spot_img
Thursday, November 30, 2023
Homeአበይት ዜናጎንደር በኢንታሳል ሆቴል የደረሰው ፍንዳታ

ጎንደር በኢንታሳል ሆቴል የደረሰው ፍንዳታ

advertisement

ጥር 2 2009 ዓ ም

Gonder
Gonder
Source : Social Media

በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 በሚገኘው የኢንታሳል ሆቴል በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ አንድ ሰው ሳይሞት እንዳልቀረ የማህበራዊ ሚዲያ ምንጮች ዘግበዋል። የኢሳት የእንግሊዝኛ ዘገባ እንደሚያመለክተው ደሞ አራት ያህል ሰዎች ከቦንብ ፍንዳታው ጋር በተያያዘ ምክንያት የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸው ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።

ሙሉነህ እዮኤል በማህበራዊ ሜዲያ ስለጎንደር መረጃ በማካፈል ይታወቃል። እሱ ያካፈለው መረጃም ጥቃቱ በእርግጥም በጎንደር ከተማ በቀበሌ 18 አካባቢ በሚገኘው የኢንታሳል ሆቴል እንደደረሰ ቢያመለክትም የቁስለኛ ቁጥር አንድ እንደሆነ ያሳያል። ፍንዳታው ደረሰ የተባለው በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከምሽቱ 2 ሰዓት እንደሆነም ዘገባው ያሳያል። ሆቴሉ በስርዓቱ ባለስልጣናት የሚዘወተር ነውም ተብሏል።

የቤተ አምሃራ አክቲቪስቶችም በማህበራዊ ተመሳሳይ ዘገባ ይዘው ወጥተዋል።

ባሳለፍነው ሳምንት በባህር ዳር ግራንድ ሪዞርት ሆቴል ፍንዳታ እንደደረሰ መዘገቡ ይታወሳል።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here