spot_img
Wednesday, June 7, 2023
Homeአበይት ዜናአራት የቤንሻንጉል ባለስልጣናት ግድያን ተከትሎ የሰዎች ህይወት ማለፉና የበርካቶች መፈናቀል ተሰማ

አራት የቤንሻንጉል ባለስልጣናት ግድያን ተከትሎ የሰዎች ህይወት ማለፉና የበርካቶች መፈናቀል ተሰማ

- Advertisement -

Benshangul-Gumz-
Google Map

ቦርከና
መስከረም 21 2011 ዓ.ም.

የቤንሻነጉል ጉምዝ ካማሽ ዞን አራት ባለስልጣናት ግድያን ተከትሎ ከአርብ መስከረም 18፣ 2011ዓ.ም ጀምሮ በቤንሻጉል ጉሙዝ ከማሺ ዞን እና በኦሮሚያ ክልለ አጎራባች ወረዳዎች በተፈጠረ ግጭት ስድስትን ንጹሃን ሰዎች መገደላቸዉንና ሌሎች መቁሰላቸዉ ተገለፀ።

የቤኒሻንጉል ጉምዝ ካማሽ ዞን የጸጥታ ጉዳይን በተመለከተ ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ጋር በተዘጋጀ የምክክር መድረክ ለመሳትፍ ወደ ዘጠኝ የሚጠጉ የካማሽ ዞን ከፍተኛ ባለሰልጣናት ወደ ምስራቅ ወለጋ ዞን ተጉዘዉ በመመለስ ላይ እንዳሉ ባልታወቁ ታጣቂ ሀይሎች በተሰነዘረባቸዉ ጥቃት 4 ሰዎች መገደላቸዉ በአካባቢዉ ከፍተኛ ዉጥረት ፈጥሮ መሰንበቱ ይታወቃል፡፡

ጥቃቱን ተከትሎ የኦሮሚያ ክልል የገጠር ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አዲሱ አረጋ በምዕራብ ኦሮሚያ ቀጣይነት ያለው ሰላም ለማረጋገጥም ከኦነግ ጋር በተደረገው ስምምነት በስሙ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች ትጥቃቸውን ፈተው ወደ ካምፕ እንዲገቡ እየተሰራ ነው ሲሉ ተሰምተዋል፡፡

የኦሮሚያ ክልል ቅሊጡ ሸንኮሬ ዞን የፀጥታና አስተዳደር ፅህፈት ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ ታከል ቶሎሳ በበኩላቸዉ በአካባቢዉ ተከስቶ በነበረዉ ግጭት ምክኒያት ከሃምሳ በላይ የመኖሪያ ቤቶች እንደተቃጠሉ፤አራት ሰዎች እንደቆሰሉና በርካቶች ከመኖሪያቸዉ እንደተፈናቀሉ ለቢቢሲ ገልፀዋል፡፡
አክለዉም የፀጥታ ሀይሎች ሁኔታዉን ለማረጋጋት ወደ ሥፍራዉ እንደተሰማራና የተፈጠረዉን ችግር በፍጥነት ለመቆጣጠር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡
የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ፖሊስ ቢሮ ሃላፊ የሆኑት አቶ ሰይፈዲን ሀሩን አደጋዉን ተከትሎ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ ጥፋቱን የፈጸሙት ማንነታቸዉ ያልታወቁ ፀረ ሰላም ሀይሎች እንደሆኑ ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡

ጥቃቱ ከደረሰ በኋላ የመከላከያ ሰራዊት ወደ ሥፍራዉ መሰማራቱ ቢገለፅም ከችግሩ አንጻር ቁጥሩ እጅግ አነስተኛ መሆኑን በአካባቢዉ የሚኖሩ ግለሰቦችን በማነጋገር መረዳት ተችሏል፡፡

ከዚህም ጋር ተያይዞ በአካባቢዉ ይኖሩ የነበሩ የጉምዝ ተወላጆች ቤት ንብረታቸዉን ጥለዉ ወደ ጫካ መሰደዳቸዉንና የኦሮሞ ተወላጆች ደግሞ በአጎራባች ወደሚገኙ የኦሮሚያ ክልል ወረዳዎች እንደተሰደዱ የቤንሻንጉል ክልል የኮሙኒኬሽን ሃላፊ የሆኑት አቶ ዘላለም ጃለታ ተናግረዋል፡፡
ከወር በፊት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ዋና ከተማ አሶሳ በተፈፀመ ብሄርን መሰረት ያደረገ ግጥት የ10 ንፁሃን ዜጎች ህይወት ሲያልፍ በርካቶች መፈናቀላቸዉ ይታወሳል፡፡

ከስፍራዉ የተፈናቀሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ የአማራ ክልል ተወላጆች በባህር ዳር ከተማ በተለያዩ ቤተ ክርስቲያናትና ትምህርት ቤቶች ተጠልለዉ እርዳታ ሲደረግላቸዉ እንደነበርም ይታወቃል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሃገሪቱ በተለያ ክልልሎች ብሄርን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡ በዚህም ሳቢያ በርካቶች የመኖሪያ ቀያቸዉን ጥለዉ እንዲሰደዱ ተገደዋ፡፡

በያዝነዉ ዓመት ብቻ በኦሮሚያ፤ በሶማሊ፤ በደቡብ ክልሎች ተፈጥረዉ በነበሩ ግጭቶች ምክኒያት ከ1.6 ሚሊየን በላይ ዜጎች መሰደዳቸዉን ዩኒሴፍ በነሃሴ ወር ያወጣዉ መረጃ ያመለክታል፡፡

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,879FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here