spot_img
Wednesday, March 22, 2023
Homeአበይት ዜናአንዱዓለም አራጌ እና እስክንድር ነጋ መንግስት ለዳግም ውንጀላ ያዘጋጀላቸውን ወጥመድ ሰበሩ

አንዱዓለም አራጌ እና እስክንድር ነጋ መንግስት ለዳግም ውንጀላ ያዘጋጀላቸውን ወጥመድ ሰበሩ

- Advertisement -

Enkinder-Nega- Andualem Arage

ቦርከና
ጥር 30 2010 ዓ.ም

የፌደራሉ አቃቤ ህግ ትላንት ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ እስክንድር ነጋ እና አንዱዓለም አራጌ ከሌሎች ከሰባት መቶ በላይ የሚሆኑ ፌደራል እና ክልል እስር ቤቶች ካሉ አስረኞች ጋር እንደሚለቀቁ ቢገልጹም ፤ ማንነታቸው ባይታወቅም መንግስቱን ከሚመሩ ባለስልጣናት ውስጥ ባልሰሩት ወንጀል ተከሰው ከአስራ ስምንት ዓመት በላይ የተፈረደባቸውን ሁለቱን እስረኞች ያለመፍታት አዝማሚያ አሳይተዋል::

አንዱዓለምን እና እስክንድርን ለመፍታት የተደረሰው ውሳኔ እንደተቀለበሰ የታወቀው ዛሬ የእስር ቤቱ ኃላፊዎች አንዱዓለምን እና እስክንድርን ወደ ቢሮ በማስጠራት “የግንቦት ሰባት ድርጅት አባል ነን” ብላችሁ ፈርሙ ተብለው ለመፈታታቸው እንደ ቅድመ ሁኔታ ከተቀመጠ በኋላ ነው:: ሆኖም አንዱዓለም እና እስክንድር “የግንቦት ሰባት ዓባል ስላልሆንን ዓባል ነን ብለን አንፈርምም” በማለት መንግስት ለዳግም ውንጀላ ለማመቻቸት ያመጣው ነው የተባለውን ወጥመድ ሰብረውታል::

የአንድነት ለፍትሕ እና ለዲሞክራሲ ጸሃፊ የነበረው አንዱዓለም አራጌ እና ጋዜጠኛ እስክንድር በሽብርተኝነት እና አመጽ በማነሳሳት ወንጀል ተከሰው የአስራ ስምንት አመት ጽኑ እስራት ተፈርዶባቸው እስካሁን ለስድስት ዓመታት ያህል በእስር ቆይተዋል:: ሆኖም ዓለም ዓቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችም ሆነ ኢትዮጵያውያን እንደ ፖለቲካ እና የህሊና እስረኛ እንደሚያዩአቸው ይታወቃል::

ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,440FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here