spot_img
Monday, May 29, 2023
Homeአበይት ዜናበባህር ዳር በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች ጉዳት ከደረሰባቸው በኋላ ፤ ዛሬም ሕዝባዊ አመጹ...

በባህር ዳር በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰልፈኞች ጉዳት ከደረሰባቸው በኋላ ፤ ዛሬም ሕዝባዊ አመጹ ቀጥሎ ውሏል

- Advertisement -

ነሃሴ 1 2008 ዓ ም

Bahir Dar Protest

ትላንት በባህር ዳር እየተደረገ በነበረው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ አጋዚ በመባል የሚታወቁት የህወሓት ታማኝ ወታደሮች በሰላማዊ ሰዎች ላይ በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ ሰላሳ ሰባት ሰዎች ሲገደሉ ፤ ሃምሳ ያህል ቆስለዋል።

ሆኖም ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል። ትላንት ለተገደሉት የከተማዋ ነዋሪዎች የቀብር ስነ ስርዓት ከተደረገ በኋላ ለቀስተኛው ወደ ህዝባዊ እምቢተኝነት ተመልሶ ድምጹን ሲያሰማ ውሏል።

ሱቆች እና የመንግስት መስሪያቤቶ የተዘጉ ሲሆን፤ የስልክ እና ኢንተርኔት አገልግሎትም እንደተቋረጠ ለማወቅ ተችሏል። ዛሬ በተደረገውም ሰልፍ ላይ የመንግስት ታማኝ ወታደሮች የተኩስ ሩምታ የከፈቱ ሲሆን፤ የደረሰውን የጉዳት መጠን እንካሁን ማረጋገጥ አልተቻለም።

በተመሳሳይ ሁኔታ በባሌ ፤ በሃረር ፤ በአርሲ ፤ በወለጋ እና ከፊል ሸዋ የኢትዮጵያ ክፍሎች የኦሮሚኛ ቋንቋ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን ከቅዳሜ ጀምሮ ብቻ ባደረጉት ሰላማዊ ሰልፍ ከአርባ በላይ የሚገመቱ ሰላማዊ ዜጎች እንደተገደሉ ታውቋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ በባህር ዳር እና ጎንደር ፤ በደቡብ ምስራቅ እና ደቡብ ምዕራብ እንዲሁም በመካከለኛው የኢትዮጵያ ክፍል በሃረር፤ በባሌ ፤ በአርሲ እና ወለጋ የተነሱት የተቃውሞ ሰልፎች የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ የግፍ አገዛዝ እንዲያከትም ጠይቀዋል።

በውጭ የሚገኙ የተለያዮ ሚዲያዎች ህዝባዊ ተቃውሞን የዘገቡ ቢሆንም የብዙዎቹ ዘገባ የሟቾች የቁጥር መዛባት እና ሌሎችም መሰረታዊ ችግሮች ያሉበት እንደሆነ ይስተዋላል። እንደፋይናንሺያል ታይምስ ያሉት ለምሳሌ በዘገባው ውስጥ “የአፍሪካ ምርጥ ምርታማ ኢኮኖሚ የፖለቲካ አለመረጋጋት አደጋ ተደቅኖበታል” ሲል ዘግቧል።

በእንደ እውነቱ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ባለፉት 25 ዓመታት ትርጉባ ባለው “ፖለቲካዊ መረጋጋት” ኖሯል ለማለት አይቻልም።

_____
ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ። ካነበቡ በኋላ ሼር ማድረግ አይርሱ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,864FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here