spot_img
Monday, May 29, 2023
Homeአበይት ዜናበኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል የተከሰተውን ሁከት ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊቱ ወደ አካባቢው እንደተሰማራ ተሰማ

በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል የተከሰተውን ሁከት ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊቱ ወደ አካባቢው እንደተሰማራ ተሰማ

- Advertisement -

Jijiga

ቦርከና
ሃምሌ 25, 2010 ዓ. ም

ሰሞኑን በሱማሌ ኢትዮጵያ ክልል እንዳዲስ ያገረሸ ሁከት መነሳቱን ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊት ወደ አካባቢው እንዲሰማራ እንደተደረገ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዛሬ የመከላከያ ሚኒስቴርን በመጥቀስ ባወጣው ዘገባ በጂጂጋ አካባቢ የተፈጠረው ችግር ወደ ሌሎች አካባቢዎች መዛመቱን ገልጾ እየታየ ያለው ነገር በምንም አይነት ተቀባይነት እንደሌለው እና የመከላከያ ሰራዊቱ በተሰጠው ህገመንግስታዊ ሃላፊነት እና አገባብ ሁኔታውን እንደሚቆጣጠር የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቁርጥ ሃሳብ ማድረጉን ዘግቧል።

በሌሎች የዜና አውታሮች ዘገባ አንተደገለጸው ደሞ በጂጂጋ አስከፊ የሆነ ብሔር ተኮር ጥቃት እንደተነሳ እና መከላከያ ሰራዊት በጂጂጋ ከገባ በኋላ ከጉዳዮ ጋር በተያያዘ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር በቁጥጥር ስር እንደዋሉም ተሰምቷል ፤ ሆኖም የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ሁኔታውን የሚያረጋግጥ ዘገባ አላወጡም። በጂጂጋ የንግድ ቤቶችን ኢላማ ያደረገ የለየለት ዘረፋ እንደበረም ታውቋል ። ሆኖም እስካሁን በሰው ህይወት ላይ ስለደረሰው ጉዳት የታወቀ ነገር የለም።

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,864FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here