spot_img
Wednesday, November 29, 2023
Homeአበይት ዜናየአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በሚቀጥለው ሳምንት ከእስር...

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በሚቀጥለው ሳምንት ከእስር እንደሚፈቱ ተሰማ

advertisement

Andargachew 4

ቦርከና
ግንቦት 15፥ 2010 ዓ.ም

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በሚቀጥለው ሳምንት ከእስር እንደሚፈቱ ተሰማ። የፖለቲካ እስረኞች በተፈቱ ሳምንታት ውስጥ ጅምሮ እንደሚፈታ ሲወራ እንደቆየ የሚታወቅ ሲሆን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በሚቀጥለው ሳምንት እንደሚፈታ ወደ እርግጠኝነት የቀረበ መረጃ የተገኘው ግን በትላንትናው እለት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በብሔራዊ ቤተ መንግስት የትግራይ ተወላጆች ጋር የምክክር ስብሰባ ባደረጉበት ሰዓት ጉዳዮን አንስተው ከተናገሩ በኋላ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ “አንዳርጋቸው ጽጌን በማሰራችን የተጠቀምነው ምንም ነገር የለም ፤ ጥላቻን እና ከኢንግሊዝ መንግስት እናገኘው የነበረውን እርዳታ ነው ያጣነው” እንዳሉ በቦታው ታድመን ነበር ያሉ ሰዎች ካሰራጩት መረጃ ለማወቅ ተችሏል።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከአራት አመታት በፊት በየመን ሰንዓ አለማቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በትራንዚት ላይ እያለ በየመን የጸጥታ ኃይሎች ታፍኖ ለህወሓት መራሹ መንግስት ተላልፎ ከተሰጠ ቀን ጀምሮ ከማንም ሰው ጋር እንዳይገናኝ ተደርጎ ለብቻው በጠባብ ክፍል ውስጥ መታሰሩ ይታወቃል።

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here