ደጄኔ ላቀው
ነሃሴ 11 2008 ዓ ም
ዘርህን፤ ሃገርህንና ማንነትህን ከጥፋት ለመጠበቅ ላለፉት ሳምንታት ያሳየሃቸዉን የጀግንነት የብልህነትና የሃገር ወዳድነት እርምጃ በጽሞና መላው አለም አይቷል። ኢትዮጵያም የተደፋ አንገቷን ቀና አድርጋ አይታለች፤ ተደስታለች፤ በርግጥም ልጆቸ አሉ ብላለች። በቅርቡም እነሳለሁ፤ እንደገናም አብባለሁ ብላለች።
እርምጃህም የትግራይ ወያኔ የአማራዉን ህዝብ፤ ታሪክ፤ ባህልና ያስተሳሰብ ሃያልነት እንደማያዉቀውና አማራው ታጋሽ ህዝብ እንደሆነ፤ ግን ምንጊዜም የኢትዮጵያ መካች፣ ደጀንና አለኝታ ህዝብ መሆኑን ነው ። ትግስት ፍርሃት ሳይሆን ብልህነት፤አስተዋይነት ነው፤ የበሰለ የባህል ነጸብራቅ ዉጤት ነው ። የአማራዉ ህዝብ ላለፉት 25 አመታት የትግራይ ወያኔ የወሰነበትን የጥፋት አዋጅና ተግባር ለመቋቋም ያሳየዉም ይህንን ታልቅ ባህሉን ነው ። ይህ እርምጃችሁ የምእራባዉያን ሃገሮች የኢትዮጵያን ህዝብ ከራሱ ዉስጥ በበቀሉ ግን እነሱን በማገልገል፤ የኢትዮጵያን ህዝብ በመበቀልና በባንዳነት ባህላቸው የዉጭ ሃይሎችን ለማስደስትና ፈጥኖ ደራሽ ከምንም የማይቆጠር ሰራዊት ከድሃው ኢትዮጵያ ህዝብ በማቅረብ በተለያዩ የአፍሪካ በረሃወች እንዲሞቱና አሞራ እንዲበላቸው በማድረግ፤ በምትኩ በብዙ ሚሊዮን ዶላር የሚቆጠር ሃብት በማግኘት የራሳቸዉን የተንደላቀቀ ህይዎት ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚኖረው የትግራይ ወያኔ እስትንፋሱ የሚዘጋበት ና ከተቀደሰችና በታሪኳ ኩርህ የሆነች ሃገር ይህ እርኩስ ቡድን የሚጠፋበት ፈር ቀዳጅ እርምጃ ነው ።
የኢትዮጵያን ባንዲራ በመያዝ የትግራይ ወያኔ በየበረንዳው ያንጠለጠለዉን የለማኝ ድሪቶ ጨርቅ በመጣል ፤ ኢትዮጵዉያንን ሁሉ አንድ ነን ፤ ባንዴራችንም ይችዉ የጥንቷ፤ ወራሪወችን የምታንቀጠቀጠው፤ ተፈጥሮ እንኳን የሚያዉቃት በሰማይ ላይ የምትታየው አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ አርማችን፤ ሃይላችን ነች፤ እኛ የኢትዮጵያ ልጆች ነን፤ ወልቃይት ጠገዴ የአማራው ታሪካዊ ቦታው ነው፤ ተከዜ ወንዝ፤ የጎንደርና የትግራይ መካለያ ተፈጥሮአዊ ደንበር ነው፤ ኦሮሞ ወንድማችን ነው፤ የትግራይ ወያኔ ኦሮሞዉን መግደል ያቁም፤ ጋምቤላዉ ወንድማችን ነው፤ ጋምበላዉን መግደል ያቁም ብላችሁ:ጀግናው አጼ ተዎድሮስ በትግራዩ ወሮ በላ ስሁል የሚባል አወናባጅ ምክንያት የፈረሰችዉን ኢትዮፕያን እንደገና እንደገነባት ሁሉ እናንተም በሌባው የትግራይ ወያኔ የፈራረሰችዉን ውድ ሃገራችን ኢትዮጵያ ከሞት አደጋ የሚያድናትን የጀግነት ጥሪና ተጋድሎ ፈጸማችሁ። ይህ ጀግነታችሁ እነሆ ወደተለያዩ የኦሮሞ ክልሎች፤ ባጠቃላይ በመላዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ በመባዛት ጀግናዉን የአማራ፤ የኦሮሞ እና የደቡብ እትዮጵያን ህዝብ አነሳስቷል። የትግራይ ወያኔ ያጭበራባሪ ቡድን የዘራጋዉን የዝርፊያ መዋቅር በጣጥሳችኋል፤ ለኢትዮጵያና ለአለም ህዝብ አሳይታችኋል።
ከዚህ በኋል የትግራይ ወያኔ ማድረግ ያለበት የሚከተሉት ብቻ ናቸው
(1) ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ወልቃይት ጠገዴ ጠለምትን ወደጎንደር የወሎንም መሬት ወደወሎ የጎጃም መሬቶችን ወደጎጃም መመለስ ያንንም ዉሳኔ ለኢትዮጵያ ህዝብ ማሳወቅ፤ የአማራዉን ህዝብ ይቅርታ መጠየቅ፤ ወንጀላቸዉንም አምነው፤ የኢትዮጵያ ህዝብ የሚሰጠዉን ፍትሃዊ እርምጃ ለመቀበል መዘጋጀት
(2) ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ስልጣን መልቀቅና አስቸካይ የሆነ የሽግግር መንግስት እንዲቋቋም ሁኔታወችን ማመቻቸት፡ በዚህም ተግባር ዉስጥ የትግራይ ወያኔ ምንም አይነት አስተዋጾ እንዳያደርግ ማድረግ
(3) የኢትዮጵያ ሰራዊት ሃገሪቱን ከዉጭ አጥቂ ሃይል ለመከላከልና የኢትዮጵያን ህዝብ ለመጠበቅ እንጂ ድሃ ልጆቿን ለማፈን፤ ለመረሸን፤ ለመግደል አይደለም። ይህንንም በማወቅ መላው የኢትዮጵያ ሰራዊት አባል የሆነ ሁሉ፡ የጠበንጃዉ አፈሙዝ ወደ ወገኑ ድሃ ህዝብ ሳይሆን ሃገርን ወደሸጠዉና የንግድ ስራ በተሰማራው የትግራይ ወያኔ አባል፤ አመራርና የጦር ክፍል ሃላፊ ወደሆነው ነው። ይህ እርምጃችሁ የኢትዮጵያን ህዝብ የነጻነት ትግል ያፋጥነዋል፤ የህዝብ አጋርነታችሁንና ከታሪክ ተጠያቂነት ያድናችኋል። የሙሶሎኒ ተወካዮችን ካገለገሉት ባንዳ ባለስልጣኖች ይልቅ እነሱን ለመግደል የሞከሩት ቆራጥ የኢትዮጵያ ልጆች በኢትዮጵያ ታሪክ ዉስጥ ትልቅ ስፍራ ይዘው ይገኛሉ፤ እናተም ከነዚያ ጀግኖች አንዶቹ ለመሆንና በኢትዮጵያ ዘላለማዊ አንጸባራቂ ታሪክ መዝገብ ዉስጥ እንድትሆኑ የሚያስችህላችሁን ተግባር ፈጽሙ።
የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ከዉስጡ እንደመዥገር በቅለው ሃገርን ለማጥፋትና ህዝቧን በዉስጥ ባርነት በማፈን እጅግ ከፍተኛ በደልና የግፍ ወንጀል የሚፈጽሙትን የትግራይ ወሮበላ ቡድን ቀርቶ ዘመናዊ የሆነ የጦር መሳሪያ ዪዞ ፤ መርዝና ጋስ የተጠቀመን የዉጭ ወራሪን አንበርክኳል፤ ለዚያም ነው የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻና ኩሮ ህዝብ ሆነ የሚኖረው፡ ባርነት፤ ባንዳነት፤ ሃገርን ማፍረስ ሁልጊዜም የትግራይ ወያኔና መሰሎቹ ስራ ብቻ ነው፤ በዚህም ምክንያት ከኢትዮጵያ መሬት ላንዴና ለሁሌም ዪወገዳሉ። የዘረጉት የስርቆት ስርአትም ይበጣጠሳል፤ እንደ ጤዛም ዪጠፋሉ። ስልታችሁን ጥበባዊ በሆነ መንገድ በመቀያየር ትግላችሁን ማጠናከር፤ ወያኔን በያለበት መምታት፤ እንቅስቃሴውን መግታትና፤ አንድም ነገር እንዳያደርግ ማድረግ፤ ኑሮን ዱርቤቴ ብሎ የወጣን ህዝብ ማንም ሃይል ሊያስቆመው አይችልምና ። ነጸነት በነጻ የሚገኝ አለመሆኑን ከሁሉም በላይ የኢትዮጵያ ህዛብ ያወቀዋል፡ ያንን ነው ሁልጊዜ ማሰብና በተግባርም መፈጸም ።ይህ ሃገር በቀል የመሬት አረም ፤ የእንስሣ መዥገር፤ የሰው ትኋን ባጭር ጊዜ ዉስጥ ከኢትዮጵያ ተነቅሎ እንደሚጠፋ እርግጠኛ ነኝ።
ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ህዝብ ለዘላለም ይኑር!!