እዚህ ላይ ላቁምና ወደእኛዉ የጉድ ታሪክ ላተኩር፡፡ 

በአገራችን ኢትዮጵያ “የብሄር ፖለቲካውና የዘረኝነት ስርአቱ” በፖለቲካዉ መስክ ላይ ብቻ እንኳን ያደረሰዉን ጉዳት ብንወስድ ተዘርዝሮ አያልቅም፡፡ ለምሳሌ በክልሎች የእዚያው ብሄር “ተወላጅ” ካልሆኑ በስተቀር ሌሎች ዘራቸው እየታየ መሪ መሆን አይፈቀድላቸዉም፤ በሌሎች ከፍተኛ ኃላፊነቶችም ከተመደቡ ዕድለኞች ናቸው፤ በመንግስት መዋቅሮች በተለይ ዜጎች በችሎታቸዉ፤ ተሞክሮአቸውና ዕዉቀታቸው ሳይሆን በአብዛኛዉ ዘራቸው (ብሄራቸው)ና ዘዉጋቸው እየታየ ነዉ ኃላፊነት የሚሰጣቸው፤ ምንም እንኳን ቁጥራቸው ቢበዛም፤ በተለይ የአማራ ተወላጆች በከፍተኛ አስተዳደር እርከን እንዲመደቡ አይፈቀድላቸዉም፤ ለምሳሌ በትንሹ እንኳን የድሬዳዋን ከተማ ብንወስድ፤ አማራ የሚባሉት ቁጥራቸው የኗሪዉን አንድ ሶስተኛ ያክል ሆኖም እንኳን ከተማዋን ማስተዳደር አይፈቀድላቸዉም፤ የኦሮሞና ሶማሌ ብሄር ተወላጆች ናቸው በየአራት አመቱ እየተፈራረቁ ከተማዋን የሚመሯት፤ ሌሎችንም በርካታ የዘረኛ ስርአቱ በተለያዩ ክልሎችና ከተሞች ያስከተለውን መጥፎ ክስተቶች፤ በህግ ተደግፈው የሰፈኑትን መጥቀስ ይቻላል፤ ቦታ ስለማይበቃን እዚህ ላይ ልተወዉና ለእዚህ ሁሉ ምክንያት “የብሄር ፖለቲካዉ”ና “የዘረኝነቱ ስርአት” መሠረት ወደሆነው በህገ መንግሥቱ ላይ ላተኩር፤ ከእዚያ ቀጥየም የመፍትሄ ሀሳቦች የሚመስሉኝን ጠቁሜ ጽሁፌን ለጊዜው አቆማለሁ፡፡ 

ህወሐት የተከለው የኢትዮጵያ ህገ መንግሥትና፤ እሱ የወለደው “የብሄር ፖለቲካና የዘረኝነት ስርአት” መዘዝ፤  

ገና ከጅምሩ፤ የህገ መንግሥቱ አንዱ ዋነኛ ችግር፤ “ብሄር፤ ብሄረሰብና ሕዝብ” ማለት ምን ማለት ነው? አንድነታቸዉና ልዩነታቸዉስ ምንድን ነው? ለምንስ የህገ መንግሥቱ አዉታር ሊሆኑ ቻሉ? ለሚሉት ጥያቄወች መልስ በግልጽ አለማስቀመጡ ነው፤ ይህን በታዋቂው አንቀጽ በ39 (ቁ፡5) ስር ለማብራራት ቢሞክርም በቂ አይደለም፤ “ብሄር ብሄረሰብ ሕዝብ ማለት፤ ሰፋ ያለ የጋራ ጠባይ የሚያንጸባርቅ ባሕል ወይም ተመሳሳይ ልምዶችና፤ ሊግባቡበት የሚችሉበት የጋራ ቋንቋ ያላቸው፤ የጋራ ወይም የተዛመደ ህልዉና አለን ብለው የሚያምኑ፤ የሥነ ልቦና አንድነት ያላቸዉና በአብዛኛዉ መልክዓ ምድር የሚኖሩ ናቸው” ይላል ህገ መንግሥቱ፡፡ 

እስኪ እግዚአብሔር ያሳያችሁ! እያንዳንዱን ቃል ወይም ሀሳብ አተኩራችሁ እዩትና፤ ከላይ በተጠቀሰው መስፈርት፤ በኢትዮጵያ ከ80 በላይ አሉ የሚባሉትን “ብሄር ብሄረሰቦች” ወስዳችሁ፤ ይህ ብሄር ነው ወይም አይደለም፤ ብሄረሰብ ነው ወይም አይደለም፤ ሕዝብ ነው ወይም አይደለም ብላችሁ በጥቂቶቹ ከቻላችሁ ብታስረዱኝ እንዴት ደስ ባለኝ! ለምሳሌ እዚህና እዚያ ተቆርጠዉና ተቀጥለው ብሄር ናቸው ተብለው የተካለሉትን የኦሮሚያንና የአማራን ክልል እንኳን ብንወስድ በዉስጣቸው የሚኖሩት ዜጎች በሙሉ ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ሙሉ በሙሉ አያሟሉም፡፡ አንዱን መስፈርት “ሊግባቡበት የሚችሉበት የጋራ ቋንቋ ያላቸው” የሚለውን ብንወስድ፤ በኦሮሚያ ክልል በበርካታ ቋንቋወች አማርኛንና ኦሮምኛን ጨምሮ ሕዝቡ ለመግባቢያ ይጠቀማል፤ ከእዚያ በላይ ቀደም ብሎ፤ በሁለቱም ክልሎች፤ በተለያዩና አንዳንዶቹ ጨርሶ በማይዋሰኑ ወይም በማይገናኙ አካባቢወች፤ አዉራጃወችና “ክፍለ ሀገሮች”  ነው ሕዝቡ የኖረው፤ ስለዚህ እንዴት ብሎ ነው በህገ መንግሥቱ (አንቀጽ 39 ቁ 5) በተሰጠው መስፈርት (ለምሳሌ በቋንቋ)፤ አንዱን ኢትዮጵያዊ ዜጋ አንተ የኦሮሞ፤ የአማራ ወይም የቤኒሻንጉል ብሄር አባል ስለሆንክ የእዚህ ክልል አባል ነህ ብለን ልንለየውና ልንመድበው የምንችለው? የዘሩንስ እንተወው! “የሥነ ልቦና አንድነት ያላቸዉና” “የጋራ ወይም የተዛመደ ህልዉና አለን ብለው የሚያምኑ”  የሚለዉንም እንዴት ነው ለማወቅና መለየት የሚቻለው? አንደድሬዳዋ፤ ሐረርና አዲስ አበባ ባሉ የብዙሀን ከተሞች በተለይ፤ ከተለያየ ብሄር ተጋብተው፤ ወልደዉና ተዋልደው የሚኖሩትን እንዴት ብለን ነው ብሄራቸዉን የምንለየው? ባጠቃላይ ህወሐት ባስቀመጠው መስፈርት እንኳን ብንሄድ፤ መጀመሪያ የተካለሉት ዘጠኙ ክልሎች በቂ ጥናት ተካሂዶባቸው “ራስን በራስ ለማስተዳደር” ወይም “ለፌደራል አስተዳደር” አመች ብሄሮች እንዲሆኑ ታስቦ ሳይሆን ለሌላ አጀንዳ ነበር የተዋቀሩት፡፡ እሱን ከታች በኋላ እመለስበታለሁ፡፡  

በተጨማሪ ህገ መንግሥቱ “በብሄር ብሄረሰብና ሕዝብ” ተወካዮቻቸው ነው የጸደቀው የሚለውም ፍጹም ስህተትና ከታሪክ ጋር የማይገናኝ ሀሰት ነው፤ ብሄርን ብሄረሰብንና ሕዝብን እንወክላለን የሚሉ “የብሄር ፖለቲከኞች” ያጸደቁትና ቀስ በቀስ “የዘረኝነት ሥርአት” በአገራችን የተከሉብን መዘዝ እንደሆነ ያለፉት 30 ዓመታት ምስክር ናቸው፡፡ ከሁሉም የከፋ ደግሞ፤ ህገ መንግሥቱ በተለይም አንዳንድ አወዛጋቢ የሆኑ አንቀጾቹን (ለምሳሌ አንቀጽ 39) በቀላሉ እንዳይሻሻሉ ተብትቦ ማሰሩ ነው፡፡ ህገ መንግሥት የሚደነገግበት አንዱ ዋና ምክንያት፤ በዜጎች መሀል ብሄራዊ ስሜትንና መግባባትን እያዳበረ፤ የህግ የበላይነትን እያስከበረ፤ አገርን በጋራ ለመገንባትና ለማሳደግ መሰረት እንዲሆን ታስቦ ነው፡፡ አሁን ያለው የኢትዮጵያ ህገመንግሥት ግን ብሄራዊ መግባባት ሊፈጥርና፤ አገር ለመገንባት ሊያግዝ ቀርቶ፤ ሆነ ተብሎ ዜጎችን ለማራራቅና ለመከፋፈል ብሎም ካስፈለገ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የታቀደ ሴራ እንደሆነ በተግባር፤ ባለፉት 30 ዓመታትና፤ በቅርቡም በትግራይ ጦርነት በግልጽ ታይቶአል፡፡ 

የሚገርመው፤ ታዋቂው አንቀጽ 39 እራሱ “የብሄሮችን የእራስን በእራስ የማስተዳደርና የመገንጠልን መብት ጨምሮ” የሚለው፤ መብት በህገ መንግሥቱ የተካተተው፤ በቀላሉ ከማይቀየሩት በምእራፍ 3 (“መሠረታዊ መብቶችና ነጻነቶች”) ከገቡት አንቀጾች ጋር ተሰንቅሮ ነው፤ ይህን አንቀጽ ለማሻሻል ለዚያዉም ከተቻለ፤ ብዙ ዉጣ ዉረድ አለው፡፡ በአሁኑ ህገ መንግሥትና በብሄር (ዘር) ላይ በቆመው “የፌደራል አወቃቀር” እሱን ለመንካትና ለማሻሻል በጣም አዳጋች ነው፡፡ (አንቀጽ 104 እና አንቀጽ 105 ን ይመልከቱ)፤ በአጠቃላይ ከህገ መንግሥቱ በርካታ መሻሻል የሚገባቸው አንቀጾችን መጥቀስ ይቻላል፤ እሱን ለማድረግ ግን የእዚህ ጽሁፍ ዋና ዓላማ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን፤ ሙያየም አይፈቅድልኝም፤ ከተሳካልኝ “ለብሄራዊ ምክክሩ” እንደኢትዮጵያዊነቴ ሀሳቤን አቀርባለሁ፡፡ አሁን የሚያስጨንቀኝ “የብሄራዊ ምክክሩስ” ቢሆን እራሱ ይካሄዳል ወይ የሚለው ነው! አንድ ለአገራችን ሰላምና ህልዉና የቀረን መፍትሄ እሱ ብቻ ነበር፤ ይሁን እንጅ፤ እሱም አደጋ ላይ እየወደቀ ነው! በሀገሪቱ በሞላ ሰላምና መረጋጋት በጊዜአዊ መልክ እንኳን ካልሰፈነ፤ እንዴት ብሎ “ብሄራዊ ምክክር” እና ሕዝባዊ ዉይይት ማድረግ እንደሚቻል አንዱ ፈጣሪ ነው የሚያዉቀው!  

የ”ፌደራል” አወቃቀሩ፤  

የ”ብሄር ፖለቲካዉ ህገ መንግሥት” አንዱ ዋና በአገራችን ላይ የፈጠረው ጦስ፤ የብሄር ጥያቄን ጭራሽ በአገራችን ለዘመናት ገና ዘላቂ መፍትሄ ካልተገኘለት “ከመሬት ጥያቄ” ጋር ማወሳሰቡና መተብተቡ ነው፡፡ ለዚያም ነው አንዱም መፍትሄ ለማግኘት በጣም አስቸጋሪ የሚያደርገው፡፡ ህወሐት ሀገሪቱን በብሄር (ዘር) ከከፋፈለ በኋላ፤ ክልል በሚል ስም መሬቷን በመሸንሸን አድሎ፤ “ይኸዉላችሁ እንደፈለጋችሁ አስተዳድሩ” ሲላቸው፤ “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንዲሉ እነዚህ የ“ክልሎች፤ ብሄሮችና ብሄረሰቦች” ፖለቲከኞች አንዳንዶቹ ወሰናቸዉን ለማስፋፋት፤ ሌሎቹ በድንበርና በግዛት በመጣላት ሕዝብን ከሕዝብ ማጋጨታቸዉን ቀጠሉ፡፡ ሌላዉ ቀርቶ የሀገሪቱን ዋና ከተማ ምናልባትም ከ80 ወቹ “ብሄሮችና ብሄረሰቦች” የመጡ ዜጎች ያለስጋት በሰላምና በፍቅር ተዋህደው የሚኖሩባትን አዲስ አበባን “ፊንፊኔ የእኛ ክልል ሀብት” ናት የሚሉ ተነሱ! ገና ከጅምሩ፤ የህወሐት መሪወች ኢትዮጵያን ማስተዳደሩ አንሷቸው፤ ለመጠባበቂያ የእራሴ የሚሉትን የትግራይን ክልል አስፋፍተው፤ ተከዜን ተሻግረው፤ ወልቃይት ጠገዴንና ጠለምትን፤ እንዲሁም ከላይ ራያን በጉልበት ነጥቀው “ህገ መንግሥቱ የሰጠን” የእኛ ሀብት ነው ሲሉ ነው ነገር የተበላሸው፤ ለዘመናት በሰላም አብረው ጎን ለጎን የኖሩትን ሁለቱን ሕዝቦች፤ አማራንና ትግራይን ደም አቃብተው ለመለያየትና አገራችንም ለማፍረስ ስንት ወጣት አስጨረሱ፡፡ 

ስለዚህ የኋላ ቀር ስርአት መቆሚያ የሆነውና ፍትሕ የጎደለው ህገ መንግሥትና “የፌደራል ክልል አወቃቀር” የተተከሉት በዋነኝነት በአገራችን ዴሞክራሲ ለማስፈን፤ ወይም “ብሄሮች እራሳቸዉን በእራሳቸው እንዲያስተዳድሩ” ታስቦ ሳይሆን፤ አገሪቱን በዘርና በብሄር በክልል ከፋፍሎ፤ በስልጣን እስካሉ ድረስ መሬትና ሀብት ያለገደብ እየዘረፉ ለመግዛት፤ አለዚያም ካልተቻለ የእራስን ሰፊ ክልል ወይም ብሄር ይዞ ለመገንጠል ነው ቢባል ከእዉነት የራቀ ሚሆን አይመስለኝም፤ ለእዚህ ነው በብሄር ፖለቲካና በዘር ልዩነት ላይ የተመሠረተው “የፌደራል ሥርአት” ተብየዉ የክልል አስተዳደር መዋቅርም፤ ዛሬ ጭራሽ የአገሪቱን ህልዉና እየተፈታተናት ያለው፡፡ 

ህወሐት (ኢሕአደግ) ኢትዮጵያን ለ27 ዓመት በገዛበት ወቅት “ብሄሮችና ብሄረሰቦች” የተባሉት እራሳቸዉን በእራሳቸው ሊያስተዳድሩ ቀርቶ፤ በላያቸው ላይ የአንድ ብሄር የገዥ መደብ (የህወሐት) ወኪሎች በፓርቲ ስም እየተመደቡላቸው፤ የእራሱን ስልጣን ለማስጠበቅ በአምባገነንነት የሚገዙና፤ የክልሉንና የሕዝቡን መሬትና ሀብት የሚዘርፉ ነበሩ የሚያስተዳድሯቸው፡፡ የሚያሳዝነው ባለፉት አምስት አመታት ህወሐት ከማእከላዊ ስልጣኑ ተወግዶም ስርቆቱ፤ የሀገሪቱን ሀብትና መሬት መዝረፉና፤ በሕዝቡ ላይ ግፍ መሥራቱ ሊቆም ቀርቶ ጭራሽ ባሰበት፡፡ የህወሐት ተማሪወች ተተኩበት! አዲሱ የብልጽግና ፓርቲም “ከብሄር ፖለቲካዉ” (“ዘረኝነት ስርአቱ”)  ሊላቀቅ አልቻለም፤ ሕዝቡ እንደዚያ የጓጓላትን፤ ነጻነት፤ ፍትሕና እኩልነት የሰፈነባትን ኢትዮጵያ ለመገንባት፤ ትክክለኛዉን አቅጣጫ መያዝ አልቻለም፤ ዛሬ ሕዝቡ በእሱም ተስፋ እየቆረጠ ነው፤ እንደህወሐት ጊዜው ሳይመሽበት፤ በቆራጥነት ተነሳስቶ አቅጣጫዉን ያስተካክላል ብለን ተስፋ እናደርጋለን፡፡ አለዚያ እሱም የታሪክ ተወቃሽ ይሆናል!  

“የብሄር ፖለቲካዉንና ዘረኝነቱን” አስወግደን፤ ኢትዮጵያ አገራችንን፤  በሀገር ፍቅር ስሜት በጋራ ለመገንባት፤
መፍትሄው ምንድን ነው? ምን ማድረግ ይሻለናል?  

በሚቀጥለው ጽሁፌ (ክፍል 3) ይህን ትልቅ አርእስት በተለይም በህገ መንግሥቱና “የፌደራል ስርአቱ” ዙሪያ ላይ በማተኮር በምችለው አቅም ለማብራራት እሞክራለሁ፤ እስከዚያ ግን አጠር አድርጌ፤ የሚከተሉትን መንደርደሪያ ሀሳቦች በትህትና አቀርባለሁ፤ 

1ኛ የ”ብሄራዊ ምክክሩ” ስኬታማ እንዲሆን በሚገባ መምራትና ሕዝቡን በሰፊው ማሳተፍ፤ በተለይም መንግሥት በቆራጥነት፤  በቅንነትና በግልጽነት ምክክሩ እንዲሳካ ከሕዝቡ ጎን በመቆም ከልቡ መሥራት ይኖርበታል፤  

2ኛ በህገ መንግሥቱ ላይ ትኩረት ተደርጎ፤ ካለፈው ስህተት በመማር፤ ሕዝቡ ያለፍርሀት በነጻ እንዲወያይበት ማድረግ፤  

3ኛ በክልሎች መሀል አወዛጋቢ የሆኑትን የማንነትና የመሬት ጥያቄወች፤ በሰላምና በዉይይት፤ በሕዝቡ በእራሱ ፍቃድ  እንዲፈቱ ሁኔታወችን ማመቻቸት፤ ብሄራዊ ምክክሩን “የብሄር ፖለቲከኞች” ከሕዝቡ ጠልፈው እንዳያመክኑት መጠበቅ!  

4ኛ በ”ፌደራል” (ክልል) አወቃቀሩ ሕዝቡ በሰፊው እንዲወያይበትና ሀሳቡን እንዲሰጥበት ማድረግ፤ የሀገሪቱን መሬት “በብሄር  ብሄረሰብ መከፋፈሉ” ተሻሽሎ፤ ለሀገር ሰላም፤ መረጋጋት፤ ለጋራ እድገትና አንድነት፤ “ህብረ ብሄርና ፌደራል  ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ”ን ለመገንባት አመች የሆነ ፍትሐዊ የክልል አስተዳደር እንዲመሠረት ተግቶ መሥራት፤  

5ኛ “ህገ መንግሥቱ አይነካም! ወይም ሙሉ በሙሉ መቀየር አለበት! የሚሉትን ሁለት ጫፍ ይዘው “ገመድ የሚጎትቱትን”  ማዳመጥ ትተን “ህገ መንግሥቱ ይሻሻል” በሚለው አቋም እንጽና! በ230 ዓመት እድሜው የአሜሪካን ህገ መንግሥት  ሙሉ በሙሉ ሳይቀየር 27 ጊዜ ተሻሽሏል፤ ከማሻሻያወቹ አንዱ (Amendment 13) ባርነትን በአሜሪካ ያስቀረው አንቀጽ  ነው፤ ሕዝባችን ከተስማማ በኢትዮጵያም ህገ መንግሥቱ “ፖለቲካ በብሄር ሀይማኖትና ዘር ጣልቃ እንዳይገባ” ወስኖ፤  በአገር ላይ ብቻ ያተኮሩ፤ ሀገር አቀፍና ህብረ ብሄር የሆኑ ፓርቲወች እንዲመራ ማድረግ ይቻላል፤ ይህ መሻሻል  (Amendment) እራሱ ትልቅ እፎይታና ሰላምን በአገራችን ያሰፍናል!  

 እነዚህን ሀሳቦች በክፍል 3 ለማብራራት እሞክራለሁ፤ በደህና ቆዩኝ! እስከዚያ ለአገራችን ቸር ወሬ ያሰማን!  

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ልጆቿን ይባርክ! ሰላም ያዉርድልን!  

ዓቢዩ ብርሌ (ጌራ)  
በሀገር ፍቅር ጉዞ መጽሐፍ ደራሲ  
የካቲት 23 ቀን 2015 ዓም (March 2nd, 2023) 

የኤዲተሩ ማስታወሻ : የዚህ ጽሁፍ ክፍል አንድ በኢትዮጵያ በሚታተመው የሪፖርተር ጋዜጣ ላይ ወጥቶ እንደነበር ጸሃፊው ገልጸዋል:: በሚከተለው አድራሻ ማግኘት ይቻላል https://www.ethiopianreporter.com/116104/

__

በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena 
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

የአድዋን 127ኛ በዓል የዐብይ ብልጽግና ሲያራክሰው ዝም ልንል አንችልም

Adwa _ Addis Ababa

አክሎግ ቢራራ (ዶር)

“ ከሲኦል ተመልሰንም ቢኾን ኢትዮጵያን እንበታትናታለን”! 
ህወሃት የአማራውን ሕዝብ ለማስፈራራትና ወልቃይትን ለማጠቃለል የሰጠን ማስጠንቀቂያ 

“ጠንካራ ሕዝብ አንድነቱንና ክብሩን በደሙ ያፀናል”  የአማራ ክልል ፕሬዝደንት ዶር ይልቃል ከፋለ 

“ሞት ሰለቸኝ፤ ውሸት ሰለቸኝ” ኦባንግ ሜቶ፤ የሰብአዊ መብት ጠበቃ 

“ዛሬ የውርደት ቀን ነው” አንዳርጋቸው ጽጌ፤ የአድዋን የድል በዓል ብልፅግናዎች ሲያቃውሱት ተመልክቶ የተናገረው 

“የፋሺስት ጣሊያን ጀነራል ግራዚያኒ ከሙታን ተነስቶ እንደገና አዲስ አበባን ይዞ የየካቲትን ፍጅት ሊድግም ነው? ይኽ ምን ይባላል? አቢይ አሕመድ እንደ ሮማዊው ቄሳር እንደ ኔሮ እንጦጦ ላይ ተሰይሞ ክራር እየተጫወተ በተድላ ደስታ እየተዝናና  ይሆን?”  ፕሮፌሰር ጳውሎስ ሚልኪያስ

“He (Abiy Ahmad) intentionally closed his eyes to the TPLF’s maneuver to keep its  modern weaponry and its professional defense forces. It seems that Abiy and the TPLF have  silently agreed that the handing over of old weapons and the disbanding of TPLF recruits is  enough to fool Ethiopians into believing that the TPLF has disarmed. “ 

Journalist Leo Okere, “Abiy Ahmad’s Machinations for Amharafrei,” February 22, 2023 

የዚህ ሃተታና ምክረ ሃሳብ ዋና ምክንያት ህወሃታዊያን፤ ኦህዴዳዊያን/ ኦነጋዊያንና የኦሮሞ ብልጽግና የዘውግ አክራሪዎች፤ ተተኪዎችና መሪዎች በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊነት በሚያምኑ አካላት፤ በተለይ በወጣቱ ትውልድ አባላት ለይ የሚያካሄዱትን ዘርፈ ብዙ ግፍና በደል የሚፈጽሙት በታቀደና ስልት ባለው ደረጃ እንጅ በዘፈቀደ አለማሆኑን ለማሳየት ነው። 

ለዚህ መረጃ ካስፈለገ የዐብይ ብልጽግና መንግሥት የአድዋን በዓል ፍጹምና አደገኛ ወደ ሆነ ጠባብ ብሄርተኝነት ለመቀየር መሞከሩ ነው። ይህ የፖለቲካ ቁማር አብዛኛውን የኦሮሞን ሕዝብ ይወክላል የሚል እምነት የለኝም። የሚያጠናክረው ክስተት ግን የማዘናጋትና አጀንዳዎችን የመቀያየር ጥበበኛ የሆኑት ጠቅላይ ሚንስትር (The Prime Minister who excels  in the art of deception) ኢትዮጵያን ከአንድ ግጭት ወደ ሌላ ግጭት፤ ከአንድ ቀውስ ወደ ሌላ ቀውስ እያሸጋገሯት መሆኑን ለማሳየት ነው። ህወሃት እኔ ካልገዛኋት ኢትዮጵያን እበታትናታለሁ ብሎ ፎከረ። ኦህዴድ/ኦነግ/የኦሮሞ ብልጽግና እኔ ኢትዮጵያን አፈራርሸና አድሸ ሙሉ በሙሉ የበላይ ሆኘ ካልገዛኋት ብዙ ሚሊየን ሕዝብ ቢጨፈጨፍ አልጠየቅም የሚል መርህ ይከተላል። 

የበላይነት የፖለቲካ ዘዴው ከፈረንጆች የተቀዳ ከፋፍለህ ግዝው መሆኑን መገንዘብና እኛ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊነት የምናምን ግለሰቦችና ስብስቦች ከጎጥ፤ ከመንደር፤ ከብሄር፤ ከኃይማኖት መለያ በላይ መጥቆ በመውጣት፤ ያለ ምንም ማመነታታት የምንሰበሰብበት፤ የምንደረጃበትና አማራጮችን የምንቃርብበት ወቅት ነው። ይህ ለነገ የሚተው አይደለም። 

ዛሬ ኢትዮጵያ በፖለቲካ ሥልጣን ፍላጎት የሰከሩ ብሄርተኞች የሚገዟት አገር እንጅ፤ በሕግ የበላይነት፤ በሕዝብ እህትማማችነት/ወንድማማችነት/አንድነት፤ በእውነተኛ እክሉልነትና በፍትህ የሚያምን የመንግሥት አመራር የላትም። መንግሥት አለ ብሎ ለመናገር የሚያስችል ሁኔታም የለም። ኢትዮጵያ በዓለም ደረጃ ተንቃለች ብል አልሳሳትም። 

ለምሳሌ፤ እስከ አፍንጫው የታጠቀው የኢትዮጵያ የመከላከያ ኃይል የሱዳንና የደቡብ ሱዳንን ወረራና ሰፊ መሬት ነጠቃ ሊከላከል አልቻለም። በተጻራሪው ግን ሕዝብን ለማስፈራራት ሲባል በአዲስ አበባ የጦር ጀቶችና ሄሊክፕተሮች ሰማይና ምድሩን ሲቆጣጠሩና ሕዝቡን ሲያስፈራሩ ታይተዋል። ሕዝብ እንደ ጠላት የሚታይባትን አገር በሃያኛ አንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማየት ያማል፤ ያሳፍራል፤ ያዋርዳል። ጠላቱ ማነው? ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው። 

የፖለቲካ ጠበብቱ አንዳርጋቸው ጽጌ ባለፈው የአድዋን 2023 የድል በዓል ለማየት በአዲስ አበባ እየተዘዋወረ የአይን ምስክር ሆኖ የተናገረውን ታሪክ ሲጠቅሰው ይኖራል። “ዛሬ የውርደት ቀን ነው” ያለው ወዶ አይደለም። የተናገረው ሃቁን ነው። በኦሮሞ ብልጽግና አቀነባባሪነትና አመቻችነት ኢትዮጵያን የሚገዙት ኦህዴዶች/ኦነጋዊያን ጽንፈኞችና እብሪተኞች ናቸው። 

በሌላ አነጋገር፤ ህወሃትን ተክቶ ኢትዮጵያን በበላይነትና በአምባገነንነት በሚገዛው የኦሮሞ ብልፅግና ፓርቲና በህወሃት መካከል ያለው ልዩነት ለይስሙላ ነው። በጋራ ጠላታቸው ላይ ይስማማሉ። የጋራ ጠላታቸው የአማራው ብሄር ለመሆኑ ተጨማሪ መረጃ አያስፈልገውም። 

ግን፤ በአማራው ሕዝብ ላይ የሚካሄደው ግፍና በደል፤ የዱር አራዊት የመሰለ (barbaric) ግድያ፤ ማፈናቀል፤ ማሳደድና ማዋረድ ቀስ በቀስ በአፋሩ፤ በሶማሌው፤ በወላይታው፤ በጉራጌው፤ በትግራዩና በሌላው ኢትዮጵያዊ ላይ ሁሉ እንደሚደርስ አንጠራጠር። የሚካሄደው ፍጹም የሆነ ሁሉን አቀፍ የበላይነት ነው። 

ዋናው ብሄር ተኮር ጭካኔ በአማራው ላይ መሆኑን በተለያዩ ትንተናዎቸ ኢህአዴግ ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ አሳይቻለሁ። አማራውን ከእልቂት እንዲድን ተከላክሎ ኢትዮጵያን ለመታደግ የሚቻለው ግን ሌላውንም በኢትዮጵያ የሚኖር ሕዝብ በመቀስቀስና በማበረታት እንጅ በመለያየት ሊሆን አይችልል የሚል እምነት አለኝ። ከፋፋዩን የኦሮሞ ብልፅግናን መንግሥት ካላጋለጥንና ከብሄር ባሻገር ካልተባበርን ኢትዮጵያ እንደ ሃገር ልትቀጥል አትችልም። 

እኛ የለት የለቱን አጀንዳ ብቻ ስለምናይ ነው እንጅ፤ ለዚህ አማራ ጠልነት ስር እየሰደደ መሄድ መሰረት የሆነው በ60ዎቹ ዓመታት በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲና በውጭ ስለ የብሄረሰቦች ጥያቄ (The national question) ተብሎ ስለሚጠራው ጉዳይ በሰፊው ንትርክ የተካሄ ትርክት መኖሩንና የተማሪውን እንቅስቃሴ ከሁለት እንደ ከፈለው መርሳት የለብንም። ዛሬ “ከአማራ በላይ አማራ ነን” የሚሉት የአማራው ምሁራን፤ ግራ ክንፍ አባላትና ስብስቦች ይህንን ከስታሊን የተወረሰ ትርክት እንዳስተጋቡትና እንዳጠናከሩት የረሱት ይመስለኛል። ስንት ወጣቶች በፖለቲካ ልዩነት ተጨፍጭፈዋል? በኢትዮጵያ ፋይዳቢስ ንትርክ ምክንያት ያሸነፉት የብሄር ነጻ አውጭ ግንባሮች ናቸው—በተለይ ህወሃትና ኦነግ። ብአዴን እኮ የህወሃት ልጅ ነው። 

በሌላ አነጋገር ህወሃት፤ ኦነግ፤ የኤርትራ ነጻ አውጭ ግንባርና ሌሎች ግንባሮች ይህንን የኢትዮጵያ ወጣቶች እንቅስቃሴና የብሄር ፖለቲካ ግብዓት ተጠቅመውበታል። በወቅቱ “ነጻ የምትወጡት ከማን ነው?” ብለን የጠየቅን ጥቂቶች ነን። ይህ ያለፈ ታሪክ ስለሆነ ወደ ጎን እተወዋለሁ። 

የዐብይ ብልጽግና ዛሬ የሚከተለው የፖለቲካ መስመር መሰረት የብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ጥያቄ ነው። እኔ የምገነዘበው፤ ሰሜነኞች (አቢሲኒያዎች) ለሶስት ሽህ ዓመታት ገዝተዋል፤ መዝብረዋል፤ ጨቁነዋል ወዘተ እና አሁን ጊዜው የኦሮሞ ብልጽግና የበላይነት መሆኑን በውድ ሆነ በግድ ተቀበሉ የሚለውን ሃቅ ነው። ጠቅላይ ሚንስትሩ የዚህ ስር ነቀል ለውጥ ወገንተኛ ናቸው (Abiy is partisan to this tectonic shift).  

በአንድ የዋሽንግተን ስብሰባ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲናን እኔና የኔ ጓደኛ ለመሆኑ “የአንተ ኢትዮጵያዊ ጀግና ማነው?” ብየ የኔ አጼ ቴዎድሮስና አፄ ምንኒልክ እንደሆኑ ነገርኩት። “እኔ ጀግና የለኝ” ያለው ትዝ ይለኛል። 

ስላ ወቅቱ ተደራራቢ ቀውስ ምሳሌዎች ልስጥ። 

አማራው ወደ አዲስ አበባ እንዳይገባ ማገብ  

በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ የሚካሄደው የአማራ ብሄር ጠልነትን በግልጽ በሚያሳይ ደረጃ አማራውን በብሄሩ እየለዩ ልክ በበረት እንደታጎረ እንስሳ “መጤ ነህ፤ ነፍጠኛ ነህ፤ የዱሮውን ናፋቂ ነህ፤ ውጣና አትገባም” ወዘተ እያሉ ከቤትና ከንብረቱ እያባረሩት ነው። ከዚህ የባሰ ግፍና በደል፤ ጭካኔና ዘረኛነት አለ? የለም። 

በውጭ የሚኖረው ግዙፍ አማራ የተከፋፈለና ለዓላማ አንድነት በጋራ ለመቆም ያልቻለ ስለሆነ፤ ይህንን የህልውና ጉዳይ እንኳን ለማስቆም በኣንድ ላይ ሆኖ ጠንካራ አቤቱታ ለተባበሩት መንግሥታት ሰብአዊ ኮሚሽን፤ ለአሜሪካና አውሮፓ ባለሥልጣናት፤ ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት፤ ለሂውማን ራይትስ ዎች፤ ለአምነስቲ ኢንተርናሺናል ለማቅረብ አልቻለም። ባጭሩ፤ ከግራ ክንፉ የወረስነው የእርስ በእርስ ጥላቻ፤ መነታረክና መከፋፈል አማራውን እየጎዳው ነው። 

የኦሮሞ ብልጽግና መንግሥት አማራውን እንደ እንስሳ ማጎር፤ ማሳደድ፤ ማዋረድ፤ መጨፍጨፍና ከቀየው በገፍ ማስወገድ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ነው። በተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ህግጋት መስፈርት ሲታይ ይህ ተደጋጋሚ ድርጊት የዐብይን ብልጽግና መንግሥት በሕግ ያስጠይቀዋል። ክስ መቅረብ አለበት። ለዚህ ባለሞያዎችን ለይቶ እንዲሳተፉ ማድረግና ገንዘብ መሰብሰብ ወሳኝ ነው። 

ችግሩ ይህ ብቻ አይደለም። 

አዲስ አበባ ወይንስ ሸገር?  

ባለፈው “Is Abiy a liability or an asset?” በሚለው ድርሰቴ እንዳሳየሁት፤ አዲስ አበባን ለማዳከም፤ ፋይዳ ቢስ ለማድረግና በምትኳ “የሸገር ከተማን” ግንባታ በአስቸኳይ ስኪታማ ለማድረግ የሚደረገው የተቀነባበረ እንቅስቃሴ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ይጎዳል። አዲስ አበባ ስትዳከም የሚጎዳው ማነው? ሸገርን ለመገንባት ፈሰስ የሚሆነውን ወደ አንድ ትሪልየን ብር የሚገመት መዋእለንዋይ ማን ይሸከመዋል? ሸገር የማን ከተማ ይሆናል? የሸገር የመጨረሻ ግብ ምንድን ነው? የሚሉትን ጥያቄዎች መመለስ ያስፈልጋል። ይህ መሰረታዊ ችግር ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን ይመለከታል። 

የኢትዮጵያን ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በብሄር መክፋፈል ለምን?  የኢትዮጵያን ተዋህዶ ቤተክርስትያን በዘውግ ለመከፋፈል የሚደረገው ሴራ፤ የአድዋን አገራዊና ዓለም አቀፋዊ በዓል ታሪክና ገጽታ በማናጋት፤ በማዛባትና የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ በማድረግ ለኦነጋዊያን/ኦህዴዳዊያን/የኦሮሞ ብልጽግና መንግሥት አይን ያወጣ የበላይነት አመች ሁኔታዎችን የመፍጠር ሂደት አፍራሽ ነው። ዘረኝነት ነው።

የአማራው ሕዝብ በመላው የኦሮምያ ክልል፤ በሰሜን ሸዋ፤ በቤኒ-ሻንጉል ጉሙዝ፤ በአዲስ አበባና ሌሎች አካባቢዎች በኦነጋዊያን ኃይል በጅምላ እየተጨፈጨፈ፤ ከቀየው እየተባረረ ወደ ደብረብርሃንና ሌሎች የአማራ ከተሞች እንዲሸሺ የሚደረገው ወዘተ የሚካሄደው ሁሉ የተያያዘና በሚገባ የታቀደ የበላይነት ጉዞ ነው። እኔ አንዱን ብሄር ተኮር ሂደት ከሌላው ለመለየት አልችልም። ስር ነቀል የሆነ መዋቅራዊ ለውጥ እየተካሄደ ነው። ይህ ሁሉ አፍራሽ ሂደት ነው (This is the  essence of deconstructing Ethiopian society with intent to create a “new Ethiopia.”).  

እኔ የምከራከረው የኢትዮጵያን ግዛታዊ አንድነት ለመቀጠል የሚቻለው ታላቁንና የመላውን በዓለም ዙሪያ የሚኖረውን፤ በተለይ በቅኝ ገዢዎች ቀንበር ስር ይሰቃይ የነበረውን ጥቁር ሕዝብ ለክብሩ፤ ለነጻነቱ ከዳር እሰከ ዳር የቀሰቀሰውን በታላቁ፤ በአስተዋዩ፤ በጥበበኛው፤ ሕዝብን ለአንድ አገራዊ ዓላማ በማስተባበር ኢትዮጵያን የነጻነት ተምሳሌት ያደረጉትን፤ ዛሬ ይህች አገር የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መዲና እንድትሆን መሰረት የጣሉትን አፄ ምንሊክን በማክበርና በማስታወስ ሊሆን ይገባል የሚል ነው። ታሪክን ለስልጣንና ለጥቅም እየበረዙ (Deconstructing and changing historical facts to fit ethnic  elite supremacy) ኢትዮጵያን ለመታደግ አይቻልም። ታሪክ ለስርቆት አያመችምና እስኪ ሰከን በሉ። 

የአድዋ መንፈስ ወጣቶችን በቲር ጋዝ በማፈን፤ በሰደፍ በመደብደብ፤ በማሰርና በማሳደድ፤ አድዋን በቤተክርስቲያን ሆነው ያከብሩ የነበሩ ወገኖቻችን በመግደል ሊሰረዝ አይችልም። የአድዋ መንፈስ የሚከበርበትን ቦታ በመቀየር ሊኮላሽ አይችልም። የአድዋ መንፈስ የእምየ ምኒልክንና የእቴጌ ጣይቱን ምስሎችና ፎቶግራፎች እንዳይሰራጩ በመከልከል ሊበከል አይችልም። የአድዋ መንፈስ የኢትዮጵያን አረንጓዴ ብጫ፤ ቀይ መለያ ሰንደቅ አላማ እንዳይታይ በማድረግ ሊበከል አይችልም። አድዋ በእያንዳንዱ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ልብ የሰረፀ ስለሆነ ማንም ኃይል ሊሰርዘው አይችልም። ዋጋ ግን ያስከፍላል። 

“የትላንት የታሪክ ምርኮኞች” ፋይዳ አለውን?  

በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ግፍና በደል፤ ጭቆናና ሌላ ጥፋት አልተሰራም ለማለት አልችልም። የአማራውን ሕዝብ ብቻ ለይቶ ላለፉት ጥፋቶች ተጠያቂ፤ ተከሳሺና ተወቃሽ ለማድረግ የሚያስችል መረጃ የለም። ውጣ ውረድ፤ ግፍና በደል በማንኛውም ሀገረ መንንግሥት ግንባታ ላይ የሚደረግ ክስተት ነው። ከሰራነው ስህተት መማርና ኢትዮጵያን ዘመናዊ አገር ማድረግ ግዴታችን ነው። ይህ ግዴታ ግን የአማራው ብቻ ሊሆን አይችልም። ላለፈው ቂም በቀልን እወጣለሁ፤ መግዛትና መብላት የኔ መብትና ተራ ነው በሚል መርህ፤ አማራውን ለይቶ ወደ መሰረታት ከተማ ወደ አዲስ አበባ አትገባም ማለት ከግፍ በላይ ግፍ ነው። ከፋሽስቶች ድርጊት በምን ይለያል? ወንጀል ነው። አማራውን “ምን ልታደርግ ትችላለህ?” የሚል የትእቢተኞች መልእክት ነው። አገር አፍራሽ ነው። አማራውን ሙሉ በሙሉ ማዋረድ ነው። በመሰረታት አገር ተዋርዶ ለመኖር የሚፈልግ አማራ ሆነ ሌላ ኢትዮጵያዊ የለም። በተጨማሪ፤ ማንነቱን የማይቀበልና ታሪኩን የሚክድ ሕዝብ ሊበለፅግ አይችልም። 

በተደጋጋሚ ለማሳሰብ የምፈልገው የአማራው ሕዝብ በመላው ኢትዮጵያ ከሌላው ብሄር፤ ብሄረሰብና ሕዝብ ጋር ተጋብቶ፤ ተዋልዶ፤ ተቻችሎ፤ የነዋሪውን ባህልና ቋንቋ ተቀብሎ፤ ጥሮ ግሮና ተጋምዶ የሚኖር ታላቅ ሕዝብ ነው። ስለሆነም፤ የአማራው እልቂት የሁሉም እልቂት መሆኑን መቀበል ብልሃተኛነትን ያንፀባርቃል። ኢትዮጵያን ለመታደግ አማራውን መታደግ፤ አማራውን ለመታደግ ኢትዮጵያን መታደግ ያስፈልጋል ማለት ነው። ይህ መርህ የአንድ ሳንቲም ግልባጭ ነው። 

እንቁ ሃሳብ እንጅ እንቁ ብሄር የለም  

በሁሉም ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ውስጥ የሚከሰቱትን ደካማ ጎኖች ማስተካከለል እንዳለ ሆኖ፤ የትላንት ታሪኩን ጠንካራ ጎን በሚገባ ለማስተጋባት፤ ለተከታታይ ትውልድ ለማስተላለፍ፤ ለማክበርና ለመጠቀም የማይችል ህብረተሰብና አገር የወደፊቱንም ተስፋና ብሩህ አቅጣጫ ለመቀየስ እንደማይቻል የማሰብ ግዴታ አለብን። ይህም በአንድ ብሄር የሚደረግ ጥረት አይደለም። ሁሉም ኢትዮጵያዊያን ክብር የሚሰጣቸው የሰው ፍጥረት መሆናቸውን የመቀበል ግዴታም የሁላችንም ነው። 

አፄ ምንሊክን የምናደንቃቸውና የምናከብራቸው የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ጀግና መሪ ስለሆኑ ነው። የሚያኮራ ታሪክ አለን እያልን የዐብይን ብልጽግና መንግሥት የምንተቸው ለምን ወራዳ ስራ ትሰራላችሁ በሚል ነው። የሰራችሁት ጥቁር ቀለም ነውና ያስጠይቃችኋል ማለቴ ነው። የዐብይ ብልፅግና ካቢኔ ለምን ከሌሎች አገሮች ታሪክ አይማርም?  

ለእውነት ተገዢ እንሁን!  

አሜሪካኖች ጆርጅ ዋሺንግተንን፤ ቱርኮች ከማል አታተርክን፤ ቻይኒሶች ጀኔራል ዩ ፌን፤ ራሺያኖች ታላቁ ጴጥሮስን (Peter  the Great) ወዘተ ያደንቃሉ፤ ያከብራሉ። መንግሥታታቸውን ይቀያይራሉ። መብታቸው ነው። ታሪካቸውን ግን መንግሥታቸውን በቀያየሩ ቁጥር ታሪካቸውን አብረው አይቀይሩም፤ አይክዱም፤ አያዋርዱም። ግፍና በደል አይፈጽሙም።

የጆርጅ ዋሽንግቶን ቅድመ አያቶች በቅኝ ገዢነታቸው የመጀመሪያውን ደረጃ የያዙ እንግሊዞች ስለሆኑ ጥቁር አሜሪካኖች ውይንም የአሜሪካ ህንዶች (indigenous millions who perished during the formation of the United States)  ዋሽንግተንን አያከብሯቸውም ማለት አይደለም። ይህ ቢሆን ኖሮ አሜሪካ ታላቅ አገር አትሆንም ነበር። 

በአድዋ በዓል አከበባር ላይ ባለፉት አምስት ዓመታት–በተለይ ባለፉት ሁለት– የተከሰተውን ጠብ ጫሪ፤ አማራ ጠል ንትርክ ሳንሰላስል የታዘብኩት የብሄር ፖለቲካ መጋቢ የሆነ አንድ የማይካድ የጋራ ዓላማ ሂደት አለ። ህወሃት አማራ ጠል በሆነው መመሪያው መሰረት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ በከፋ ደረጃ አንድ ሚሊየን ንጹህ ዜጎች እንዲሞቱ አደረገ። የኢትዮጵያ መንግሥት ባደረገው ግምገማ መሰረት በአፋር፤ በአማራና በትግራይ ክልሎች ብቻ የወደመውን የመዋእለ ንዋይ ፈሰስ ለመተካት ሃያ ሁለት ቢሊየን ዶላር ያስፈልጋል። የውጭ እዳዋ ከሃያ ሰባት ቢሊየን ዶላር በላይ የሆነችው ኢትዮጵያ ይህንን የካፒታል ክፍተት እንዴት እንደምታሟላው አላውቅም። ጦርነቱ አላስፈላጊና ዋጋ ያስከፈለ መሆኑን ግን በሚገባ አውቃለሁ። ከእብድነት በላይ እብድነት ነው። ተጠያቄነትን አስፈላጊ የሚያደርገው መረጃው ነው።  

ሃላፊነትና ተጠያቂነት የሌለባት ኢትዮጵያ  

On February 28, 2023, ዋሽንግቶን ፖስት የትግራይን ሕዝብ እልቂት በሚመለከት “Hundreds massacred in Ethiopia as  peace deal being reached” የዓለምን ሕዝብ ህሊና የሚቀሰቅስ ርእስ ለእልቂቱ ተጠያቂ የኤርትራ መንግሥት መሆኑን ያበስራል። 

“The agreement between the Ethiopian government and Tigrayan rebels brought about a  cease fire in a two-year war that had made northern Ethiopia one of the deadliest places in  the world. But the deal did not address the status of Eritrean troops. Neither the Ethiopian  nor Eritrean government has made any public statement on how Eritrean soldiers who  perpetrated mass killings like the most recent one near Adwa could be brought to justice. Joint investigations by the Ethiopian Human Rights Commission, whose head is appointed  by parliament, and the Office of the United Nations High Commissioner for Human Rights  have documented crimes against humanity and war crimes carried out by all sides up  until June 2021. The head of the EHRC, Daniel Bekele, said they had identified many other  incidents requiring investigation and they would be dealt with under a transitional justice  mechanism. 

The U.N. International Commission of Human Rights Experts, a separate body, also  documented war crimes by all sides, and said the government and its allies may have  committed crimes against humanity. In January, the Ethiopian government asked the  United States to support its bid to terminate the commission, calling its work “highly  politicized.” 

ትግሬ ቢሆን አማራ፤ አኟክ ቢሆን አፋር ወዘተ እልቂት በሕግ ያስጠይቃል። ዋሽንግተን ፖስት ቢፈልግና ቢያስብበት ኖሮ  Lemkin Institute for Genocide Prevention February 3, 2023 ያወጣውን “Statement in Support of an  International Investigation of Abiy Ahmed’s Crimes in Ethiopia” ሊጠቅስ ይችል ነበር። ይህንን አላደረገም ብለን  እኛ ጉዳዩን ቸል እንዳንለው አሳስባለሁ።  

በተጨማሪ ዋሽንግቶን ፖስት ሆነ ብሎ ይሁን በሌላ ምክንያት ትኩረት ያልሰጣቸው ጉዳዮች አሉ። ከነዚህ መካከል፤  

• በኦሮምያ ክልል በወለጋ፤ በሰሜን ሸዋ፤ በአዲስ አበባ ዙሪያ የሚካሄደውን የአማራ እልቂት፤ • ለጦርነቱ ምክንያት የሆነውና አሁንም ሌላ ጦርነት ሊቀሰቅስ የሚችለው የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምትና ራያ  ጉዳይና በማይካድራ የተፈጸመው የሚዘገንን የአማራ እልቂት፤ 

• የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ለመከፋፈል የተደረገው ሴራ፤ የታሰሩ አባቶችና ምእመናን፤ የተገደሉ  የእምነት አባላት፤

• የዐብይ ብልፅግና መንግሥት በበላይነት የሚያሽከረክረው የአዲስ አበባ አስተዳደር አማራው ተለይቶ ወደ አገሪቱ  መዲና ወደ አዲስ አበባ ልትገባ አትችልም የሚለው የሰብአዊ መብት ረገጣ ሊጠቀሱ ይገባ ነበር።  

ይህ ክፍተት መኖሩ እንዳለ ሆኖ ለሁሉም ዜጎች እልቂት የዐብይ ብልፅግናና የኦሮምያ መንግሥት ባለሥልጣናት፤ የህወሃትና የኦነግ/ኦህዴድ አመራሮች በሃላፊነት መጠየቅ አለባቸው።  

ኢትዮጵያ ወደ የት እየተጓዘች ነው? የሚለው ጥያቄ ተመልሷል ለማለት እችላለሁ። የህወሃት ከፍተኛ መሪዎችና ጠቅላይ  ሚንስትር ዐብይ አህመድ በተከታታይ ያካሄዱት የሁለትዮሽ (Bilateral agreement) ስምምነት ለመሸወዳችን ዋቢ ነው።  ኦባንግ ሜቶ “ውሸት ሰለችኝ” ያለውን ሃቅ እጋራለሁ። በኢትዮጵያ ስም ብዙ ውሸት ይነገራል። ከእርቅና ከሰላም ጀርባ  ያለውን ድብቅ ሴራ ማጤን ወሳኝ ነው። የሴራው ይዘት ፍትህ ሳይሆን ፍጹም የሆነ የኦነጋዊያን/ኦህዴዳዊያን የበላይነት  ነው። ዐብይ ከደሙ ንጹህ ናቸው የሚለውን አልቀበልም። አበው “ማነን ይዞ ጉዞ” የሚሉትን ብሂል እናጢን።  

እኔ የማቀርበውን ትችትና ምክረ ሃሳብ ወደ ጎን ትታችሁ ጋዜጠኛ ሊዖ ኦኬሪ በመረጃ ተደግፎ የጻፈውን ደጋግማችሁ  ብታነቡ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ የኢትዮጵያን ሕዝብ ሸውደውታል። ዋሽተዋል ማለቴ ነው። “ኢትዮጵያ!  ኢትዮጵያ! ኢትዮጵያ!” ማለት በራሱ የኢትዮጵያን አገራዊ አንድነት ስኬታማ ሊያደረገው አይችልም። የኢትዮጵያዊነት  መሰረቱና መስፈርቱ የዜጎች ደህንነት፤ እኩልነትና አንድነት፤ ፍትህ፤ የሕግ የበላይነት፤ እውነተኛ ዲሞክራሳዊ ስርዓት ወዘተ  ነው።  

ሌዖ ኦኬሪ እንዳስቀመጠው፤ በህወሃት አመራርና በኦሮሞ ኦነጋዊያን የበላይነት በሚመራው የብልፅግና መንግሥት ባለሥልጣናት መካከል የተዋቀረው የበላይነት መጋመድና ስልት ኢላማው አጀንዳዎችን በስልት በመቀያየር የአማራውን ሕዝብ፤ የአማራ ብልጽግና ፓርቲ አመራርን ጨምሮ ሙሉ በሙሉ ማንበርከክ ነው። “The love making between the  two (TPLF and Abiy) involves the foreplay of banishing from their ethnic heaven the “devil” they fear  most, the one who does not understand that there is no other love but ethnic love: the Amhara. The  Abiy-TPLF love makings in ethnic heaven, he said, are punctuated by the ecstatic cry, “neftenga,  neftegna, neftegna” when they reach their climax. “ 

የህወሃት የበላይ አመራርንና ጠቅላይ ሚንስትሩን ምን ጉዳይ ሊያስማማቸው ቻለ? የሚለውን ጋዜጠኛው ከኔ በበለጠ አንደበት አስቀምጦታል። አንድ ሚሊየን ህዝብ ተጨፍጭፎ፤ አማራው በማይካድራ፤ በደራ፤ በስቴ፤ በመተከል፤ በወለጋና በሌሎች አካባቢዎች በየለቱ እየተጨፈጨፈ፤ ወደ አዲስ አበባ ለመግባት አትችልም እየተባለ ወዘተ ወዘተ ለዚህ ሁሉ ጭካኔና የሰብአዊ መብት ቀውስ ማን በሃላፊነት ይጠየቃል? ብየ ራሴን ስጠይቅ፤ መልሱ ጋብቻው እኮ የተፈፀመው ሁለቱንም የበላይ አካላት በሚጠቅም ስልት በምስጢር ተስማምቶ ራስን በወንጀለኛነት ከሚያስጠይቅ የዓለም መንግሥታት ክስ ለመታደግ ነው እላለሁ። ጊዜ ይወስዳል እንጅ ይኼ ሸፍጠኛነትና ጮሌነት አያዋጣም። 

በውጭ የምንኖር ኢትዮጵያዊያን ህወሃትን ለማጋለጥና የምእራብ አገሮች አቋማቸውን እንዲያስተካክሉ ከፍተኛ ትግል አድርገናል። የገንዘብ እርዳታም አድርገናል። ይህንን ያደረግነው ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያ ህዝብ እንጅ ለዐብይ አህመድ አይደለም። አንሞኝ፤ ይህም አስተዋጾ ተረስቷል። ያ ጦርነት ለምን ተካሄደ? ማን አሸንፎ ወጣ? የሚለውን ታሪክ ይመራመረው። ሌዖ ኦኬሪ እንዲህ ሲል ያስቀመጠውን ግን እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ሊያስብበት ይገባል። 

“Abiy is trying hard to create a “free love” relation between Tigray and Oromia, a free love that gives  intense pleasure only when it mobilizes hatred to crush the Amhara. What for? I asked. You fool, he  said. To prevent the Amhara from continuing to be the symbol, the thinkers, and the motive force of  Ethiopian peace and unity. “ 

በአማራው ላይ የሚካሄደው የተቀነባበረ ከእልቂትና ውድመት ጋር የተያያዘ ሴራና መዋቅራዊ ለውጥ ይህንን ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊነት የቆመ ሰላም ወዳድ ሕዝብ ሙሉ በሙሉ ለመገርሰስ ነው። ጋዜጠኛው እንዳስቀመጠው፤ የማናውቀው፤ ግን ከቃላትና ዲስኩር ውጭ ሆኖ ለገመገመው ቀስ በቀስ ይፋ የሆነው የዐብይ እውነተኛ ገጽታ እንደሚከተለው ነው። 

አብይ የሚናገረው ቃላት እንደ ቅጠል ነው። መስፈርት መሆን ያለበበት የሚሰራው ነው (“Acta non verba.” Words are  leaves, and deeds are fruits. Look at what he does and not at what he says. Not only is he treating the  TPLF as a victor and Ethiopia as defeated, said he, Abiy has also made his own the TPLF hatred of the 

Amhara. He lets the Amhara be massacred systematically in Oromia. He is tacitly cooperating with  ethnicist forces to make Oromia, as the Germans would say, “Amharafrei.” “ 

በሌላ አነጋገር፤ ዐብይ አሕመድ የአማራውን ጭፍጨፋ የማያወግዝበት፤ የአዲስ አበባን እገባና የኦርቶዶክስን ክፍፍል የማይተችበት ዋና ምክንያት የሴራው አካል በመሆኑ ነው። “ In the case of Ethiopia, “Amharafrei” means cleansing  the ethnic kilils of Amharas by all means necessary. Look, he said, not only Abiy has tacitly consented to  make Oromia and other kilils “Amharafrei” by killing and displacing Amharas, he is also quietly  supporting the arch-ethnicist Shimelis Abdissa and Adanech Abeibei’s scheme to make Addis Ababa  “Amharafrei” by preventing Amharas to travel to Addis Ababa. Likewise, he is preparing the ground to  deliver Wolqait and Raya to the TPLF. Ask yourself, my friend continued, why is Abiy not raising a  finger to liberate the hundreds of Amharas captured during the war and are still kept in horrendous  conditions in TPLF prisons, despite the Pretoria Agreement? Why does Abiy still allow the continued  occupation of Aber Gele and adjacent Amhara areas by TPLF forces? Why does Abiy try to disarm the  Amhara Special Forces despite the continued presence of TPLF forces in eastern Amhara, while allowing  the TPLF to keep almost intact the Tigray Defense Forces? Because, for Abiy and the TPLF, every  opportunity to create an “Amharafrei” Ethiopia is not to be missed.” 

እኛ ኢትዮጵያዊያን ለመናገር ያልደፈርነውን፤ አሁንም ቢሆን ብዙዎቻችን ችላ ያላልነውን ጋዜጠኛው በትክክክል አቅርቦልናል። ዐብይ አህመድ ሸውዶናል ማለት በቂ አይደለም። አደጋውን በሚገባ ተገንዝቦ የኦሮሞ ብልፅግና በበላይ ሆኖ የሚመራው መንግሥት በሁሉም መስፈርቶች ለኢትዮጵያ፤ ለአፍሪካ ቀንድና ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፤ ኦሮሞውን ጨምሮ የማያዋጣ መሆኑን የምናስተጋባበት ወቅት ደርሷል። 

ምክረ ሃሳቦችን ልጠቁም 

1. የአማራው ክልል ባለሥልጣናት፤ የአማራ ብልፅግና ፓርቲ አባላት፤ የአማራ ስብስቦችና ተቆርቋሪ ግለሰቦች በሙሉ ከአሁን በኋላ በኦሮሞ ብልጽግና የበላይነት በሚመራው በዐብይ መንግሥት ላይ ያላቸውን እምነት ወደ ጎን ትተው የራሳቸውንን አቅም መገንባት፤ ማጠናከርና እየተናበቡ መስራት ይገባቸዋል። “ባንተባበር ይበሉን ነበር” የሚለው የወጣቱ አማራ ቀስቃሽ መፈክር ወደ አቅም ግንባታ እንዲሸጋገር ሁላችንም ድርሻችንን እንድንወጣ አደራ እላለሁ። ውጭ የምንኖረው ከማውራትና ሌላውን ከመተቸት ወጣ ብለን በአቅም ግንባታው ስራ ላይ እንረባረብ እላለሁ። 

2. የአማራው መንግሥት ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች፤ ዘመነ ካሴን፤ ሌሎችን በብዙ ሽይ የሚቆጠሩ የፋኖ፤ የልዩ ኃይል አባላት ጨምሮ በአስቸኳይ እንዲፈታ አሳስባለሁ። 

ከላይ እንዳሳየሁት በህወሃት የበላይ መሪዎችና በዐብይ መካከል የተካሄደውን ስምምነትና ይፋ ያልሆነውን ጸረ-አማራ “ቃል ኪዳን” ስገመግም (ለምሳሌ ያልተፈታው የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምትና ራያ ጉዳይ) የአማራው ክልል ራሱን ከአስከፊ የወያኔ ጥቃት ለመከላከል የሚችለው ፋኖውን፤ ልዩ ኃይሉን ትጥቅ በማስፈታት ሳይሆን ተጨማሪ ኃይል በማሰልጠን ነው እላለሁ።  

3. የኢትዮጵያን ኢህአዴግ/ብልጽግና የፈጠራቸውን ስርዓታዊና መዋቅራዊ ቀውሶች ለጊዜውም ቢሆን ለመፍታት የሚቻለው የአማራና የኦሮሞ ብልፅግና አመራሮች በሚያደርጉት የሁለትዮሽ ውይይት ብቻ ሊሆን አይችልም። የአማራን ብልፅግና አመራር የምመክረው ይህ ሁሉንም ኢትዮጵያዊያን የሚመለከት አስቸኳይ ጉዳይ ስለሆነ በውይይቱና በመፍትሄው ድርድሩ ላይ ሁሉም የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች እንዲሳተፉ ግፊት እንዲያደርግ ምክሬን እለግሳለሁ። 

4. የዐብይ ብልፅግና አመራሮች በአድዋ በዓል ዙሪያ በቤተክርስትያን ውስጥ ሆነው በዓሉን በሰላም ሲያከብሩ በነበሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ ለተፈጸመው እልቂት ሙሉ በሙሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ ዓለም አቀፍ ጥሪ የማድረግ ግዴታ አለብን። 

5. የብልጽግና፤ የኦህዴድ/ኦነግና የአዲስ አበባ ከተማ ባለሥልጣናት የአማራውን ብሄር እየለዩ ወደ አዲስ አበባ ልትገባ አትችልም የሚሉት የሚዘገንን የሰብአዊ መብት ጥሰት ሕገ ወጥ ስለሆነ መላው የዓለም ሕዝብ እንዲያውቀው አናድርግ፤ ክስ እንዲመሰረት ድጋፍ እንለግስ፤ ሰላማዊ ሰልፎች እንጥራ፤ የአፍሪካ አንድነንት ድርጅትና ኢጋድ ጫና እንዲያደርጉ ዘመቻ እንጀምር እላለሁ።

6. ህወሃት በማኒፌስቶው ላይ ያወጣውን ፀረ-አማራ መርህና ኦህዴድ/ኦነግ የአማራውን አስደናቂ የሃገረ መንግሥት ምስረታ ዘርፈ ብዙ ሚና “አፈራርሰን አዲሲቱን ኢትዮጵያን እንመሰርታለን” የሚሉት በሥልጣን የበላይነት የሰከሩ ጽንፈኞች የሚጠቀሙት ሕገ መንግሥት ኢትዮጵያን ያሸጋገራት ከህወሃት የበላይነት ወደ ኦሮሞ ብልፅግና የበላይነት መሆኑ በማያሻማ ደረጃ የመቀበል ግዴታችን ድምጽ በማሰማት እንድንወጣ አሳስባለሁ። 

ይህ የብሄር ልዩነትን መሰረት ያደረገ፤ ግጭቶችን የሚፈለፍል ሕገ መንግሥትና የክልል አስተዳደር በአስቸኳይ መቀየር አለበት። በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ የምንኖር አገር ወዳዶች ይህ ሕገ መንግሥት እንዲቀየር የተቀነባበረ የሕዝብ ግንኙነትና የሕዝባዊ ዲፕሎማሲ ስራ መስራት አለብን። ባለሞያዎችን ሰብስበን አማራጮችን የማቅረብ ግዴታ አለብን። 

7. በዜግነት መብት ላይ ብቻ የሚቀነባበረው አዲስ ሕገ መንግሥት ልክ ሌሎች የአፍሪካ አገሮች እንደ ደነገጉት በኃይማኖትና በብሄር የፖለቲካ ፓርቲ መመስረት ከሕግ ውጭና የዜጎች ግዴታ መሆኑን መደንገግ አለበት። 

በመጨረሻ፤ የኢትዮጵያ መሰረታዊና መዋቅራዊ ተግዳሮቶች እየትባባሱ መሄዳቸውን አብዛኛው የኢትዮጵያና የዓለም ሕዝብ  ይጋራል። ምን እናድርግ በሚለው ላይ ግን ብዙ ስራ ፊታችን ላይ ተደቅኗል። ሁለት ምክረ ሃሳቦችን ልጠቁምና አስቡበት፤ 

• ለሁሉም በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊነት የሚያምኑ የህብረ-ብሄር፤ ብሄር፤ ብሄረሰቦችና ሕዝቦች ተወካዮች፤ አገር ወዳዶች፤ ባለሞያዎችና ሌሎች ባለድርሻዎች በአንድ ላይ ሰብሶብ ምክክር እንዲያደርጉና በፍኖት ካርታ እንዲስማሙ አስቸኳይ ዓለም አቀፍ፤ አገር አቀፍ ጥሪ ማድረግ እና፤ 

• በኢትዮጵያዊያና ላይ የሚካሄደውን የሚዘገንን አፈና፤ ግድያ፤ ብሄር ተኮር እልቂትና ማፈናቀል በሚመለከት ተከታታይ ሰላማዊ ሰልፎች ማካሄድ፤ አቤቱታዎችን በጽሁፍና በመረጃ እየደገፉ 

ለሚመለከታቸው የተባበሩት መንግሥታት፤ ለአሜሪክና ለአውሮፓ ባለሥልጣናት፤ ለአፍሪካ አንድነት መስሪያ ቤት መሪዎችና ለሌሎች ለሚመለከታቸው ሁሉ ማድረስ፤ በቁርጠኛነት የሚከታተል አካል መመስረት የሚል ሃሳብ አቀርባለሁ።  

__

በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena 
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

 

ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ በዓለ አድዋ (ከቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ)

መፈንቅለ-በዓለ-አድዋ

(ከቀሲስ ኤፍሬም እሸቴ)

መግቢያ

የዳግማዊ አጼ ምኒልክ የክተት አዋጅ ከያዛቸው ቁምነገሮች መካከል አንደኛው ንጉሠ ነገሥቱ የመጣውን ጠላት የገለጹበት መንገድ ነው። በአጭሩ እንዲህ ይነበባል፡-

“… አሁንም አገርን የሚያጠፋ ሃይማኖትን የሚለውጥ ጠላት እግዚአብሔር የወሰነልንን የባህር በር አልፎ መጥቷል እና እኔም ያገሬን ከብት ማለቅ የሰውንም መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው  እያለፈ ደግሞ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፡፡  አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም፡፡ ያገሬ ሰው ካሁን ቀደም የበደልኩህ አይመስለኝም፡፡ አንተም እስካሁን አላስቀየምከኝም፡፡ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ፤ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ ለሚስትህ ለሃይማኖትህ ስትል በሃዘን እርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ አልተውህም፡፡  ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም … “

ይህ በብዙ የታሪክ ሊቃውንት ብዙ የተባለበት የክተት አዋጅ ለእኔ የሚከተሉትን ቁምነገሮች ይዟል። 1ኛ/ የመጣው ጠላት “አገርን የሚያጠፋ ሃይማኖትን የሚለውጥ ጠላት” መሆኑ፣ 2ኛ/ ይህንን ጠላት ለመዋጋት ደግሞ አገርንና ሃይማኖትን ከመውደድ በተጨማሪ “ለልጅህ ለሚስትህ ስትል” በምትለው ሐረግ ሰው ለቤተሰቡ ሲል መዋጋት እንዳለበት ያሳስባል። በጠቅላላው የኢትዮጵያ ታሪክም የምንገነዘው ጠላቶቻችን አገራችንን አጥፍተዋል፣ ሃይማኖታችንን ተዋግተዋል፣ ቤት-ቤተሰቦቻችንን ንደዋል፣ አፍርሰዋል። ዛሬስ? በ 2015 ዓ.ም?

መንግሥት በጣሊያን መንገድ

ወራሪው የጣሊያን ጦር የጥፋቱ ዒላማ አድርጎ የተነሣባቸው ነገሮች አገር፣ ሃይማኖትና ቤተሰብ ነገሩ። ሌሎች ጥፍቶች በሙሉ ቢዘረዘሩ ከነዚህ ከሦስቱ አይወጡም። በሚደንቅ ሁኔታ ዛሬም በሀገራችን ያሉት ኢትዮጵያዊ ቆዳ ያላቸው አድራረ ኢትዮዽያ በነዚህ በሦስት ጉዳቶች ላይ መዝመታቸውን ስንመለከት የታሪኩ ተመሳሳይነት ያስደንቀናል።

የብልጽግና መንግሥት ለማንም በማያሻማ ሁኔታ በነዚህ ሦስት ተቋማት ላይ ግልጽ ጦርነት ማወጁን በግልጽና በተግባር አሳይቶናል።

U. መፈንቅለ ሲኖዶስ

መንግሥት ቀደም ብለው ከመጡት ፀረ ሃይማኖት መንግሥታት በመማር የእምነት መሪዎችን ከመቀየር ሙሉ በሙሉ ተቋሙን ወደ መውረስ (መፈንቅለ ቅዱስ ሲኖዶስ) ተሸጋግሯል። ለረዥም ጊዜ በታቀደ ሁኔታ በተለይም የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን ቅርጿን፣ ዓላማዋን፣ ቀኖናዋን፣ ታሪኳንና  አንድነቷን ለመናድ መንግሥታዊ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ይገኛል። በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ የተወሰኑ ጳጳሳትን በመገንጠል 25 መነኮሳትን እንዲሾሙ አስደርገዋል። በመንግሥት ታጣቂ በመታገዝ አብያተ ክርስቲያናትና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን ንብረቶች በጉልበት ተወርሰዋል።

ይህ ሁሉ ወንጀል ሲፈጸም መላው ኢትዮጵያ በከፍተኛ ኃዘን ሲመታ፣ በቅዱስ ሲኖዶስ መሪነት ኢትዮጵያውያን ያለ ምንም የእምነት ልዩነት ጉዳዩን በይፋ ሲቃወሙ እና አስፈላጊ ከሆነ ሕይወታቸውን አሳልፈው ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን በዕንባ ጭምር መግለጽ ሲጀምሩ መንግሥት አንገቱን ለመድፋት መገደዱን፣ የችግሩ ጠንሳሸና ባለቤት በችግር ፈቺነት ራሱን ሲያቀርብ ተመልክተናል። በጣም ተወኔታዊነት የተለበስ የዕርቅ ውይይት በቴሌቪዥን ሲተላለፍም አየን። ጠ/ሚሩ ቅዱስ ፓትርያርኩን “የጠፉትን በጎች ይዤ መጣሁ” ሲሉ ሰማን። ቀኖና ጥሰው ከወጡት የቀድሞ ጳጳሳት ሁለቱ ሲመለሱ አንደኛው አለመመለሳቸውን፣ ሾምናቸው ያሏቸው መነኮሳትም የጠ/ሚሩንና የፍርድ ቤት ውሳኔን ተቃውመው በሕገ ወጥ መንገዳቸው መቀጠላቸውን አየን። ጠሚሩ ፊጸምኩት ያሉት እርቅ የስትራቴጂካዊ ማፈግፈግ እንጂ ከልብ የተደረገ መመለስ አለመሆኑን በተግባር አየን። እነሆ መፈንቅለ ሲኖዶሱ አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው። ይህ ችግር ሳይቀረፍ ሌላ ችግር ፈንድቶ ወጣ። መፈንቅለ ቤተሰብ።

ለ. ቤተሰብ የማፍረስ ዘመቻ

የብልጽግና መንግሥት ከሚታወቅባቸው ተግባራትና በታሪክ ፊት ለዘወትርም ከሚነሳባቸው ተግባራት አንዱ በቤተሰብ ማፍረስ ላይ ያደረገው ትልቅ ዘመቻ ነው:: ለውጥ መጣ ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ በሚያሰልስ ሁኔታ የተለያዩ ብሔረሰቦች አባላት (በዋነኝነት የአማራው) ደም ያለ ገደብ ፈስሷል። የዘር ማጽዳት ተፈጽሟል፤ እየተፈጸመም ነው። አጼ ምኒልክ በአዋጃቸው “ለልጅህ ለሚስትህ ስትል” እንዳሉት ብልጽግናም ልጄን/ ልጆቼን፣ ሚስቴን/ ትዳሬን (ቤተሰቤን) ለሚል ሁሉ ብልጽግና  ጠላት ሆኖ መጥቷል። ማንም ጠላት ለማድረግ አስቦ ሙሉ ለሙሉ ሊፈጽም ያልቻለውን ቤተሰብ የመበተን ተግባር በመፈጸም ላይ ይገኛል። ቤት ያፈርሷል፤ ቤተሰብ ይንዳል። ሕዝብ እትዝብቱ ከተቀበረበት ቀዬው በጉልበት ተነቅሏል፡ እየተነቀለ ነው። ሀብቱ፣ ንብረቱ ወድሟል፣ ተዘርፏል። እየወደመ እየተዘረፈም ነው። “ቢይ ኩን አባ’ ቀባ” (ይህ ሀገር ባለቤት አለው) በሚል የምሥጢር ቃል ተጠቅልሎ ኦሮምኛ ተናጋሪ ያልሆነ ሁሉ “ሀገርህ አይደለም፣ ቤትህ ንብረትህ አይደለም” ተብሎ ተዘምኖበታል:: ሕጻናት ልጆቹ በጅብ ተበልተዋል፣ ነፍሰ ጡር ሚስት በጥይት ተገድላለች፣ የተረፉት ወደማያውቁት “ሀገራቸው” ተባርረው በድንኳንና በሜዳ ተበትነው ቀርተዋል። ይህ ሁሉ ሳያንስ አድዋ ላይ መፈንቅለ በዓል ተጀምሯል።

ሐ . አድዋን መሥረቅና መቅበር

የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ.ም የዋለው የአድዋ በዓል በታሪክ ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ነው። በዓሉን ለማክበር የወጡ ሰዎች በመንግሥታቸው የተገደሉበት፣ የተደበደቡበት፣ የተዋከቡበት፣ የተንገላቱበት አሳዛኝ ቀን ነው። ከበዓሉ ቀን አስቀድሞ የመንግሥት ጎምቱ ባለሥልጣናት የዘመቻውን መሪ አጼ ምኒልክን ከበዓሉ ለማውጣት መንቀሳቀስ ጀመሩ። የቲያትር ቤቶች ንጉሡና ንግሥቲቱ የሌሉበት ድራማ እንዲያዘጋጁ መታዘዛቸው ታወቀ:: ሚዲያዎች ይህንኑ በተግባር አውለውት ታየ። ሕዝብ አዘነ። ተቆጣ፡፡ መንግሥት የሕዝቡን የቍጣ ማዕበል ሲመለከት ታክቲኩን በመቀየር በዓሉን መከላከያ እንዲያከብረው ትዕዛዝ ሰጠ። መከላከያም ያለውን ሕዝባዊ ቅቡልነት በመጠቀም በዓሉን አዘጋጀ። በጥሩ ሁኔታ ተከናወነ።

ዋናው በዓሉ በሚከበርበት በዳግማዊ ምኒልክ አደባባይ ጠዋት የመንግሥት ባለሥልጣናት በሐውልቱ ሥር የአበባ ጉንጉን አስቀምጠው ተመለሱ። ምዕመናን በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ዓመታዊ የቅ/ጊዮርጊስንና የአድዋን በዓል ለማክበር  ተሰበሰቡ፡፡ ከአደባባዩ በተለያዩ አቅጣጫዎች ወደ በዓሉ ለመግባት የሞከሩ ወገኖች ተከለከሉ። የዳግማዊ አጼ ምኒልክና የኢትዮጵያ ሰንደቅ ያለባቸው አልባሳትን የለበሱ እየተለዩ በፖሊስ ጥቃት ደረሰባቸው፡፡ ሌሎችም ላይ አስለቃሽ ጭስ ተተኮሰ፡፡ ሕዝብ ተተረማመሰ፣ ተረጋገጠ። ብዙ ሰው ራሱን ስቶ ወደቀ። ከፖሊስ የተተኮሰ ጥይት የሰው ሕይወት ቀጠፈ።

በቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሕዝቡ ላይ አስለቃሽ ጭስ በመተኮሱ ሕጻናት፣ ወጣቶችና አረጋውያን፤ ምዕመናን፣ ካህናትና መነኮሳት ራሳቸውን እየተሳቱ ወደቁ። በአምቡላንሶች ወደ ሕክምና ተቋማት ተወሰዱ። ታቦተ ሕጉም በዓሉ ሳይፈጸም ወደ መንበሩ ተመለሰ። በዓሉም ተቋረጠ፡፡ ሕዝብም አለቀሰ።

ይህ ሁሉ ለምን?

የካቲት 23 ቀን በብልጽግና እና አክራሪ ጎሰኞችና ስትራቴጂስቶች የተያዘው ዘዴ ሕዝቡ ተረጋግቶ በዓሉን እንዳያከብር ማድረግና በዓሉን ከሕዝብ በዓልነት ወደ መንግሥት በዓልነት የመውሰድ “መፈንቅለ-በዓል” ነው። ምን ይጠቅመዋል የሚለውን በአጭሩ ላቅርብ።

አድዋ ሕዝባዊ፣ ሀገራዊ/ ዓለምአቀፋዊ እና በተወሰነ ደረጃም ሃይማኖታዊ በዓል ወደ መሆን ያደገ በዓል ነው። ሕዝባዊ ነው ማለት ያለ ምንም አስገዳጅነት፣ ያለ ማንም አስተባባሪነት እና መሪነት በሕዝብ ፈቃድና በሕዝብ ገንዘብና ጉልበት፣ ኃይልና ጥበብ የሚከበር በዓል በመሆኑ ነው። በዓሉ በሀገራችን ሁሉም አካባቢዎች ስለሚከበር ሀገራዊ ነው። በመላው ዓለም እንደ አድዋ ለመከበር ዕድል ያገኘ ኢትዮጵያዊ በዓል የለም። በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች ባሉ ከተሞች ይፋዊ ሆኖ እንዲከበር ዕውቅና ያገኘ በዓልም ነው። ከዚህም በላይ ድሉ የተገኘው በእግዚአብሔር ቸርነት በሰማዕቱ በቅ/ጊዮርጊስ አማላጅነትና ተራዳዒነት ነው ብላ የምታምነው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በመናገሻ ገነት ጽጌ ቅ/ጊዮርጊስ ታቦተ ሕጉን አውጥታ በታላቅ ሁኔታ ታከብረዋለች:: ታዲያ መንግሥት እነዚህን ሁሉ አከባበሮች በመደምሰስ የግሉ በዓል ለማድረግ ኩ’ዴታ/coup d’etat ሲፈጽም እጅ ከፍንጅ ተይዟል:: ግን ለምን ኩ’ዴታ አስፈለገ?

ብልጽግና እና ሌሎች አክራሪ ብሔረተኞች የተቸገሩት ነገር ሕዝብ የኢትዮጵያ ማማ እና ካስማ መሆኑን ለማስቀረት ለማስቀየር አለመቻላቸው ነው። አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ሰንደቅ ዓላማችን ላይ ከ30 ዓመታት በላይ መንግሥታዊ የጥላቻ ዘመቻ ተካሂዶበታል፡፡ በዘመነ ወያኔ የነበረው ሰንደቅን የመጥላት ዘመቻ በዘመነ ብልጽግና በመሣሪያ በታገዘ ሁኔታ መንግሥት መር ሀገራዊ እመቃ/ Crackdown ወደመሆን የተሻገረ ጉዳይ ነው። የካቲት 23 ቀን 2015 ዓ.ም ፖሊሶች የኢትዮጵያን ሰንደቅ በያዙና በለበሱ ሰዎች የፈጸሙት ግፍ ጉዳዩ መንግሥታዊ እንጂ የግለሰብ ፖሊሶች ችግር አለመሆኑን ቁልጭ አድርጎ አሳይቷል። ጠበቃ አንዱዓለም በዕውቀቱ ስለዚሁ ጉዳይ ሲገልጽ የሚከተለውን ብሏል።

“የባሰ አታምጣ አለ ያገሬ ሰው! አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሲያይ የሚያቅለሸልሸው የጸጥታ አካል ይዘን የት ልንደርስ ነው?!🤔 እኔን ይቺን ቲሸርት ለማስወለቅ የተረባረበው የፖሊስ ብዛት ትንሽ ኃይል ቢጨምር አልፋሽጋ ላይ [በሱዳን] የተወሰደብንን መሬት ማስመለስ ይችል ነበር!!😀 ደሞኮ የአንዳንዶቹ የንቀታቸው ልክ! እንግዲህ መንግሥት በዓሉን የምታከብርበትንም ሆነ የምትለብሰውን ልብስ እኔ ነኝ የምመርጥልህ  ብሏል!.. ከታሪክ ጋር ግብግብ ነው የተያዘው!!”

መንግሥት በምኒልክ አደባባይና በቅ/ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በዓሉን ለማክበር የተሰበሰበውን ሕዝብ በኃይል በሚበትንበት በዚያው ሰዓት በመስቀል አደባባይ ግን ታላቅ መንግሥታዊ የአድዋ በዓል በመከበር ላይ ነበር። የብዙ ሀገራት የጦር አታሼዎች፣ ጸጉረ ልውጥ የውጪ ሀገር ሰዎች፣ በመንግሥት ተመርጠው የመጡ የጠሚ ዐቢይን ፎቶና መፈክሮች ያነገቡ የከተማው ነዋሪዎች እና የተለያዩ የመለዮ ለባሽ ክፍሎች (መከላከያ፣ አየር ኃይል፣ ፖሊስ ወዘተ) የተሳተፉበት በዓል በሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።

ይህ በመንግሥት ደምቆ የተከበረው በዓል ጊዮርጊስ አካባቢ ከተከበረው በዓይነቱም በይዘቱም የተለየ ነው:: የበዓሉ ባለቤትነት ለጊዜው ለመለዮ ለባሹ ይሰጥ እንጂ በቀላሉ ከመከላከያውም ሊወሰድ የሚችል ነው:: ያለሕግ የተሰጠ ነገር ያለ ሕግ ይወሰዳል። ጦሩም የእኔ በዓል ነው ብሎ ሊከራከርለት የሚችለው ጉዳይ አይደለም።

መንግሥታዊ በዓልን በአንድ ደብዳቤ መሠረዝ ይቻላል። በሕዝብ ፍቅር ተጀምሮ በሕዝብ ልብ የተቀበረን በዓል ግን በምንም አዋጅ ልታስቀረው አትችልም። መፈንቅለ በዓሉ ሳይጀመር የከሸፈውም ለዚህ ነው።

ማጠቃለያ

የመንግሥት ርምጃ የግብታዊነት ውጤት አይደለም። የታቀደ እና የታሰበበት ነው። በጊዜያዊ ጩኸትና ተቃውሞ ይገታል ብሎ ማሰብም የዋህነት ይሆናል። መሠረታዊ ዓላማቸውን ከመረዳትና በመሠረታዊና አመክኖአዊ ተቃውሞ ማድረግ ግዴታ ነው። በተለይም መንግሥት ይህንን ፍፁም ፀረ ኢትዮጵያዊ እና ፀረ ሃይማኖታዊ ተግባር የሚፈጽመው በኦሮሞ ስም እንደመሆኑ ጉዳዩን ለኦሮሞ ሕዝብ በግልጽ ከማስረዳት ጋራ ይህንን አክራሪ እንቅስቃሴ ፊት ለፊት መግጠም ይገባል።

ምናልባት በመንግሥት ኃላፊዎች ውስጥ የቀረ እንጥፍጣፊ የኃላፊነት ስሜት ካለ ይህንን ሀገር አፍራሽ ታሪክ-ጠልነት በመተው አድዋን የመሳሰሉ የአደባባይ በዓላት የሚከበሩበት ሕግ በምክር ቤት ማስጸደቅና ተግባራዊ ማድረግ ይገባዋል።

በሀገሪቱ መንፈሳዊና ማኅበራዊ ተቋማት ላይ የተጀመረው የጉልበት ወረራ እና ሕዝብን ከቤቱ የማፈናቀል ዘመቻ አንደ መፈንቅለ ሲኖዶስና የአድዋ በዓል ግልበጣ ሁሉ መንግሥት ላይ የሚያመጣው ተቃውሞ ከባድ ይሆናል። ለጊዜው እሳተ ገሞራው ባለመታየቱ የሌለ ይመስላል። መፈንዳቱ ግን አይቀርም:: ብቻውን ሳይሆን ከመሬት መንቀጥቀጥና ከማዕበሎች ጋራ ተደባልቆ። በኢትዮጵያ እየጋመ የመጣው ሕዝባዊ ቁጣ ማዕበልና ርዕደመሬት ሆኖ ይመጣል። የሚተርፍ አይኖርም። አስተዋይ መንግሥት ለራሱም ለሀገርም ሲል መንገዱን ያስተካክላል፡፡

በዳግማዊ ምኒልክ አደባባይ ግርግር መካከል አንዲት ዕድሜዋ ከ15 ዓመት የማይበልጥ ልጅ የተናገራችውን ነገር መጥቀስ ለጽሑፉ ጥሩ ማጠቃለያ ይሆናል። “አትሩጡ እምነታችሁ ያድናችኋል! ፈረሰኛው ይመጣል! እንደዚህ እንዳስለቀሱን አይቀርም!” የብላቴናዋ ንግግር ከመንፈስ እንጂ ከሥጋና ከደም አይደለም። ልብ ያለው ልብ ይላል።

ይቆየን

__

በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena 
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ

ብአዴናዊነት (ከበሃይለ ምኒሌክ) 

ከበሃይሉ ምኒልክ

ስለ ብአዴን ታሪካዊ ዳራ መናገር ማንበብና መጻፍ ለሚችልና ሚዲያ ለሚከታተል ሰው ማደናቆር ይመስለኛል፡፡ የብአዴን አባላት የነበሩና ሌሎች ጸሐፊዎች እንደነገሩን ኢህዴን    መርህና ስትራቴጅ የለሹ ኢህአፓ በደረግና በወያኔ ሲዳከም ማምለጫ ያጡ ጥቂት ሰዎች የወያኔ መሪዎችን ርዕዮተዓለም ተቀብለው ያቋቋሙት ድርጅት ነው፡፡ ምንም እንኳ አገራዊ ፓርቲ ቢመስልም የድርጅቱ አመራሮች ከወያኔ በላቀ ደረጃ ለአማራ የነበራቸው ጥላቻ ከፍተኛ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የደርግን መንግሰት በመጣል ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ስማቸውን ወደ ብአዴን ቀይረው የፈጸሟቸው ድርጌቶችም ለአማራ ህዝብ ያላቸው ጥላቻ ጥልቅ እንደሆነ ተመልክተናል፡፡እዚህ ላይ ላነሳው የሚገባ አንድ ጉዳይ አለ፡፡ አንዳንድ የኢሕዴን መካከለኛ አመራር የነበሩ ሰዎች የህወሐትን አቅጣጫ ተረድተው ተጋድሎ ለማድረግ ጥረት አድርገው ነበር፡፡ ህወሐትና የኢህዴን የበላይ አመራሮች የእነዚህን ጥቂት ግለሰቦች ቆራጥነት ተረድተው ወጥመድ በማጥመድ በእንጭጩ አስቀሯቸው እንጂ፡፡ 

እንደሚታወቀው የአማራ ክልል ከተዋቀረ በኋላ ከላይኛው ክልላዊ መዋቅር እስከታችኛው የቀበሌ አስተዳደር ያሉትን ፖለቲካዊና አስተዳደራዊ መዋቅሮችን ቦታ የሚሸፍን ካድሬዎችን መመልመል፤ ማሰልጠንና መመደብ የመጀመሪያ ተግባር ነበር፡፡ በየደረጃው የተመደቡ ካድሬዎች የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ማለፍ ያልቻሉ ወይም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መጨረስ የተሳናቸው፤ የመጀመሪያ ደረጃ መምህራን፤ በተለያዩ የመንግስት መዋቅር ውስጥ የሚሰሩ አንዳንድ ሰራተኞች፤ ሰው ገድለው በደርግ ዘመን በወንጀል ይፈለጉ የነበሩ ናቸው፡፡ የእነዚህ ሰዎች ፖለቲካ ውስጥ እንዲገቡ ያደረጋቸው ዋና አላማ የአማራ ህዝብ ያሉበትን ውስብስብ ችግሮች በመታገል ለመፍታት ሳይሆን ስራ የሌላቸው ስራ ለማግኘት፤ ዝቅተኛ ስራ የነበራቸው የተሻለ ደመወዝ ለማግኘት ነበር፡፡ ይህንንም ለማሳካት ከወያኔ የሚወርድ ትዕዛዝ ያለምንም ማመንታት በመፈጸም ታማኝነታቸውን ማስመስከር የዕለት ስራቸው ነበር፡፡ ለህዝብና ለአገር ይጠቅማል አይጠቅምም የሚል ሀሳብ አንስቶ መሟገትና መታገል ፈጽሞ የሚታሰብ አለበረም፡፡ ብዙ ሰዎች የፖለቲካና የብሄር ንቃተ-ህሊና (political and ethnic consciousness) ስለሌላቸው ነው ብለው ይሟገታሉ፡፡ በእርግጥ አብዛኛዎቹ ብአዴንን የተቀላቀሉ ሰዎች የትምህርት አቅማቸው የደከመና ስለ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ከሚሰጣቸው ስልጠና ውጭ የማያውቁ ደናቁርት ናቸው፡፡ ከተወሰኑ የኢህአዴግ አገዛዝ ዘመናት በኋላ ወደ መካከለኛና ከፍተኛ የመንግስት መዋቅር የመጡ የማስተርስና PhD ድግሪ ያላቸውም ሰዎች የፖለቲካና የብሄር ንቃተ-ህሊና (political and ethnic consciousness) አላቸው ለማለት አያስደፍርም፡፡ በአንዳንድ አጋጣሚዎች ተገናኝተን ስንወያይ በመንግስት ወይም በፓርቲ ሚዲያዎች የሚነዛው ፕሮፖጋንዳ እውነት ነው ብለው የሚከራከሩ ናቸው፡፡ ኢፍትህአዊ የሀብት ስርጭት፤የአማራ ህዝብ መፈናቀልና ሞት አይታያቸውም፡፡ በጣት የሚቆጥሩ ሰዎች  የኢህአዴግ ጸረ-አማራነትና የስርዓቱን ኢፍትአዊነት ተረድተው ለመታገል የሞከሩ ቢኖሩም እንኳ በግምገማና በሴራዎች በራሱ በብአዴን መዋቅርና በደህንት አካላት ከድርጅቱ እንዲባረሩ ተደርገዋል ወይም ተገድለዋል፡፡  

በአጠቃላይ  የብአዴን አባላት ስናዳራዊ ካድሬዎች ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ እንደ ፕሮፌሰር ምንዳርያለው ዘውዴ  አባባል ስናዳራዊ ካድሬ ማለት “ነፍሱን ለከርሱ፤ ህሊናውን ለኪሱ፤ ነጻነቱን ለእለት ጉርሱ የሸጠ ኑባሬ ማለት ነው፡፡” በሌላ መልኩ ብአዴናዊነት ማለት ባንዳነት ማለት ነው፡፡ ባንዳ ወይም ባንዳነት የሚለውን ቃል  የተለያዩ ስዎች የተለያየ ትርጓሜ ሰጥተውታል፡፡ ብዙ ጸኃፊዎች ባንዳነት ማለት ወገኑንና ሀገሩን በመክዳት ከጣሊያን ጋር የወገነ ከሀዲ ማለት ነው ብለው ተርጉመውታል፡፡  የፕሮፌሰር ምንዳርያለው ዘውዴ  ትርጉም ግን  በፊት ከነበሩት ትርጓሚዎች የተለየ ነው፡፡ ፕሮፌሰሩ የባንዳነት ትርጉምን እንደሚከተለው ገልጾታል፡፡ 

 “ባንዳነት ማለት በጣም ትንሽ ጭንቅላት ላይ የተቆለለ ትልቅ ሆድ  ማለት ነው፡፡ በ ከመርፌ ቀዳዳ በጠበበችና ከዘንጋዳ ፍሬ በኮሰሰች ህሊና ውስጥ ለሞራል፤ ለእውነት፤ ለእውቀት፤ ለአገር ፍቅር ምንም ቦታ የሌለው ማለት ነው፡፡ ያለችውን የኮሰሰች ህሊና በሙሉ እንደ ተራራ የገዘፈውን ከርስ ለመሙላት ቀለብ ፍለጋ የሚማስን ማለት፡፡ ከርሱን ለመሙላት ብቃት ስሌለው በምድር ላይ ያለ ወንጀል በሙሉ ለመፈጸም ወደኋላ የማይል ማለት ነው፡፡” 

ከላይ የተገለጸው ትርጉም በትክክልም ብአዴናዊነትና ባንዳነት አንድ መሆናቸውን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ብአዴኖች የህዝቡን ንሮ በማኮስመን እነሱ የተሻለ ኑሮ ኖረዋል፡፡ ከቀበሌ አስተዳዳሪነት ጀምሮ እስከ ክልል መዋቅር የሰራ የብአዴን አባል ቢያንስ በየከተሞች ሁለትና ሶስት ቤት ያልገነባ የለም፡፡ የህዝብን ሀብት በመመዝበር ትልቅ ሀብት ያፈሩ ካድሬዎች የትየሌሌ ናቸው፡፡ አላማቸውን ለማሳካት የአማራን ህዝብ አንድነት ከማስጠበቅ ይልቅ በየጎጣቸው ተቧድነው የምዝበራ ኔትወርክ ሲዘረጉ ኖረዋል፡፡ ከዘህ በላይ የሞራል ልሽቀትና ባንዳነት ምን መገለጫ አለ፡፡

በ2010 ዓ.ም ከትህነግ የ27 አገዛዝ ወደ ኦሮሙማ አገዛዝ ስርዓት ለውጥ ወቅት የብአዴን መሪዎች ቀደም ሲል የአማራ ህዝብ ላይ የደረሰ ግፍ የለም ብለው ይከራከሩት የነበረውን አቋም ቀይረው በትህነግ አገዛዝ ወቅት ኢፍትአዊ የልማት ስርጭትና ኢድሞክራሲያዊነት ተስፋፍቶ እንደነበር ይህ አካሄድ ከአሁን በኋላ እንደማይደገም ደመቀ መኮንን ወይም አምስት ብሩና ሌሎችም ብአዴናዊያን በየመድረኩ ሲደሰኩሩ ብዙዎች ተስፋ አድርገው ነበር፡፡ እነዚህ ሰዎች አገልጋይነታቸውን ወይም ባንዳነታቸውን ትተው ለአማራ ህዝብ ጥቅም ሊቆሙ ነው የሚለው መወያያ ነበር፡፡ ብዙዎች የብአዴን ንስሐ መግባት እውነት መስሏቸው ነበር፡፡ ነገር ግን የብአዴን ለአማራ ህዝብ ጥቅም እቆማለሁ የሚለው ቃል ሳይውል ሳይድር ወሬ ሆኖ መቅረቱን ከብዙ ክስተቶች መረዳት አብዛኛው የአማራ ህዝብ መረዳት እንኳን አልቻለም፡፡ በየክልሎች በተለይ በኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የአማራን ብሄር መሰረት ያደረገ መፈናቀልና ግድያ ሲፈጸም በሽግግር  ወቅት የሚከሰት ክስተት ነው ብለው ብአዴኖችም ሆነ ሌሎች ተስፈኞች ሲያስተባብሉ ቆይተዋል፡፡ የኮሌኔል አብይ መንግስት አማራ ላይ ትኩረት ያደረገ ግድያና ማፈናቀል ሆን ብሎ እያስፈጸመ መሆንን ሳይረዱ፡፡ ለነገሩ ብአዴን የፖለቲካል ታክቲክና ስትራቴጂ የሚባል ጽንሰ-ሀሳብ የማይረዳ ግኡዛን ስብስብ ነው፡፡ ቢረዳስ የአማራ ህዝብ ስቃይ ምኑ ነው፡፡ የእያንዳንዱ ካድሬ የዛሬ ንሮው ከተመቸው ከዚህ በላይ አላማ የለውም፡፡ ለነገሩማ የብአዴን ካድሬ ብቻ ሳይሆን ኮለኔል አብይ አህመድ “ኢትዮጵያ ኢትየጵያ” ሲል አብዛኛው የከተማ ህዝብ እውነት መስሎት ነበር፡፡ የፖለቲካ ታክቲክ መሆኑን አልተረዳውም፡፡ በጸረ-ኢትዮጵያዊነትና በጸረ አማራ እሳቤ ያደገ ሰው መልካም መሪና ለአገር አሳቢ አይሆንም ብሎ የገመተ የለም፡፡ 

በመጀመሪያዎቹ አመታት የተከሰቱ ቀውሶች የኮለኔሉ አስተዳደር ስላልጠና ነው ሲጠነክር የታዩ ችግሮች ሙሉ በሙሉ ይፈታሉ የሚሉ ብአዴናውያን የትየሌሌ ነበሩ፡፡ ይሁንና ችግሮች እየተፈቱ ከመሄድ ይልቅ እየተወሳሰቡ ሄደዋል፡፡ በተለይ ባለፉት ጥቂት አመታት በአማራ ህዝብ ላይ የተፈጸሙ ድርጊቶች ዘግናኝ ናቸው፡፡ከተለያዩ የአማራ ክልል ቦተዎች ለህክምና፤ ለንግድና ለሌሎችም ማህበራዊ ጉዳዮች ወደ አዲስ አበባ የሚሄዱ ሰዎች ወደ አገራቸው ርዕስ ከተማ አትገቡም ተብለው ተከልክለዋል፡፡ ለብዙ ዘመናት ያፈራቸው ንብረቶች በታጠቀ ሃይል ዘረፋ ተፈጽሞበታል፡፡ በአዲስ አበባ ዙሪያ ላቡን አንጠፍጥፎ የሰራውን ቤት በማፍረስ ንበረቱ ተዘርፏል፡፡ በሚለዮን የሚቆጠረው አማራ ለብዙ አመታት ይኖረባቸው ከነበሩ የኦሮሚያና ቤኒሻንጉል ቦታዎች ተፈናቅሎ በድንኳን ንሮውን እየመራ ይገኛል፡፡ ይህ ሁሉ ግፍ ሲፈጸም ብአዴኖች የተለመደውን አገልጋይነታቸውንና ከህዝብ ይልቅ ለከርሳቸው ቅድሚያ ሰጥተዋል፡፡ 

ሰሞኑን ባወጧቸው አንዳንድ መግለጫዎች ብአዴናውያን ሊያመሩ ነው የሚል አንዳንድ ሞኞች ሲታለሉ ከሶሻል ሚዲያው መረዳት ችያለሁ፡፡ ከርስን መሰረት ያደረገ የህሊናና- አቅመ ቢሶች ስብስብ እንዴትስ አንደነትን ፈጥሮ የህዝብን ብሶት ሊቀርፍ ይችላል፡፡ ፈሪ ቢሸፍት ከጓሮ አያልፍም እንደሚባለው ነው የብአዴን ነገር፡፡ ከየካቲት 21-22 ቀን 2015 ዓ.ም   የሁለቱ ብልግና ክንፎች 4 ኪሎስብሰባ ላይ እንደ ነበሩ ተባራሪ ወሬዎችን ስንሰማ እውነትም አነዚህ ሰዎች መረዋል ብለህ ስታሰብ በልማትና በመልካም አስተዳደር ላይ አብረን ልንሰራ ተስማምተናል የሚል መግለጫ ሲሰማ ምን ሊባል ይችላል፡፡ ስናዳራዊነት የሚለው የምንዳርያለው ትንታኔ የብአዴንን ባህሪ በትክክል የሚገልጽ ነው፡፡ መግለጫው ለኮለኔል አብይ ኦሮሙማ መንግስት የብአዴንን አገልጋይነትና ታማኝነት በትክክል ያሳየ ነው፡፡ በሌላ አነጋገር የተሸናፊነት ስነ-ልቦና ያጎለበቱ በመሆናቸው ጥያቄ ባነሱ በማግስቱ ወደነበሩበት አቋም ይመለሳሉ፡፡ ከዝንብ እንዴት ማር መጠበቅ ራስን ማታለል ነው፡፡ እናም የአማራ ህዝብ ሆይ ብአዴንን እንደራስህ አካል አትቁጠረው፤ የራስህ ተወካይ አይደለም፤ ይልቁንስ ሰቆቃህ የተራዘመ እንዲሆን እየሰራ ያለ ስብስብ ነው፡፡ የህዝብ ግፍ አንገፍግፏቸው ለመደራጀትና ትግል ለማድረግ የሚፍጨረጨረውን ፋኖ ማሳደድ እንጂ የአማራ ህዝብ ጠላቶችን ለመታገል አይደለም ብአዴን የተፈጠረው፡፡ስለሆነም አማራ ከመጥፋት ለመታደግ ብአዴንን መታገል የመጀመሪያ አማራጭ ሊሆን ይገባል፡፡ 

__

በነጻ አስተያየት መድረክ የሚቀርቡ ሃሳቦች የጸሃፊውን እንጂ የግድ የቦርከናን ድረገጽ ሃሳብ ላያንጸባርቁ ይችላሉ፡፡ በዚህ ድረ ገጽ ላይ መጣጥፍ ለማውጣት ከፈለጉ ጽሁፍዎትን በሚከተለው አድራሻ በኢሜይል ይላኩልን info@borkena.com  

የቴሌግራም ቻናላችን ፡ t.me/borkena 
ትዊተር ፡ @zborkena
ፌስቡክ ፡ Borkena 
የቦርከና ቻናልን ስብስክራይብ ለማድረግ እዚህ ይጫኑ