spot_img
Wednesday, June 7, 2023
Homeአበይት ዜና240 የታጠቁ ወታደሮች ትላንት ወደ ቤተ መንግስት ዘው ማለታቸው ተሰማ

240 የታጠቁ ወታደሮች ትላንት ወደ ቤተ መንግስት ዘው ማለታቸው ተሰማ

- Advertisement -

Special Forces_

ቦርከና
ጥቅምት 1 ፤ 2011 ዓ.ም

በትላንትናው እለት ቁጥራቸው 240 የሚሆኑ የመንግስት ወታደሮች ከነትጥቃቸው ወደ ቤተ መንግስት መግባታቸው ተሰምቷል። ወታደሮቹ የመከላከያ ልዮ ሰራዊት አባል ሲሆኑ ቀደም ሲል በቡራዩ ተፈጥሮ በነበረው ችግር ምክንያት በዚያው ተሰማርተው ሁኔውን ሲያረጋጉ የቆዮ መሆናቸው ከመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘገባ ታውቋል።

ወታደሮቹ ወደ ቤተመንግስት የመጡበት ምክንያት የደሞዝ እና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስሩን እናነጋግራለን በሚል እንደሆም ታውቋል ፤ እንደ መንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘገባ።

ምንም እንኳን ያለ ቀጠሮ ዘው ብለው ወደ ቤተመንግስት ቢገቡም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንዳናገሯቸው እና አለን ያሉትን ችግር በመስማት በጥናት ላይ የተመሰረተ ማስተካከያ እንደሚደረግ እንደነገሯቸው ታውቋል።

ውይይታቸውን እንደጨረሱ ከወታደሮቹ ጋር “ፑሽ አፕ” ሰርተው ሁኔታውን የተለሳለሰ እንደነበር ለማሳየት ሞክረዋል – ጠቅላይ ሚኒስትሩ ።

በጉዳዮ ላይ በማህበራዊ ሚዲያ የተለያዮ አስተያየቶች እየተሰነዘሩ ነው ፤ አብዛኞው ኢትዮጵያዊ ወታደሮቹ የዲሲፕሊን ጥሰት አንደፈጸሙ እና ከበስከጀርባቸው ሌላ ኃይል ሊኖር ይቻላል በሚል ግምት ሁኔታው እንዲጣራ እየጠየቁ ነው ።
__
ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,879FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here