ቦርከና
ሃምሌ 25 2010 ዓ.ም.
ለክቡር
የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር
ዶክተር ዐቢይ አህመድ
የተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር
ከዛሬ ነገ ኢትዮጵያ በእርስ በርስ ጦርነት በደም ትጥለቀለቃለች ተብሎ ሕዝብ የተጨነቀባቸዉ ቀናቶቸ ነበሩ፡፡ የአገዛዙ ክፍልም ኢትዮጵያ እንደ ሶርያ ትሆናለች በማለት ሕዝቡን ያስፈራሩት ነበር፡፡ ነገር ግን አንድ ተዓምር ተፈጠረ፡፡ ይህም ለዉጥ የአንድ ብልህ መሪ መፈጠር ነበር፡፡ የሕዝቡ እምነት በአንድ ጊዜ ተቀየረ፡፡ አንድነት፣ ፍቅር፣ ይቅርታ፣ ዴሞክራሲ፣ ሥልጣኔ፣ መደመር፣ እነዚህ የመሳሰሉ ያልታወቁ አዲስ ፍልስፍናዎች በመሆናቸዉ በሕዝቡ ላይ ከዳር እስከ ዳር ብዙ ተስፋና አዲስ ያልነበረ እምነትን ተፈጠረ፡፡ ይህም በሰላምና በትዕግስት የተገኘ ድል ዓለምን አስደነቀዉ፡፡ ወድቆና ተንኮትኩቶ የነበረዉ የኢትዮጵያ ገበና በአንድ ጊዜ ከአድማስ ባሻገር ለሚገዉ ዓለም ጭምር ከአድንቆት በላይ ያልተጠበቁ ተስፋዎችና እምነቶችን ቀሰቀሰ፡፡ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀንድ ብቻ ሳይሆን የመላዉ አፍሪካ መብራት ነች የሚል አነጋገርም ከብዙዎች ቦታ ተሰሙ፡፡ የጎሣ ትግልና ጦርነት ቀርቶ ኢትዮጵያ አንድ የምትሆንበት መፍትሔ ተገኘ፡፡ ተአምሩ በዚህ ብቻ አላከተመም፤ የብዙ ሺ ሕይወት የተከፈለበት የኤርትራና የኢትዮጵያ ጦርነት ከሃያ ዐመት ጠላትነት፣ ጥላቻና ጭካኔ በኋላ ካለ አንድ አሰታራቂና ሽማግሌ መሪዎች ተቃቅፈዉና ተሳስመዉ ማየቱ ያላስደነቀዉ ሕዝብ አለ ለማለት ያስቸግራል፡፡ ብዙ ፖለቲከኞችም መደነቅ ብቻ ሳይሆን ቅናትም የተሰማቸዉ ነበሩ፡፡ ይህ ሁሉ በአጭር ጊዜ የተፈጸመ ለዉጥ የአንድ ፖለቲካ ፓርቲ አቋም ሳይሆን የአንድ ሰዉ ብቻ ትግል ያመጣቸዉ ዉጤቶች ናቸዉ፡፡
ሙሉውን በፒዲ ኤፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
__
ማስታወሻ:በዚህ ጽሁፍ ላይ የተንጸባረቁ ሳሃቦች የጸሃፊውን/የጸሃፊዋን እንጂ የድረገጹን አቋም አያንጸባርቁም።
ነጻ አስተያየት ወይንም ሃሳብ በዚህ ድረ ገጽ ለማውጣት ጽሁፍዎትን በeditor@borkena.com ወይንም በ info@borkena.com ይላኩልን።