spot_img
Monday, December 4, 2023
Homeዜናጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በእስር ቤት አለመኖሩ ተገለጸ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በእስር ቤት አለመኖሩ ተገለጸ

advertisement

ኢሳት
ኅዳር 30 ፥ 2009

Temesgen Desalegne
Temesgen Desalegne

በዝዋይ እስር ቤት በእስር ላይ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በእስር ቤቱ አለመኖሩንና ያለበት ቦታ እንደማይታወቅ የጋዜጠኛውን ጉዳይ የሚከታተሉ አካላት ለኢሳት ገለጹ።

የጋዜጠኛው ቤተሰቦች በበኩላቸው የማህበራዊ ድረገጾች ባሰራጩት መረጃ ዝዋይ እስር ቤት ተመስገንን ለመጠየቅ ሁለት ቀን ቢሄዱም፣ በእስር ቤቱ ተመስገን የሚባል የመንግስት እስረኛ አናውቅም የሚል ምላሽ እንደሰጧቸው አረጋግጠዋል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በማፈላለግ ላይ ያሉ የቤተሰቡ አባላት አዲስ አበባ በሚገኘው የማዕከላዊ ምርመራ እስር ቤት ቢሄዱም፣ “ተመስገን የሚባል የለም” መባላቸውን አስታውቀዋል።

ለሶስት ቀናት ጋዜጠኞው ያለበትን ቦታና ሁኔታ ለማወቅ ያልቻሉ የቤተሰቡ አባላት መንግስት ተመስገን ደሳለኝ ያለበትን ሁኔታ እንዲያሳውቋቸው አክለው ጠይቀዋል።

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በከሳሽ አቃቤ ህግ የተመሰረተበትን የስም ማጥፋት ሃስተኛ መረጃ ማሰራጨት መነሻ በማድረግ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሁለት አመት በፊት ጋዜጠኛው በሶስት አመት እስራት እንዲቀጣ መወሰኑ ይታወሳል።

ጋዜጠኛው በዚሁ በእስር ቤት በነበረ ጊዜ የጤና መታወክ እክል አጋጥሞት ህክምና እንዲያገኝ ተደርጎ እንደነበር በወቅቱ መገለጹም የሚታወቅ ነው።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here