spot_img
Monday, October 2, 2023
Homeአበይት ዜናየአጋዚ ሰራዊት በሞያሌ በንጹሃን ላይ የጂምላ ግድያ ማድረጉን ተከትሎ ሃምሳ ሺህ የሚሆኑ...

የአጋዚ ሰራዊት በሞያሌ በንጹሃን ላይ የጂምላ ግድያ ማድረጉን ተከትሎ ሃምሳ ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ወደ ጎረቤት ኬኒያ ተሰደዋል

advertisement
Moyale
የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን
ምንጭ ፤ የጀርመን ድምጽ ራዲዮ

ቦርከና
መጋቢት 3 2010 ዓ ም

ባለፈው ሳምንት መገባደጃ የህወሓት መንግስት ታማኝ ወታደሮች በኢትዮጵያ የድንበር ከተማ ሞያሌ ላይ አስር ያህል ሰዎችን ከገደሉ እና በርካቶችን ካቆሰሉ በኋላ 50,000 የሚሆኑ የከተማው ነዋሪዎች አጋዚ ተጨማሪ ስጋት ሊፈጥር ይችላል በሚል ስጋት ወደ ጎረቤት ኬኒያ መሻገራቸው ተሰምቷል። እስካሁን ባለው መረጃ መረሰት የተሰደዱት ኢትዮጵያውያን ያሉት በሞያሌ ኬኒያ ነው።

50,000 የኢትዮጵያ ሞያሌ ነዋሪዎች ወደ ኬኒያ ሞያሌ መሰደዳቸውን የኢትዮጵያ ሞያሌ ከተማ ከንቲባ አቶ አስቻለው ዮሐንስ ለጀርመን ድምጽ ራዲዮ አረጋግጠዋል። ከአንድ ቀን በፊት ከንቲባው ከአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ የአማርኛ አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ኮማንድ ፖስት አንድ ሻለቃ ጦር ወደ ሞያሌ ኢትዮጵያ የላኩት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ታጣቂዎች እንደገቡ መረጃ ስለደረሰኝ ነው ያለውን ሃሰት ሲሉ እንዳጣጣሉት የሚታወስ ነው። አብዛኛው ግድያ የተፈጸመው ሸዋበር ተብሎ በሚጠራው የንግድ እንቅስቃሴ በነበረበት አካባቢ እንደሆነም አስታውቀዋል። ድርጊቱንም አግባብ አይደለም ሲሉ ከንቲባው ኮንነውታል።

በኬኒያ የቀይ መስቀል ማህበር ለተፈናቀሉ ወገኖች የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ አዳደረገም ተሰምቷል።

የኬኒያ ሞያሌ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ)ተዋጊዎች በስፋት የሚንቀሳቀሱበት አካባቢ እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን ይሄን ያህል ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያን በአንድ ጊዜ ኦነግ በሚንቀሳቀስበት አካባቢ መሰደዳቸው ድርጂቱ አጋጣሚውን በወታደራዊም ሆነ በፖለቲካ አንጻር ሊጠቀምበት ይችላል የሚሉ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ ነው።
__
ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,723FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here