spot_img
Sunday, September 24, 2023
Homeአበይት ዜናየህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጂ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ተገድለው ተገኙ

የህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጂ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ተገድለው ተገኙ

advertisement

ስመኘው በቀለ

ቦርከና
ሃምሌ 19 : 2010 ዓ. ም.

የህዳሴው ግድብ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጂ በመሆን በታታሪነት ሲሰሩ የነበሩት ኢንጂንር ስመኘው በቀለ ዛሬ ጠዋት በአዲስ አበባ ተገድለው ተገኝተዋል።
አስከሬናቸው ያሽከረክሯት በነበረ ቪ ቲዮታ መኪና ውስጥ ከመስቀል አደባባይ ዋናው መንግድ ገባ ብሎ እንደተገኘም የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀማል ዘይኑ ተናግረዋል።

አስከሬናቸው በጥይት መመታት ምልክት እንዳለበት እና በቀኝ እጃቸውም ሽጉጥ ይዘው እንደተገኙም አክለው ገልጥጸዋል። አስከሬናቸውም ለምርመራ ወደ ጳውሎስ ሆስፒታል መላኩ ታውቋል፥ፖሊስ ለምርመራው ይጠቅመኛል ያለውን መረጃ እንደሰበሰበ እና ምርመራው እንደተጠናቀቀም ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን አሳውቋል።

የተቀናበረ ግድያ በሚመስለው በዚህ ድርጊት ቁጭት የገባቸው ኢትዮጵያውያን በመዲናዋ በአዲስ አበባ እና በባህር ዳር የተቃውሞ ሰልፍ እንዳደረጉም ታውቋል።

የቦርከና ድረ ገጽ ዝግጂት በኢንጂነር ስመኘው በቀለ አሳዛኝ ግድያ የተሰማውን ሃዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸው እና ለመላው ኢትዮጵያውያን መጽናናትን ይመኛል።

ቪዲዮ ምንጭ : የኢትይጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,682FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here