spot_img
Thursday, November 30, 2023
Homeዜናበአዲስ አበባ አንድ የፌደራል ፖሊስ አባል በመጠጥ ሀይል ተገፋፍቶ በፈፀመው ጥቃት የሁለት...

በአዲስ አበባ አንድ የፌደራል ፖሊስ አባል በመጠጥ ሀይል ተገፋፍቶ በፈፀመው ጥቃት የሁለት ባልደረቦቹን ህይወት አጠፋ

advertisement

ቦርከና
መስከረም 22 2011 ዓ.ም.

በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ወሎ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አንድ የፌደራል ፖሊስ አባል በመጠጥ ሀይል ተገፋፍቶ በባልደረቦቹ ላይ ጥቃት መፈፀሙ ተነግሯል።

ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑን ጠቅሶ እንደዘገበዉ የፌደራል ፖሊስ አባሉ በባልደረቦቹ ላይ በፈፀመው ጥቃትም ሁለት የፌደራል ፖሊስ አባላት ህይወት አልፏል።

ፖሊስ ጥቃቱን ለማስቆም በወሰደው እርምጃም ጥቃቱን የፈፀመው የፌደራል ፖሊስ አባል ህይወቱ ማለፉን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል አስታውቀዋል።

ቦርከና ያነጋገራቸዉ የአካባቢዉ ነዋሪወች ከሌሊቱ አካባቢ ጀምሮ በሥፍዉ ተኩስ ድማፅ ይሰማ እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ጥቃቱ የተፈፀመዉ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሸዋ ሱፐር ማርኬት እየተባለ በሚጠራዉ ሥፍራ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የሚኖሩበት ህንፃ አቅራቢያ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡

ሆኖም በተኩስ ልዉዉጡ ወቅት ከተገደሉት ዉጭ ጉዳት የደረሰበት የፖሊስ አባል ወይም ሌላ ግለሰብ ስለመኖሩ ለማረጋገጥ አልተቻለም፡፡

በአሁኑ ወቅም በስፍራው ተስተጓጉሎ የነበረው የትራፊክ እና ሌሎች እንቅስቃሴዎች ወደ መደበኛ ሁኔታቸው መመለሳቸውን ገልፀዋል።
ግድያዉ በተፈፀመበት አካባቢ እስከ ጠዋቱ 2፡30 መንገድ ዝግ እንደነበርና የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ መስተጓጎል ተፈጥሮ እደነበረ በአካባቢዉ የሚሰራ ግለሰብ ለቦርከና ተናግሯል፡፡

በሰለሞን ይመር
___
ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here