spot_img
Sunday, September 24, 2023
Homeስፓርትፕሪሚየር ሊግ ፡ ቻምፒዮኖቹ በአሸናፊነታቸው ቀጥለዋል

ፕሪሚየር ሊግ ፡ ቻምፒዮኖቹ በአሸናፊነታቸው ቀጥለዋል

advertisement

May 26, 2015
አብርሃም ገ/ማርያም
ምንጭ ሶከር ኢትዮጵያ

የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 25ኛ ሳምንት ቅዱስ ጊዮርጊስ ድል ሲቀናው አዳማ ከነማ ነጥብ ጥሏል፡፡

3ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አዳማ ከነማ ወደ ጎንደር ተጉዞ ከዳሽን ቢራ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 0-0 በሆነ አቻ ውጤት ፈፅሟል፡፡ አዳማ ከነማ የአቻ ውጤቱን ተከትሎ በ41 ነጥቦች 2ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡

አዲስ አበባ ስታድየም ላይ አስቀድሞ ቻምፒዮን መሆኑን ያረጋገጠው ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ብሄራዊ ሊግ መውረዱን ያረጋገጠው ወልድያን አስተናግዶ 4-1 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል፡፡ በጨዋታው መጀመርያም ቅዱስ ጊዮርጊስ ቻምፒዮንነቱን ማረጋገጡን ተከትሎ ወልድያዎች በግራ እና ቀኝ በመቆም ፈረሰኞቹን በክብር አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

በጨዋው ግብ በማስቆጠር ቅድሚያውን የያዙት ወልድያዎች ሲሆኑ ማይክ ሰርጂ በ45ኛው ደቂቃ ከፍፁም ቅጣት ምት ክልል ውጪ ግሩም ግብ አስቆጥሯል፡፡

በሁለተኛው አጋማሽ ፈረሰኞቹ ፍፁም የጨዋታ ብልጫ ያሳዩ ሲሆን አራቱንም ግቦች ያስቆጠሩት በዚሁ የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ነው፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስን ግቦች ከመረብ ያሳረፉት ፍፁም ገብረማርያም (2) ፣ ምንያህል ተሾመ እና አዳነ ግርማ ናቸው፡፡

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,682FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here