በሙሉነህ ዮሃንስ
ታህሳስ 12 2009 ዓ ም
ወያኔ ከየገጠሩ ወደ ዳባት እስር ቤት ለመክተት የያዟቸውን ብዛት ያላቸው ያልታጠቁ ገበሬወች ሲያጓጉዙ በአካባቢው በጀግንነት የሚታወቁት የጎበዝ አለቆች በጥምረት ድንገተኛ ከበባ ውስጥ አስገብተው ጥቃት በመፈፀም ገበሬወቹን ነፃ አውጥተዋቸዋል።
ወያኔወች ተጨንቀዋል ደንግጠዋል። ከተማ እየገባን አመራር ላይ እርምጃ እንወስዳለን የሚል ደብዳቤ ተበትኗል። የጀግኖቹን ተደጋጋሚ አንፀባራቂ ድል ቀኑ ሲደርስ እንገልፀዋለን! አሁን ስራቸውን እናግዝ እንደግፍ!
በተያያዘ ዜና
በወያኔ ኮምማንድ ፓስቱ ቁጥጥር ስር የወደቀው የሰሜኑ እዝ ወደሰሜን እና ደቡብ ጎንደር የላካቸው በወታደራዊ ደህንነት እናበወታደራዊ ምህንድስና የተሰማሩ አባላቶች መገደላቸውንናመሰወራቸውን ለኮማንድ ፓስቱ የላከውና እጃችን ከገባው ሪፖርት ለማወቅ ተችሏል::
በሪፓርቱ መሰረት
1. ወታደር መሀንዲስ ትህትና በለው
2. ወታደራዊ የደህንነት አባል ቃሲም ይማም
3. ወታደር መሀንዲስ ዝናቡ ሕንጻ
4. ኮማንደር ማንያዝ ገብሬ
5. ወታደር ማሀንዲስ ቃቄ
የደረሱበት ያልታወቀ መሆኑን መረጃዋች ሲጠቁሙ
1. የ10 አለቃ ስንሻቅ፣
2. ጉዋድ ምሪ ወ/ር መሀሪ ጎላ
3. ወታደራዊ ደህንንት አባል ወ/ር ሶስና ፍስሀዬ
4. ወ/ር ገላው ስንቄ
5. ወ/ር ምጅዱ
6. ወ/ር አለሞ አጋፋሪ
7. ጋረድ ብሻፍለጋው
የተባሉ የመረጃና የቅኝት ወታደሮች
በህዝባዊ ሀይሉ መበላታቸው ተረጋግጦአል::