spot_img
Saturday, September 30, 2023
Homeዜናበአርማጭሆ ሳንጃ ወረዳ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ...

በአርማጭሆ ሳንጃ ወረዳ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ቀጥሏል (ኢሳት)

advertisement

ኢሳት (ኅዳር 14 ፥ 2009)

ሃምሌ 5 ፥ 2008 ጎንደር ከተማ የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ በሰሜን ኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠሉ እየተሰማ ሲሆን፣ በአርማጭሆ ሳንጃ ወረዳ ረቡዕ ዕለት አንድ መኪና በተወሰደበት ዕርምጃ መቃጠሉንም የአይን ዕማኞች ገልጸዋል።

በተበታተነ መልኩ ሲካሄዱ የነበሩ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች በአንድ ዕዝ በተቀናጀ መንገድ እንዲካሄድ ስምምነት ላይ መደረሱንም፣ በበረሃ የሚገኙት ታጣቂዎች ከኢሳት ጋር ባካሄዱት ቃለ-ምልልስ ገልጸዋል።

በሰሜን ኢትዮጵያ በአማራ ክልል በተለይም በሰሜን ጎንደር በየአካባቢው ተደራጅተው በጎበዝ አለቆች ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ሃይሎች በጋራና በአንድ ዕዝ ስር ለመታገል መወሰናቸውንና በቤተክርስቲያን ተገኝተው ቃል መሃላ መፈጸማቸውን ለኢሳት ገልጸዋል።

ሰኞ ህዳር 12 ፥ 2009 ዓም በአንድነት በጋራ ዕዝ ስር ለመታገል የወሰኑት በቁጥር 450 የሚቆጠሩት ታጣቂዎች ኢትዮጵያ ነጻነቷን እስከምታገኝ እንደሚታገሉ ገልጸዋል።
ሰሚን ጎንደር ኢትዮጵያና ደቡብ ጎንደር ቴዎድሮስ በሚል በሁለት ቡድን የተከፈሉት የታጠቁ ሃይሎች ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩም የእንቅስቃሴው መሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። ከአርበኞች ግንቦት 7 የተጠናከረ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸውም አክለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም በሰሜን ኢትዮጵያ የቀጠለው በመሳሪያ የተደገፈ እንቅስቃሴ በአብደራፊ፣ ቃብትያና፣ ሁመራ አካባቢዎች ተጠናክሮ መቀጠሉን የሚገልጹት የአይን ምስክሮች፣ የታጠቁ ሃይሎች ረቡዕ ዕለት በሳንጃ ወረዳ በሰነዘሩት ጥቃት የዳሽን ቢራ የጫነ መኪና መቃጠሉን ገልጸዋል።

በዚህም ጥቃት ሳቢያ መንገድ በመዘጋቱ በርካታ መኪኖች ከእንቅስቃሴ መገታታቸው ታውቋል።

ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ በአብደራፊ በቃፍቲያ ወታደራዊ ግጭቶች መቀጠላቸው የተሰማ ሲሆን፣ በርካታ የታጠቁና ያልታጠቁ ሃይሎች ወደ ትግል መውጣት መጀመራቸው ተመልክቷል።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,705FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here