spot_img
Wednesday, June 7, 2023
Homeአበይት ዜናደኢህዴን አቶ ሽፈራው ሽጉጤን የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ

ደኢህዴን አቶ ሽፈራው ሽጉጤን የድርጅቱ ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ

- Advertisement -

SEPDM

ቦርከና
ጥቅምት 20 2010 ዓ ም

የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢሕዴን) የሃያ አራት ቀን የድርጂት ግምገማውን ሲያጠናቅቅ አቶ ሽፈራው ሽጉጤን የድርጅቱ ሊቀመንበር ፤ አቶ ሲራጂ ፈርጌሳን ደሞ ምክትል ሊቀመንበር አድርጎ መመረጡን አስታውቋል።

ድርጂቱ በወቅታዊ ሃገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቻለሁ ብሏል። ካሳለፋቸው ውሳኔዎች አንዱ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፖርቲዎች በክልሉ ያለስጋት በነጻነት እንዲንቀሳቀሱ እና አላማቸው እንዲያስተዋውቁ አደርጋለሁ ብሏል።

በተጨማሪም የኃይለማርያም ደሳለኝን ከድርጂቱ ኃላፊነት ለመልቀቅ ያቀረቡን ውሳኔ ተቀብሎ አጽድቋል።

ባለፈው ሳምንት ድርጂቱ ያሳለፈው ውሳኔ በማህበራዊ ድረገጽ ከወጣ ከሰዓታት በኋላ መረጃው እንዲነሳ መደረጉ ይታወሳል። በሰዓቱ የተሰጠው ምክንያትም የድርጂቱ የማህበራዊ ድረ ገጽ ባልታወቁ ሰዎች ተጠልፎ የተለጠፈ ነው። ደኢሕዴን አመራሮችን ገና አልመረጠም የሚል ነው።

የሺፈራው ሺጉጤ በሊቀመንበርነት መመረጥ በተቃዋሚው ጎራ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ እንደነበረ ይነገራል። ምክንያት ተቃውሞ ለበረታበት ህወሓት ሺፈራው ሺጉጤ ታማኝ ናቸው በሚል። ኃይለማርያምን በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንዲተካ ህወሓት ያስመርጠዋል የሚለው አስተያየት ጠንከር ይላል።
ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,879FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here