spot_img
Wednesday, March 22, 2023
Homeዜናመታወቂያ የሌላቸው ነዋሪዎች እየመረጡ ነው

መታወቂያ የሌላቸው ነዋሪዎች እየመረጡ ነው

- Advertisement -

ወረዳ 20 ምርጫ ጣቢያ መታወቂያና የምርጫ ካርድ የሌላቸው ነዋሪዎች እየመረጡ ነው ተብሏል፡፡ ነዋሪዎች በዚህ አካባቢ ነዋሪ ከሆኑ ስድስት ወር ሆኗቸዋል በሚል ያለ ቀበሌ መታወቂያ እየመረጡ እንደሆነ ተገልጾአል፡፡ ንፋስ ስልክ ላፍቶ 5ና 8 ምርጫ ጣቢያ ላይ መታወቂያና የምርጫ ካርድ ያልያዙ ነዋሪዎች እየመረጡ እንደሆነ የአካባቢው የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩ የሆነው አቶ እስክንድር ጥላሁን ገልጾአል፡፡ በዚሁ ምርጫ ጣቢያ ፖሊስ ምርጫ ጣቢያው ውስጥ እየገባ መረጃ እየወሰደ እንደሆነ ተገልጾአል፡፡ ‹‹ፖሊስ ህግ ከማስከበር ውጭ ምርጫ ጣቢያ ውስጥ ሊገባ አይችልም፡፡ መታወቂያ ስጠይቀው ግን ያሳየኝ የፖሊስ መታወቂያ ነው፡፡ ትክክል እንዳልሆነ ስንነግራቸው ሊሰሙን አልቻሉም፡፡›› ሲሉ ተዘዋዋሪ ታዛቢው ገልጸዋል፡፡

በዚሁ ወረዳ በሌላ ምርጫ ጣቢያ ላይ የተመደቡ ታዛቢም ብዙ መታወቂያችን ጠፍቶብናል ከሚሉት በተጨማሪ መታወቂያ እንደሌላቸው የሚያምኑ ሰዎች እየመረጡ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹እኔ መታወቂያ የሌላቸው መምረጥ እንደሌለባቸው ስከራከር በብሎክ ነው የተሰጠን፡፡ መታወቂያ እንደሌለን እያወቁ በብሎክ ከፍለው ምርጫ ካርድ ሰጥተውናል፡፡ ስለሆነም ቀድመውም ያውቁታል›› በሚል መምረጥ እንዳለባቸው ገልጸውልኛል ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ ወረዳ 14 ምርጫ ጣቢያ 9 አንድ ግለሰብ ምርጫ ጣቢያው ውስጥ በመግባት ‹‹ንብን ምረጡ›› እያለ መራጩን ሲያስገድድ ተደርሶበታል ተብሏል፡፡

ምንጭ -ነገረ ኢትዮጵያ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,440FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here