spot_img
Thursday, November 30, 2023
Homeአበይት ዜናበደቡብ አፍሪካ በሁለት ቀናት ውስጥ ሰባት ኢትዮጵያውያን ተገደሉ

በደቡብ አፍሪካ በሁለት ቀናት ውስጥ ሰባት ኢትዮጵያውያን ተገደሉ

advertisement

ደቡብ አፍሪካ

ቦርከና
ሚያዚያ 26 2010 ዓ.ም

በደቡብ አፍሪካ ከጆሃንስበርግ ከተማ 28 ኪሎሜትር ገደማ በስተደቡብ ምስራቅ በምትገኘው የቶኮዛ ከተማ 48 ሰዓት ባልሆነ ጊዜ ውስጥ ሰባት ኢትዮጵያውያን እንደተገደሉ ተሰማ::

ኢሳት ከአካባቢው የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አመራሮች አገኘሁት ባለው መረጃ መሰረት ግድያው የተፈጸመው ትላንት አኩለ ሌሊት ላይ ነው:: ሰለባዎቹ በንግድ ስራ የሚተዳደሩ እንደነበሩ ሱቆች እንደነበሯቸው እና ከግድያው በኋላ ንብረታቸው እንደተዘረፈም ታውቋል::

ግድያውን ያደርሱት የተደራጁ የሚመስሉ ዘራፊዎች እንደሆኑ ቢታመንም ፤ ግድያው ሙሉ በሙሉ ከዘረፋ ጋር የተያያዘ ለመሆኑ የተረጋገጠ ነገር እንደሌለ እና ጉዳዮ በምርመራ ላይ እንዳለ ኢሳት በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሰብሳቢ የሆኑንት አቶ ታምሩ አበበን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል::

በተያያዘ ዜና የዛሬ ሳምንት ገደማ በቅጥር ነብሰ ገዳይ የተገደለው አፍቃሪ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ተሟጋች ገዛኸኝ ገብረመስቀል ግድያው በተቀነባበረ ሁኔታ ለመፈጸሙ ስም መግለጽ ያልፈለገ የደቡብ አፍሪካ ፖሊስ አባል ተናግሯል፤ ታዋቂው የደቡብ አፍሪካ ሜይል ኤንድ ዘጋርድያን ሚዲያም በግድያው ላይ ሰፊ ዘገባ ይዞ ወጥቷል::

ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here