spot_img
Monday, December 4, 2023
Homeአበይት ዜናሰበር ዜና – በዝቋላ ገዳም ዙሪያ ሰደድ እሳት ተቀሰቀሰ (ሐራ ዘተዋህዶ እንደዘገበው)

ሰበር ዜና – በዝቋላ ገዳም ዙሪያ ሰደድ እሳት ተቀሰቀሰ (ሐራ ዘተዋህዶ እንደዘገበው)

advertisement

መጋቢት 1 2009 ዓ ም

. ከደቡብ ምሥራቅ ወደ ገዳሙ ቅዱሳን ጫካ (ምዕራብ) እየተቀጣጠለ ነው
. የወረዳው አስተዳደር እና ሕዝብ ከገዳሙ ማኅበረሰብ ጋራ እየተጋገዘ ነው
. ቃጠሎውን ለመቆጣጠር ተጨማሪ ርዳታና ድጋፍ እየተጠየቀ ነው

Zequala Fire - Ethiopia

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ የደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ዙሪያ፣ ዛሬ፣ መጋቢት 1 ቀን 2009 ዓ.ም. ከቀትር በኋላ የእሳት ቃጠሎ ተቀሰቀሰ፡፡

ከቀኑ 9፡00 ገደማ፣ በገዳሙ ደቡብ ምሥራቅ አቅጣጫ ከርቀት የተቀሰቀሰው እሳት፣ ይህ ዘገባ በሚጠናቀርበት ሰዓት፣ የቅዱሳን ጫካ/ከተማ እየተባለ ወደሚጠራው ምዕራባዊ አቅጣጫ፣ በከፍተኛ ኃይል እየተቀጣጠለ መኾኑን የገዳሙ አባቶች ተናግረዋል፡፡

ቃጠሎው የተቀሰቀሰበት አካባቢ፥ “ከርቀት ታች የተራራው ጫፍ ላይ ነው፤ ከገዳሙ ከ7 እስከ 9 ኪ.ሜ ይኾናል፤” ያሉት ገዳማውያኑ፣ እሳቱን ለማጥፋት ቢረባረቡም፣ ማምሻውን ከዐቅም በላይ መኾኑን ተናግረዋል፡፡

“የቅዱሳን ጫካ የምንለው አለ፤ በአዱላላ በኩል ሲታይ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ነው፤ አኹን በእርሱ በኩል እየመጣ ነው፤ እኛም ወደዚያው እየሔድን ነው፤” በማለት በተለይ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን አስጊ እንደኾነ ገልጸዋል፡

አደጋው እንደተሰማ፣ የአዱላላ ከተማ አስተዳደር፣ ሕዝቡ ወደ እሳቱን ወደማጥፋት እንዲሔድ መቀስቀሱ የተሰማ ሲኾን፣ ነዋሪውም ወደ ስፍራው በመንቀሳቀስ የበኩሉን ጥረት እያደረገ እንዳለ ታውቋል፡

የመከላከያ ኃይልን ጨምሮ ሌሎችም አካላት አፋጣኝ እገዛና ድጋፍ እንዲያደርጉ፣ ቃጠሎውን ለመቆጣጠር በመረባረብ ላይ የሚገኙ ገዳማውያንና ምእመናን ጠይቀዋል፡፡

የቃጠሎውን መንሥኤ በተመለከተ፣ ትክክለኛው ምክንያት ለጊዜው ባይታወቅም፣ “እንደተለመደው ከሰል አክሳዮችን ነው የምንጠረጥረው፤” ብለዋል፣ ከገዳማውያኑ አንዱ አባት፡፡

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here