spot_img
Sunday, May 28, 2023
Homeአበይት ዜናእስክንድር ነጋ ፤ አንዱዓለም አራጌ እና ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ አስራ ሁለት ...

እስክንድር ነጋ ፤ አንዱዓለም አራጌ እና ተመስገን ደሳለኝን ጨምሮ አስራ ሁለት ጋዜጠኞች ፤ ጦማሪዎች እና የመብት ተሟጋቾች ዛሬ በአዲስ አበባ ታስረዋል

- Advertisement -

Enkinder-Nega- Andualem Arage
ቦርከና
መጋቢት 16 2019 ዓ.ም

ዛሬ ለቡ በሚገኘው የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ቤት በቅርቡ ከእስር የተፈቱትን አንዱዓለም አራጌን እና እስክንድር ነጋን ለመሸለም እና ለማመስገን በተዘጋጀ የግብዣ ስነ ስርዓት ፖሊስ በድንገት በመክበብ አንዱዓለም አራጌን እና እስክንድር ነጋን ጨምሮ አስራ ሁለት ያህል ሰዎች እንደታሰሩ ተሰምቷል።

እንደ ኢሳት ዘገባ የታሰሩት ጋዜጠኞች ፤ጦማሪዎች እና ፖለቲከኞች ዝርዝር የሚከለው ነው

፩) ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ
፪) ጋዜጠኛ ፍቃዱ ማህተመ ወርቅ
፫)ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
፬) አቶ አንዱዓለም አራጌ
፭) አቶ አዲሱ ጌታነህ
፮) ጦማሪ ዘላለም ወርቅ አገኘሁ
፯) ጦማሪ ማህሌት ፋንታሁን
፰) ጦማሪና ጋዜጠኛ በፍቃዱ ኃይሉ
፱) ወይንሸት ሞላ
፲) ይድነቃቸው አዲስ
፩፩) ስንታየሁ ቸኮል
፩፪) ተፈራ ተስፋዬ

በገዢው ፓርቲ ማህበራዊ ደረ ገጽ ሰሞኑን የሚለቀቁ መልዕክቶች የህወሓት ቡድን ኢሕአዴግን እንደገና ሙሉ በሙሉ እደተቆጣጠረ የሚያመላክቱ እንደሆኑ እና ፓርቲው ወደ ቀደመ የጭቆና እና የአፈና አገዛዝ ለመመለስ መወሰኑን የሚያመላክቱ ናቸው የሚሉ አስተያየት ሰጭዎች አሉ::

በተያያዘ ዜና ዛሬ በባህር ዳር ተመሳሳይ አፈና እና እስር የነበረ ሲሆን የዮኒቨርሲቲ መምህራኞች ጭምር አንደታሰሩ ታውቋል:: ባለፈው ሳምንት የኦሮሞ ክልላዊ መንግስት ፍትህ ቢሮ ቃል አቀባይ አቶ ታየ ደንደዓ እንደታሰረ ይታወሳል::
ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,856FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here