spot_img
Wednesday, November 29, 2023
Homeየዓለም ዜናኢጣሊያ፤ ከ 5000 በላይ ስደተኞች ከመስመጥ ተረፉ

ኢጣሊያ፤ ከ 5000 በላይ ስደተኞች ከመስመጥ ተረፉ

advertisement

የአውሮፓ ህብረት የድንበር ጠባቂ ድርጅት በምህፃሩ ፍሮንቴክስ ዛሬ እንዳስታወቀው፤ ከዓርብ ዕለት አንስቶ ከ5000 በላይ የሜዲትራንያን ባህር ስደተኞችን ለማዳን ተችሏል። ከነዚህም ውስጥ አብዛኞቹ ከሊቢያ በ25 ጀልባዎች የተጓዙ ስደተኞች ናቸው። የጎርጎሪዮሳዊው አዲስ ዓመት ከገባ ከጥር ወር አንስቶ ብቻ ከ45 000 የሚበልጡ ሕገ ወጥ ስደተኞች ኢጣሊያ ገብተዋል። እንደ ዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት መረጃ ከሆነ ደግሞ 1,770 የሚሆኑ ወንዶች፣ ሴቶች እና ህፃናት በአደገኛው የባህር ጉዞ ሕይወታቸውን አጥተዋል። የአውሮፓ ኮሚሽን ቁጥራቸው ከ40 000 በላይ የሆኑ ከሶርያ እና ኤርትራ በኢጣሊያ እና በግሪክ በኩል አውሮፓ የገቡትን ስደተኞች አባል ሃገራቱ እንዲቀበሉ ባለፈው ረቡዕ ጠይቋል።

ምንጭ – የጀርመን ድምጽ ራዲዮ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here