spot_img
Saturday, September 23, 2023
Homeዜናቆሼ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ የቆሻሻ መጣያ መሬት መንሸራት ከሃያ በላይ ሰዎች...

ቆሼ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ የቆሻሻ መጣያ መሬት መንሸራት ከሃያ በላይ ሰዎች ህይወት አለፈ

advertisement

መጋቢት 3 2009 ዓ ም

Garbage dump landslide - Addis Ababa - Ethiopia News
ምንጭ አሶሲየትድ ፕሬስ

በአዲስ አበባ ቆሼ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ የቆሻሻ መጣያ መሬት መንሸራት ምክንያት ቢያንስ ከሃያ በላይ ሰዎች እንደሞቱ ታውቋል። ከጥቂት ሰዓትት በፊት አሶሲየት ፕሬስ የሞቱን ቁጥር 15 በማለት የዘገበ ቢሆንም አሁን በብዙ ሜዲያዎች እየወጣ ባለው ዘገባ የሟቾች ቁጥር ቢያንስ 24 ሳይደርስ እንዳልቀረ ታውቋል። 37 ያህል ሰዎች በሆስፒታል እርዳታ እየተደረገላቸው ነው።

መሬቱ በአካባቢ በነበሩ ቤቶች ላይ ነው የተደረመሰው ተብሏል።

አደጋው የደረሰው ትላንት ማታ ከምሽቱ በስምንት ሰዓት አካባቢ እንደነበር ፋና ባወጣው አጭር ዘገባ አስታውቋል።

አቶ አሰፋ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ ለአሶሲየት ፕሬስ እንደተናገሩት አደጋው ሲደር በአካባቢው ከ150 በላይ ነበሩ ብለዋል። ስድስት ያህል የመቆፈሪያ መኪናዎች በፍለጋው ሂደት እንደተሰማሩ የአሶሲየትድ ፕሬስ ዘገባ ጨምሮ ገልጿል።

የእግሊዝኛው ዘገባ እዚህ አለ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,676FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here