spot_img
Thursday, November 30, 2023
Homeአበይት ዜናየህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ነገ የሚካሄድ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ

የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ነገ የሚካሄድ አስቸኳይ ስብሰባ ጠራ

advertisement

TPLF-Logo የህወሃት

ቦርከና
ሰኔ 3፤2010 ዓ. ም

የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ “የክልኩን እና የሃገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታ እገመግማለሁ” በሚል አስቸኳይ ስብሰባ እንደጠራ ለድርጂቱ ቅርበት አለው የሚባልለት የፋና ብሮድካስቲግ ኮርፖሬት ዘግቧል።

ድርጂቱ ስብሰባውን እንዳጠናቀቀ የገመገማቸውን ነጥቦች እና የደረሰበትን አቋም ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል።

ከባድማ ጋር ተያይዞ ገዢው ፓርቲ ሰሞኑን ያሳለፈው ውሳኔ ጋር የተያያዘ እንደሆነም ተገምቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከኡጋንዳ ወደ ግብጽ አቅንተው የሁለት ቀናት ይፋዊ የስራ ጉብኝት በሚያደርጉበት ወቅት ነው የህወሓት ማአከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ የተጠራው። በዚህ ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የጦር ኃይሎች ኤታማዦር ሹሙን ሳሞራ ዩኑስን በጡረታ አሰናብተው በምትካቸው ጀኔራል ሰዐረ መኮነንን መሾማቸው ይታወሳል።

በተያያዘ ዜና ትላንት በኢሮብ ትግራይ የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከአስራ ስምንት ዓመት በፊት ከኤርትራ ጋር በአልጀርስ የተደረገውን የሰላም ስምምነት ሙሉ በሙሉ በመቀበል ባድመን ለኤርትራ አሳልፎ ለመስጠት የደረሰበትን ውሳኔ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ ተደርጓል።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here