spot_img
Monday, October 2, 2023
Homeዜናበሳውዲ አረቢያ አንድ ኢትዮጵያዊት የሞት ቅጣት ተፈጸመባት (ኢሳት )

በሳውዲ አረቢያ አንድ ኢትዮጵያዊት የሞት ቅጣት ተፈጸመባት (ኢሳት )

advertisement

ኢሳት
መስከረም 17 ፥ 2009

በቅርቡ በአንድ የሳውዲ አረቢያ ህጻን ላይ ግድያን ፈጽማለች ተብላ የጥፋተኝነት ውሳኔ የተላለፈባት ኢትዮጵያዊት ሰኞ በመቅላት ድርጊት የሞት ቅጣት እንደተፈጸመባት የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣናት ገለጹ።

በ20ዎቹ የእድሜ ክልል ውስጥ የምትገኘው ኢትዮጵያዊት ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኒታ የአሰሪዎቿን ታዳጊ ህጻን በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሏን የሳውዲ አረቢያ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
የአገሪቱ ፍ/ቤት በተከሳሿ ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔን ቢያስተላልፍም፣ ኢትዮጵያዊቷ ግድያውን በምን ምክንያት እንደፈጸመች የታወቀና የተገለጸ ነገር አለመኖሩን አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ ከሃገሪቱ ዘግቧል።

የሳውዲ አረቢያ የሃገር ውስጥ ሚኒስቴር በበኩሉ ኢትዮጵያዊቷ በከፍተኛ ፍርድ ቤት ሳይቀር ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ የመቅላቱ ድርጊት እንደተፈጸመባት ለመገናኛ ብዙሃን አስታውቀዋል።
ሳውዲ አረቢያ ሰኞ በኢትዮጵያዊቷ ላይ የፈጸመችውን የመቅላት ድርጊት ጨምሮ በተያዘው የፈረንጆች አመት ብቻ 124 ሰዎችን በተመሳሳይ ድርጊት መግደሏን አዣንስ ፍራስን ፕሬስ በዘገባው አስፍሯል።

በ10ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረቢያ በአብዛኛው በቤት ሰራተኝነትና በሌሎች ስራዎች ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,723FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here