spot_img
Wednesday, March 22, 2023
Homeአበይት ዜናበሃማሬሳ ሃረር በተነሳ ህዝባዊ ተቃውሞ ላይ የአጋዚ ሰራዊት በከፈተው ተኩስ አስር ያህል...

በሃማሬሳ ሃረር በተነሳ ህዝባዊ ተቃውሞ ላይ የአጋዚ ሰራዊት በከፈተው ተኩስ አስር ያህል ሰዎች እንደተገደሉ ተሰማ ፤ በብዙ ከተሞች አድማ ተመቷል

- Advertisement -

ሃማሬሳ ሃረር

ቦርከና
የካቲት 5 2010 ዓ ም

ትላንት በሃማሬሳ ሃረር በሃገር ውስጥ ተፈናቃዮች ካምፕ “መንግስት የሚገባውን ትኩረት አልሰጠንም፤ ለችግራችን አፋጣኝ መልስ እንፈልጋለን” በማለት ሰልፍ የወጡ ከኢትዮጵያ ሶማሊ ክልል በተፈናቀሉ ወጣት ኢትዮጵያውያን ላይ የመንግስት ታማኝ ወታደሮች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ አስር ያህል ሰዎች እንደተገደሉ እና እስከ አስራ አንድ የሚደርሱ ሰዎች እንደቆሰሉ በማህበራዊ ሚዲያ የወጡ መረቻዎች አመልክተዋል።

ከሟቾች ውስጥ አንደኛው የክልሉ ፖሊስ አባል መሆኑ የታወቀ ሲሆን ከአካባቢው ምንጭ አለን በሚል መረጃ በማህበራዊ ድረ ገጽ እንዳጋሩት የመብት ተሟጋቾች ከሆነ ፖሊሱ የመከላከያ ሰራዊትን ጥቃት በመቃወም ሲታኮስ ነው የተገደለው።

የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ከሃማሬሳ ጋር በተያያዘ የሟቾችን ቁጥር አራት ነው ያለ ሲሆን በሃገር ውስጥ ተፈናቃዮች ካምፕ ባሉ ወጣቶች እና በፖሊስ እና መከላከያ በተፈጠረ ግጭት ሳቢያ እንደተከሰተ አስታውቋል።

ምክንያቱን በሚመለከትም ወጣቶች ወደ ስደተኛ ጣቢያው ምግብ በማመላለስ ላይ የነበሩ የጭነት መኪናዎች ላይ ጥቃት በመሰንዘር መኪኖችን በማቃጠላቸው ነው ሲሉ በማህበራዊ ሚዲያ ያሉ የመንግስት አፈቀላጤዎች ይሟገታሉ።

እንዲህ ባሉ ጉዳዮች በማህበራዊ ሚዲያ ፈጣን መረጃ በማካፈል የሚታወቁት የክልሉ መንግስት ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋ ቅጤሳ እስካሁን በጉዳዮ ላይ ያጋሩት መረጃ የለም።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ለሚቀጥሉት ሶስት ቀናት በማህበራዊ ሚዲያ አማካይነት የተጠራው ህዝባዊ አመጽ በስራ ላይ ውሎ በክልሉ በተለያዮ ከተሞች የንግድ እንቅስቃሴዎች ቆመዋል፤ የህዝብ ማጓጓዣዎች ዝውውርም እንደተገታ ታውቋል። የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሁኔታውን አምኖ “ምክንያቱን እያጣራ እንደሆነ” አሳውቋል።
———
ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

ከኢትዮጵያ መረጃ ለማካፈል የምትፈልጉ በሚከተለው አድራሻ መላክ ይቻላል info@borkena.com

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,440FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here