spot_img
Sunday, April 2, 2023
Homeአበይት ዜናየአርበኞች ግንቦት 7 አመራር አባላት በዛሬው እለት አዲስ አበባ ገብተዋል

የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር አባላት በዛሬው እለት አዲስ አበባ ገብተዋል

- Advertisement -
 ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ
ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ
ፎቶ : ኤ ኤፍ ፒ በዮናስ ታደሰ
AFP

ቦርከና
ጳጉሜ 4 2010 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ መንግስት የትጥቅ ትግል ለሚያደርጉ ተቃዋሚዎች ሃገር ቤት ገብተው በሰላማዊ መንገድ እንዲታገሉ ያደረገውን ጥሪ ተከትሎ ፤ የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁኔታ ለሰላማዊ ትግል እንደሚመች እና እንደማይመች የራሱን ግምገማ በማድረግ ፤ ከመንግስት አካላትም ጋር ድርድር በማድረግ ወደ ሃገር ቤት ለመግባት መወሰኑ የሚታወስ ነው።

በዚሁ መሰረት ዛሬ የድርጂቱ ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ጸሃፊው አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አዲስ አበባ ገብተዋል። ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ጣቢያ እንደደረሱም ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት አቀባበል አድርገውላቸውል።

በአዲስ አበባ ስታዲየም በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የድርጂቱ ደጋፊዎች በተገኙበት ደማቅ የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ አንዳርጋቸው ጽጌም በስታዲየሙ ለተሰበሰቡት ደጋፊዎቻቸው ንግግር አድርገዋል፤ የፖለቲካ መሪዎቹን ለመቀበል ከተደረገው ዝግጂት ጋር በተያያዘ አዲስ አበባ ቀደም ሲል መንግስት በአዋጂ የከለከለው ባንዲራ በከፍተኛ ሁኔታ ተውለብልቧል።

የአርበኞች ግንቦት 7 ወደ ኢትዮጵያ ገብቶ ሰላማዊ ትግል ለመታገል መወሰኑ ተዳክሞ የነበረውን የአንድነት ጎራ ያጠናክረዋል ሲሉ አስተያየታቸውን የሚሰጡ ኢትዮጵያውያን በርካታ ናቸው።

በ አዲስ አበባ ስታዲየም የነበረውን አቀባበል ዝግጂት ቪዲዮ ለማየት ይሄንን ይጫኑ
__
ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,472FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here