spot_img
Wednesday, June 7, 2023
Homeአበይት ዜናበጎንደር ከተማ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ጎልታ ትታይ የነበረች ወጣት በህወሓት መንግስት ታጣቂዎች ታፈነች

በጎንደር ከተማ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ጎልታ ትታይ የነበረች ወጣት በህወሓት መንግስት ታጣቂዎች ታፈነች

- Advertisement -

መስከረም 9 2009 ዓ ም

nigist-yirga

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከአማራ ተጋድሎ ጋር የተያያዙ ዜናዎችን በመዘገብ የሚታወቀው ሙሉቀን ተስፋው እንደዘገበው በጎንደር ከተማ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ጎልታ ትታይ የነበረች ወጣት በህወሓት መንግስት ታፍና ወደ ማዕከላዊ እስር ቤት እንደተወሰደች ዘግቧል።

ስሟ ንግስት ይርጋ እንደሚባል የጠቆመው የሙሉቀን ዘገባ ፤ እድሜዋ ገና በሃያዎቹ መጀመሪያ ሲሆን የወያኔ መንግስት ታጣቂዎች ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን አፍኖ ለመውሰድ ወደ ጎንደር በመጡበት ወቅት በተፈጠረው ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ በመምራት እና በማስተባባር ባደረገችው ንቁ ተሳትፎ እንደምትታወቅም ጨምሮ ገልጿል።

ወጣት ንግስት ይርጋ ሃገሯን የምትወድ እና በህዝባዊ እምቢተኝነቱ ንቁ ተሳታፊ ከመሆኗ ሌላ ምንም ወንጀል የሌለባት ሲሆን ፤ ስለ “ጥልቀት ተሃድሶ” ሲያወራ የሰነበተው የወያኔ መንግስት በጎን እየወሰደ ያለው የእብሪት እርምጃ እየደገሰ ያለው ነገር ጠቋሚ እንደሆነ ያሳያል ሲሉ አስተያየታቸውን የሰጡ ሰዎች አሉ።

ቦርከና

ያጋሩ ፤ ቦርከናን በፌስ ቡክ ሼር ያድርጉ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,879FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here