spot_img
Monday, June 5, 2023
Homeአበይት ዜናዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ሳምንት ኢትዮጵያን የጎበኙትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸውን ከስልጣን አነሱ

ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ሳምንት ኢትዮጵያን የጎበኙትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸውን ከስልጣን አነሱ

- Advertisement -
ሬክስ ቲለርሰን
ሬክስ ቲለርሰን ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋር ተገናኝተው በተወያዩበት ጊዜ
ምንጭ: ፋና

ቦርከና
መጋቢት 4 2010 ዓ ም

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደረጉትን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸውን ሬክስ ቲለርሰንን ከስልጣን አንስተዋል። በምትካቸው የአሜሪካ የስለላ ድርጂት (ሲ አይ ኤ) ኃላፊ የሆኑትን ማይክ ፓምፒዮን ሾመዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ ርምጃውን የወሰዱት ከሬክስ ቲለርሰን ጋር በአንዳንድ የፖሊሲ ጉዳዮች (ለምሳሌ በኢራን ጉዳይ) ልዮነት አለን በማለት ነው።

የስልሳ አንድ ዓመት እድሜ ያላቸውን የሲ አይ ኤን ምክትል ዳይሬክተር ጂና ሃስፐልን በሲ አይ ኤ ዋና ኃላፊነት ይሾማሉ ተብሎ ይጠበቃል። ሁለቱም ተሿሚዎች በአሜሪካ ሴኔት ፊት ቀርበው መጽደቅ አለባቸው የኃላፊነት ቦታቸውን ከመያዛቸው በፊት። ጂና ሃስፐል ከሰብዓዊ መብት ጋር በተያያዘ ባላቸው ዶሴ እስር ቤት እንጂ ሹመት አይገባቸውም የሚሉ ወገኖች አሉ።
__
ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,880FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here