spot_img
Sunday, May 28, 2023
Homeዜናየደሴ የቤት ውስጥ ተቃውሞ

የደሴ የቤት ውስጥ ተቃውሞ

- Advertisement -

ነሃሴ 29 ፤ 2008 ዓ ም

ደሴ ገና ህወሓት ሲገባ ጀምሮ ደም ያፈሰሰባት ፤ ለረዝም ዘመን በተቀለደበት የምርጫ ጨዋታ እንኳን ከመጨረሻዎቹ ሁለት ምርጫዎች በስተቀር ገዥው ፖርቲ ብዙ ጊዜ የተሸነፈባት ከተማ ብትሆንም በቅርቡ በአማራ ክልል ከተቀጠለው ጸረ ወያኔ ትግል በዝምታ ተውጣ ብዙዎችን አስገርማ ነበር።

ምክንያቱን ለማጣራት የተደረጉ ሙከራዎች በሁለት አቅጣጫ ፍንጭ ሰጥተዋል። አንደኛው ደሴ ውስጥ ከነባሩ ይልቅ ከሌላ ቦታ የመጣ ሰው ስለሚበዛባት መፈራራት አለ የሚል ሲሆን ፤ ሌላኛው ማህበራዊ ተጽዕኖ የነበራቸው ወጣቶች ወይ ከተማዋል ለቀው ወደ ሌላ አካባቢ በመሄዳቸው እና የተቀሩትም በስራ እጦት ምክንያት የወያኔ ጎራ ስለተቀላቀሉ ነው የሚሉ መላምቶች ተሰጥተዋል።

እንደዚያም ሆኖ ትላንት ደሴ በቤት ውስጥ የመዋል አድማ ለማድረግ ሞክራለች፤ ተከፍተው የነበሩ የንግድ ቤቶች ቢኖሩም ሙሉ በሙሉ ከዥው ፖርቲ ጋር ቁርኝት የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ቁርኝት ያላቸው ወገኖች እንደነበሩ ከስፍራው የወጡ ምንጮች ያስረዳሉ።

የፌደራል ፖሊስ ( በፎቶ ላይ እንደሚታየው) በመንደር ውስጥ ወከባ እንደፈጠረም ታውቋል። በቀጣይነት ደሴ በአመጽ በመቀጠል ገዠው የህወሓት መንግስት በአማራ ክልል በንጹሃን ዜጎች ላይ ያደረገውን የጂምላ ግድያ እንደሚቃወም “አማራ ሪዚዝታንስ” በመባል ከሚታወቀው የፖለቲካ አመራር ቡድን ገጾች ለማወቅ ተችሏል።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,856FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here