spot_img
Thursday, November 30, 2023
Homeአበይት ዜናማሙሸት አማረ ፤ አንዱዓለም አራጌ ፤ እስክንድር ነጋ ፤ እማዋይሽ ዓለሙን...

ማሙሸት አማረ ፤ አንዱዓለም አራጌ ፤ እስክንድር ነጋ ፤ እማዋይሽ ዓለሙን ጨምሮ ሰባት መቶ አርባ ስድስት የፖለቲካ እስረኞች ተለቀዋል

advertisement

Mamushet 469x555
ቦርከና
የካቲት 7 2010 ዓ. ም

ትላንትና በቀለ ገርባ እና ጓደኞቹ ከእስር መፈታታቸው ይታወቃል:: በዛሬው ዕለትም መንግስት ተጨማሪ ሰባት መቶ አርባ ስድስት የፖለቲካ እስረኞችን ፈቷል::

ማሙሸት አማረ ፤ አንዱዓለም አራጌ ፤ እስክንድር ነጋ ፤ እማዋይሽ ዓለሙ ፤ ክንፈሚካኤል ደበበ ከተፈቱ የፖለቲካ እስረኞች ውስጥ ይገኙበታል::

በመቶዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በር ተሰባስበው ለተፈቱት የፖለቲካ እስረኞች ደማቅ አቀባበል አድርገዋል::

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሰላማዊ ትግሉን እንደሚቀጥል ወኔ እየተናነቀው ለደጋፊዎቹ ተናግሯል:: እስክንድር ነጋ እና አንዱዓለም ጌታቸው መንግስትን በኃይል ለመጣል አሲራችሁአል በሚል የሃሰት ውንጀላ የአስራ ስምንት እስራት ተፈርዶባቸው ለሰባት ዓመታት ያህል በግፍ መታሰራቸው ይታወቃል::

ወ/ሮ እማዋይሽ አለሙ ከነ ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ጋር በመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተከሰው ብዙ ግፍ እና መከራ ተቀብለዋል:: የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጂት አመራር የሆኑት ማሙሸት አማረ ለበርካታ ዓመታት ሲታሰሩ እና ሲፈቱ የቆዮ ሲሆን ዛሬ በመፈታታቸው የተለየ ደስታ እንዳልተሰማቸው እና ደስተኛ የሚሆኑት የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻ ሲሆን መሆኑን ተናግረዋል::

የፖለቲካ እስረኞቹ የተፈቱት መንግስት በታህሳስ ወር የ”ዲሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋት” እና “ለብሔራዊ መግባባት” እስረኞችን እለቃለሁ በማለት ካሳወቀ በኋላ ነው፥፥ ሆኖም አሁንም ቢሆን እነ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ በርካታ የፖለቲካ እስረኞች አልተለቀቁም::

ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here