spot_img
Wednesday, March 22, 2023
Homeአበይት ዜናበሞያሌ በተቀሰቀሰ የጎሳ ግጭት በርካታ ኢትዮጵያውያን እንደተገደሉ ተሰማ

በሞያሌ በተቀሰቀሰ የጎሳ ግጭት በርካታ ኢትዮጵያውያን እንደተገደሉ ተሰማ

- Advertisement -
ሞያሌ
ምንጭ: ኢሳት

ቦርከና
ሚያዚያ 29 ፤ 2010 ዓ ም

ትላንት በኢትዮጵያ ሞያሌ የድንበር ከተማ አካባቢ ደርሷል በተባለ የጎሳ ግጭት በርካታ ዜጎች መገደላቸው ተሰምቷል።

በኦሮሚኛ ተናጋሪዎቹ ቦርናዎች አና በሶማሊኛ ተናጋሪዎቹ ገሪ መካከል ረዥም ጊዜ ያስቆጠረ እና ብዙ ህይወት የጠፋበት ግጭት እንደነበረ ቢታወስም ትላንት ያገረሸበት ምክንያት በውል አልታወቀም። የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እስካሁን በጉዳዮ ላይ ያቀረቡት ዘገባ የለም፡፡

ኢሳት ግጭቱ በሶማሌ ልዮ ኃይል ታጣቂዎች በተሰነዘረ ጥቃት እንደተጀመረ ፤ የኦሮሞ ክልል ፓሊስ የአጸፋ ምላሽ መስጠቱን ገልጾ ከኢትዮጵያ ሶማሊ ፖሊሶች አምስት መገደሉን እና ከኦሮሞ ፖሊሶች በኩል ያለውን የሟች ቁጥር እያጣራ መሆኑን ገልጾአል፡፡

ግጭቱን ተከትሎ በርካታ ዜጎች ለህይወታቸው በመፍራት ወደ ጎረቤት ኬንያ መሰደዳቸውም ታውቁአል፡፡

ትላንት ባገረሸው ግጭት ባብዛኛው የተገደሉት ኦሮሚኛ ተናጋሪ ኢትይጵያውያን መሆናቸውም ተሰምቷል።

የቀድሞ ፈደራል የመንግስት ጉዳዮች ኃላፊ የነበሩት የአሁኑ የኦሮሞ ክልል መንግስት ቃል አቀባይ ዶር ነገሪ ሌንጮ ትላንት በማህበራዊ ድረገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት “በሞያሌ በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ተቀባይነት የለሌውና የሚወገዝ ነው፡፡ ሃላፍነት የተሰጠዉ አካል አስፈላጕን እርምጃ ወስዶ ጉዳቱን ከወድሁ ማሰቆም አለበት ብለዋል፡፡”

ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,440FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here