spot_img
Saturday, September 30, 2023
Homeአበይት ዜናየዶ/ር መረራ ጉዲና ክስ ተቋረጠ ፤ እስከ ረቡዕ ባለው ጊዜ ...

የዶ/ር መረራ ጉዲና ክስ ተቋረጠ ፤ እስከ ረቡዕ ባለው ጊዜ …

advertisement

ጥር 7 ፣ 2010

Merera Gudina
ዶ/ር መረራ ጉዲና

አፍቃሪ መንግስት የሆኑ መገናኛ ብዙሃን ዛሬ የፌደራሉን ጠቅላይ አቃቢ ህግ ጠቅሰው እንደዘገቡት የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረንስ ተቃዋሚ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና ክስ ተቋርጧል። ዶ/ር መረራ በኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጂ በታወጀ ማግስት ለስራ ጉዳይ ከሄዱበት ከአውሮፖ ሲመለሱ ተይዘው ከአንድ አመት በላይ ለሚሆን ጊዜ በእስር ላይ እንደነበሩ ይታወቃል።

በፌደራል ደረጃ የአንድ መቶ አስራ አምስት ሰዎች ክስ ተቋርጧል የተባለ ሲሆን ፤ በደቡብ ክልል እስከ አራት መቶ አስራ ሶስት የሚደርሱ “ተጠርጣሪዎች”ም እንዲሁ ክሳቸው ተቋርጧል ተብሏል።

ኢህአዴግን የመሰረቱት አራት ዘውጌ ተኮር የፖለቲካ ፓርቲዎች በኢትዮጵያ የተፈጠረውን የፖለቲካ ቀውስ ምክንያት በማድረግ ከሁለት ሳምንት በላይ የወሰደ ግምገማ በማድረግ በሰጡት መግለጫ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እና ለብሄራዊ መግባባት “በወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ” ያላቸውን እስረኞች እንደሚፈታ ማሳወቁ ይታወሳል።

ሆኖም በፌደራል ደረጃ ይለቀቃሉ ከተባሉት ከዶ/ር መረራ ጉዲና ውጭ በተቃዋሚ መሪነት የሚታወቁ ኢትዮጵያውያን ስም አልተጠቀሰም። በደቡብ ክልል ክሳቸው ተቋርጧል የተባሉት ለእስር የተዳረጉት በጌዲዮ ዞን ተነስቶ ከነበረ ግጭት ጋር በተያያዘ እንደነበረም የፋና ዘገባ ይጠቁማል ።

እንደ ፋና ብሮድካስቲንግ ዘገባ እስረኞቹ እስከ ረቡዕ ባለው ጊዜ “የተሃድሶ ስልጠና” ወስደው ይፈታሉ።
———
ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,705FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here