spot_img
Sunday, September 24, 2023
Homeዜናበዋሽንግተን ግዙፍ ሰልፍ ተካሄደ

በዋሽንግተን ግዙፍ ሰልፍ ተካሄደ

advertisement

መስከረም 9 2009 ዓ.ም

ከዋሽንግተን ፤ ቨርጂኒያ ሜሪላንድን እና ከሌሎች የአሜሪካ ግዛቶችም የመጡ ኢትዮጵያውያን በዋሽንግተን ግዙፍ የተቃውሞ ሰልፍ አድርገዋል። በዋሽንግተን ሰዓት አቆጣጠር ጠዋት ዘጠኝ ሰዓት ላይ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የተጀመረው ወደ አሜሪካ ኮንግረንስም ሄዷል።

ምንም እንኳን መንቻካ ዝናብ ቢዘንብም ሰልፈኛው ሳይበተን የተቃውሞ ድምጹን ሲያሰማ ውሏል።

ሰልፈኞች በኢትዮጵያ የህወሓት መንግስት የሚያደርገውን ግድያ በመቃወም ፤ የአሜሪካ መንግስት ወያኔን መርዳቱን እንዲያቆም እና ይልቁንም በወያኔ እየተቀናበረ ያለውን የዘር ማጥፋት ዘመቻ እንዲያስቆም ጠይቀዋል።

ካለፈው ሃምሌ ወር ወደዚህ እንኳን ከ አንድ ሺህ በላይ የሚገመቱ ኢትዮጵያውያን በወያኔ ሰራዊት መገደላቸው ይታወሳል። ባለፉት ሶስት እና አራት ቀናት የግድያ ቀጠናውን ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ በመውሰድ በኮንሶ አንድን መንደር እንዳለ አረጋውያን እና እመጫት ሴት ጭምር በቤታቸው ውስጥ እያሉ ማንደዱን የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ካሰተላለፈው ዘገባ ለማወቅ ተችሏል።

በጎንደር ከሰው ህይወትም ባለፈ ፤ ቅዳሜ ገበያ በመባል የሚታወቀው ቦታ ሙሉ በሙሉ እንደወደመ ይታወሳል።

ዛሬ በዋሽንግተን ለሰልፍ የወጣው ሰው በ20 ሺዎች ተገምቷል።

የሽፋን ፎቶ : ልደት ሙለታ

ቦርከና

ካነበቡ በኋላ ያጋሩ ፤ ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ!

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,682FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here