spot_img
Saturday, September 30, 2023
Homeአበይት ዜናከሰዓታት በፊት በጎንደር በተነሳ አመጽ ቢያንስ አንድ ሰው ተገድሏል ፤ ጎንደር ቀውጢ...

ከሰዓታት በፊት በጎንደር በተነሳ አመጽ ቢያንስ አንድ ሰው ተገድሏል ፤ ጎንደር ቀውጢ የጦርነት ቀጠና እንደመሰለች ይነገራል

advertisement

ሐምሌ 29 ፤ 2008

በማህበራዊ ድረ ገጽ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ዛሬ በጎንደር ድንተገኛ ተቃውሞ ተነስቷል። ቢያንስ አምስት ሺህ የሚገመቱ ሰልፈኖች የጎንደር ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፊት ለፊት በመሆን ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ቆይተዋል።

ሰልፉ ፍርድ ቤት የሆነነት ምክንያት የወልቃይት ጥያዊ ኮሚቴ አባል እና አመራር የነበሩት ኮሎሌል ዘውዱ ፍርድ ቤት ቀርበዋል የሚል ዜና በጎንደር ከተሰማ በኋላ ነው። ኮሎኔሉን አሁን ከሚገኝበት የጎንደር አንገርብ እስር ቤት ወደ ማዕከላዊ ለማዛወር የጎንደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች 4 ለ 1 የሆነ ድምጽ እንዳሳለፉ የተሰማው ባለፈው ሳምንት ነው። ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እስካሁን በይፋ ክስ ያልተመሰረተበት ሲሆን ፤ ክስ ቢመሰረትበት እንኳን ጉዳዮ በጎንደር ፍርድ ቤት ደረጃ ሊታይ የሚችል ሲሆን ወደ ማዕከላዊ ማዛወሩ አግባብነት ያለው አካሄድ አይደለም በማለት የህግ ሰዎች አስተያየት ይሰጣሉ።

የኢሳት ሰበር ዜና ዘገባ ቪዲዮ እንደሚያመለክተው መጀመሪያ ሰልፈኞቹ ላይ አስለቃሽ ጭስ የተተኮሰ ቢሆንም ፤ ወዲያውኑ በሰልፈኞቹ ላይ የጥይት ተኩስ ሩምታ ተከፍቷል።

በማህበራዊ ድረ ገጽ የተለቀቀ ፎቶ እንደሚያሳየው አንድ ወጣት እጂግ በአሰቃቂ ሁኔታ እንደተገደለ ያሳያል። ሆኖም የጎንደር ወጣት ባለማፈግፈግ ትግሉ መንፈሰ ጠንካራነት የተሞላበት እንደሆነ አስመስክሯል።

ጎንደር ሙሉ ለሙሉ ወደ ጦርነት ቀጣና እንደተቀየረች ባለፉት ሰላሳ ደቂቃዎች በማህበራዊ ድረገጽ የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ፤ ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የጎንደር ወጣት ተገድሏል።

Gondar protest now

ፎቶ ምንጭ : ሶሻል ሚዲያ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,705FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here