spot_img
Thursday, November 30, 2023
Homeአበይት ዜናለማ መገርሳን ጨምሮ የኦፒዲዮ አመራሮች ላይ በህወሓት የተቀነባበረ የግድያ ሙከራ እንደከሸፈ ተሰማ

ለማ መገርሳን ጨምሮ የኦፒዲዮ አመራሮች ላይ በህወሓት የተቀነባበረ የግድያ ሙከራ እንደከሸፈ ተሰማ

advertisement

ቦርከና
ታህሳስ 10፤ 2010 ዓ ም

OPDO assassination attempt
የተጠርጣሪዎቹ ናቸው የተባለው መታወቂያ

የኦፒዲዮ አመራሮችን(ለማ መገርሳን እና አብይ አህመድን እንደሚያካትት ተገምቷል) በህወሓት የተቀነባበረ ነው የተባለ የግድያ ሙከራ እንደከሸፈ ተሰምቷል።

እስካሁን ዜናውን ከሌሎች የዜና ተቋማት ማረጋገጥ ባይቻልም ተቀማጭነቱ በኔዘርላንድ የሆነ አክቲቪስት ገረሱ ቱፋ ተጠርጣሪ ናቸው የተባሉትን ሁለት ግለሰቦች መታወቂያ በማያያዝ በማህበራዊ ድረ ገጽ ዘግቧል። ገረሱ “በኦሮሞ የመብት ተሟጋችነት” የሚታወቅ ሲሆን በሃገር ቤት በተለይም ደሞ በኦፒዲኦ ውስጥ ምንጮች እንዳሉት ይገመታል። ከዚህ በፊትም መረጃዎችን በማካፈል ይታወቃል።

ገረሱ በመካሄድ ላይ ያለውን የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ በሚመለከት ሰሞኑን ህወሓት በሃሳብ እንደተሸነፈ እና ኦፒዲዮ እና ብአዴን ተመሳሳይ አቋም ይዘው እንደተገኙ መዘገቡ ይታወሳል።

በኦፒዲዮ አመራሮች ግድያ ሊፈጽሙ ነበር የተባሉት ተጠርጣሪዎች ስም ዉብሸት ላውጋው ወልደሰማያት እና ባዮ ትህትና ዘሩ እንደሚባሉ የገረሱ ዘገባ ይጠቁማል። ነገር ግን ግድያው ለማስፈጸም ታስቦ ስለነበረበት ሁኔታ እና ተያያዥ ጉዳዮች የቀረበ ዝርዝር የለም።

በኦፒዲኦ አመራር ላይ ታስቦ የነበረውን የግድያ ሙከራ እንዲያስፈጽሙ ህወሓት ከደህንነት መዋቅር ውስጥ መልምሏቸዋል የተባሉት የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ይመስላሉ። የፖለቲካ ተንታኞች ለህወሓት እጂግ አስፈሪ እየሆነ የመጣው እና እያንሰራራ ያለውን የአማራ እና ኦሮሞ አንድነት በማጨናገፍ በሁለቱ ቋንቋ ተናጋሪዎች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የታሰበ ነው በማለት የህወሓትን ደባ ያጋልጣሉ።

ህወሓት እንደዚህ አይነት እርምጃ ውስጥ ሊገባ እንደሚችል የሚገመት ቢሆንም በተንታኞች በዚህ ፍጥነት እዲህ አይነት ርምጃ በማቀናበር ቀውስ ወደሚያባባስ ሁኔታ ለመፍጠር ይፈልጋል የሚል አስተሳሰብ ያለ አይመስልም ነበር።
——
ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ማድረግ አይርሱ

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here