advertisement
የቀድሞው የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስተር ዶናልድ ራምስፊልድ ጆርጂ ቡሽ የወሰዱት በኢራቅ ላይ “ዲሞክራሲን“ የመጫን ሙከራ ስህተት ነበር በማለት ትችት እንዳሰሉ የሩሲያው የዜና ማሰራጫ አር ቲ ዘግቧል።
በተወሰደው ርምጃ ምክንያት የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃልኪዳን (NATO) ስለተዳከመ “ዘመናዊ እና አዳዲስ” ሲሉ የገለጹትን የሴኪዮሪት ስጋት አንድ ለማለት አልቻለም ባይ ናቸው። ዶናልድ ራምስፊልድ ራሳቸው ኢራቅ ዱቄት የሆነችበት አሜሪካ መራሽ ጦርነት ሲካሄድ በመከላከያ ሚኒስትርነት የሰሩ ብቻ ሳይሆን የቡሽ ፓሊሲ ቀንደኛ ደጋፊ እንደነበሩ ነው የሚታወቁት።