spot_img
Tuesday, October 3, 2023
Homeዜናአርበኛ አበራ ጎባው በታች አርማጭሆ ተሰዋ

አርበኛ አበራ ጎባው በታች አርማጭሆ ተሰዋ

advertisement

ጥቅምት 3 2009 ዓ ም

አስራ አምስት ያህል ወታደሮችን ገድሎ ተሰውቷል የተባለው ጀግናው አበራ ጎባው
አስራ አምስት ያህል ወታደሮችን ገድሎ ተሰውቷል የተባለው ጀግናው አበራ ጎባው

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተክትሎ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በተለያዮ አካባቢዎች በተለይም በጎንደር እና በጎጃም ጦርነት የሚመስል ነገር እንዳፋፋመ ይታወቃል። ዓላማው ትጥቅ ማስፈታት እና የህልውና እና የማንነት ጥያቄ ያነሳውን አማራውን ወደ ፍጹም ባርነት የመቀየር ምኞት እንደሆነ የሚናገሩ አሉ።

ትላንት በማህበራዊ ሚዲያ በወጣ መረጃ በሰሜን ጎንደር ታች አርማጭሆ ዶጋው አካባቢም 5ኛ ተወርዋሪ የሚባለው የወያኔ ጦር ጦርነት ከፍቶ እንደነበር ታውቋል። በአካባቢው ከነበሩ ኢትዮጵያውያን አርበኞች አበራ ጎባው በመባል የሚታወቀው ጀግና አስራ አምስት የሚደርሱ የህወሓትን ወታደሮች ገድሎ ተሰውቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የጀግናው ኮሎኔል ደመቀ የምርመራ ፋይሎች እንደተዘጉ ጠበቃው መከተ ካሳሁን ከኢሳት ጋር ካደረጉት ቃለ ምልልስ ማወቅ ተችሏል። የተከፈቱት የምርመራ ፋይሎች ነብስ በማጥፋት እና በሽብርተኛነት በሚል ሲሆን የመጀመሪያው ፋይል ላይ ማስረጃ ማቅረብ ባለመቻሉ ተዘግቶ ለአቃቢ ህግ ተላልፏል። አቃቢ ህግ መረጃው እንደተላከት በ15 ቀናት ውስጥ ክስ መመስረት የነበረበት ሲሆን ፤ ያንን አላደረገም። የሽብርተኛነት ፋይሉ በሰሜን ጎንደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት መታየት የማይችል ነው በማለት እሱም ተዘግቷል።

—————————
ቦርከናን ላይክ ማድረግ አይርሱ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,723FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here