spot_img
Wednesday, November 29, 2023
Homeአበይት ዜናየፌደራል አቃቢ ህግ የዶ/ር ፍቅሩ ማሩን እና ሌሎች 61 ተከሳሾችን የክስ ሂደት...

የፌደራል አቃቢ ህግ የዶ/ር ፍቅሩ ማሩን እና ሌሎች 61 ተከሳሾችን የክስ ሂደት ማቋረጡን አስታወቀ

advertisement

Fikru Maru
ቦርከና
ግንቦት 3 2010 ዓ ም

የፌደራሉ ጠቅላይ እቃቢ ህግ ሲዊድናዊ ዜግነት ያላቸውን የልብ ቀዶ ህክምና ሃኪም ዶ/ር ፍቅሩ ማሩን ጨምሮ የሌሎች 61 ተከሳሾችን የክስ ሂደት ማቋረጡን አስታውቋል። ሰሞኑን በነበረው ችሎት ክሳቸው እንዲቋረጥ ከተወሰነባቸው አብዛኞቹ ክሳቸውን እንዲከላከሉ ተበይኖባቸው እንደነበር ይታወሳል። ተከሳሾቹ ባለፈው አመት በቅሊንጦ እስር ቤት በተነሳው የእሳት አደጋም ጋር በተያያዘ ተወንጂለው ሲንገላቱ እንደነበር የሚታወቅ ነው።

“ሰው በመግደል” የተወነጀሉ አራት ተከሳሾች ግን ክሳቸው እንዳልተቋረጠ እና እንደሚከላከሉ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ኢዜአ ዘግቧል።

በቅርቡ ጊዜ ከተለቀቁ የፖለቲካ እስረኞች ተሞክሮ የክስ ሂደት ከተቋረጠ በቀናት ውስጥ እስረኞች ሲለቀቁ ተስተውሏል። ዛሬ ክሳቸው የተቋረጠላቸው የፖለቲካ እስረኞች ገና አልተለቀቁም።

——
ወቅታዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here