spot_img
Wednesday, June 7, 2023
Homeነፃ አስተያየትየኢትዮጵያ ቴሌቭዥን (ኢቢሲ) "ባጎረስኩ ተነከስኩ"

የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን (ኢቢሲ) “ባጎረስኩ ተነከስኩ”

- Advertisement -

Dimetrosድሜጥሮስ ብርቁ
ነሃሴ 29 2008

የወያኔ መንግስት ውሸት ከሚገኙባቸው ብዙ መንገዶች አንዱ ወያኔ የሚጨፍርበት የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን (አሁን ኢቢሲ) አንድ አማራጭ ነው። ሰሞኑን የኢቢሲን ዘገባ በፌስ ቡክ ስከታታል የኮንቴንት አቀራረቡ ለየት ያለ መስሎ ተሰማኝ።

ትንሽ የስነ ልቦና ጠበብትም ፈላልገው ምን አይነት አቀራረብ እና ኮንቴንት ተሻለ የአንባቢ ቁጥር ሊያመጣ ይችላል በሚለው ላይ ሳይሰሩ የቀሩ አይመስልም። ለምሳሌ “ስላልተረጋገጠ ወሬ” ውይይት የሚጋብዝ ፖስት ፖስተው ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ቀውስ ( ወያኔ ስንት ህዝብ የፈጀነት) በተወሰነ ደረጃ “ያልተረጋገጠ ወሬ” ከመስማት ጋር የተያያዘ እንደሆነ ሊያሳዮ ሞክረዋል! ለየት ያለም የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ መሆኑም ነው።

ዛሬ ደሞ እዛው ገጽ ላይ ሌላ ቪዲዮ ሳይ አንድ ህጻን ልጂ ለደለበ በሬ በእጁ የበቆሎ ቅጠል ነገር እያጎረሰ ፤ የደለበው በሬ የመጨረሻውን አፉ ላይ ካደረገ በኋሏ ህጻኑን ወግቶ መሬት ላይ ሲያስቀምጠው ያሳያል። ለቪዲዮው የተሰጠው ርዕስ “ባጎረስኩ እጄን ተነከስኩ” !

ባንድ በኩል ወቅት ሳይመርጥ መገልፈጥ የሚወድ ሰው ስላለ ያንን ኦዲየንስ በማበራከት እንደተለመደው ወጣቶች ኢትዮጵያን ሊያጠፋ ከተቃረበው የወያኔ ፖለቲካ ይልቅ ወደ ወደ ግዴለሽነቱ ለመውሰድ ያህል ነው። በሌላ በኩል ደሞ ልክ እንደዛ እንደበሬ እያጎረሱ የያዙት ካድሬ እና ኮካ በስነልቦና ወጋ ለማድረግም ይመስላል።
የወያኔ አዲስ የፕሮፖጋንዳ አቀራረብ የመልስ ምት ይፈልጋል፤ መሬት ላይ ያለው ትግል እንዳለ ሆኖ ፤ የማንቃት እና የማደራጀት ስራ እንዳለ ሆኖ የተቀናጀ የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አመላካች ይመስለኛል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ወያኔ ያሰማራቸውን እንደ ዳንኤል ብርሃነ ያሉትንም ሰዎች ወያኔ ለሚያጎርሳቸው የፖለቲካ “ከብቶች” መተው ያስፈልጋል። ሌላ ሰው አንስቶታል ይሄን ሃሳብ ትክክለኛ ይመስለኛል።
***

በሌላ ርዕስ የታምራት ላይኔን አዲስ ቃለ ምልልስ አዳመጥኩት። እንደብዙ ኢትዮጵያውያን ገና ሰውየውን ሳየው ደስ የማይል ስሜት ነው የተሰማኝ። እንደምንም ከፍቸ ያለውን ሳዳምጠው ፤ ምንም እንኳን እሱ ራሱ የወያኔ ፊትአውራሪ ሆኖ በአማራ ህዝብ ላይ ቅጥ ያጣ ጥላቻ ቢሰብክም ፤ በዚህኛው ኢንተርቪው ያነሳቸው ጥቂት ቁምነገሮች አሉ። ከማንም በላይ የወያኔ “የፖለቲካ ከብቶች” ፖከ፤ኮካ (whatever) ዲያዳምጧቸው የሚጠቀሙ ይመስለኛል። ለወያኔ ስልጣኑን ባያድኑለትም ፤ ቢያንስ ሃገር ምድር ሳይጨርስ ራሱን የሚያድንበትን መንገድ የሚጠቁሙ ይመስለኛል። “የኢትዮጵያ ህዝብ ቂመኛ አይደለም” ብሏቸዋል፤ ትክክል ነው። ይሄን ለመናገር ከሱ የተሻለ ሰው ያለ አይመስለኝም።

ቦርከና

ቦርከናን ላይክ ያድርጉ ፤ ሼር ያድርጉ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,879FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here