spot_img
Tuesday, November 28, 2023
Homeአበይት ዜናበጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዲስ ካቢኔ ሴቶች እኩሌታ የስልጣን ቦታ ያዙ

በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዲስ ካቢኔ ሴቶች እኩሌታ የስልጣን ቦታ ያዙ

advertisement
Ethiopia-_-New-Cabinet
ፎቶ ምንጭ ፤ ኢ ብ ኮ

ቦርከና
ጥቅምት 7 ፤ 2011

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አዲሱን ካቢኔያቸውን ትላንት በተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው አጸድቀዋል። የፖርቲው ሴት ፖለቲከኞች በአዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ካቢኔ እኩሌታውን የስልጣን ቦታ እንደያዙም ታውቋል። “የጾታ እኩልነት የተረጋገጠበት ካቢኔ” ነው በሚል ዜናው የዓለም ዓቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስቧል።

ከቁጥር በተጨማሪም የኢህአዴግ ሴት ፖለቲካኖች ቁልፍ የሆኑ የካቢኔ ስልጣን ይዘዋል። አዲስ የሚዋቀረው የሰላም ሚኒስቴር ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥሎ ቁልፍ የስልጣን ቦታ እንደሆነ ተንታኞች እየተናገሩ ሲሆን ቀደም ሲል በተወካዮች ምክር ቤት በአፈጉባኤነት ሲያገለግሉ የነበሩት ወ/ሮ ሙፈሪያት ከማል በሚኒስትርነት እንዲመሩት ተሾመዋል። በኢትዮጵያ የህግ የበላይነትን ማረጋገጥና ሰላምን ማስፈን ተልዕኮ የተሰጠው አዲሱ የሰላም ሚኒስቴር የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ፤ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ፤የፋይናንስ ደህንነት መረጃ ማዕከል ፤ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽንን ፤ የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነቶች ኤጀንሲን ፤ የብሔራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽንን ፤የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ስትራቴጂክ ጥናት ኢንስቲትዩትን እና የሰራተኞች እና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ ኤጀንሲን በበላይነት እንደሚመራ ወይንም የእነዚህ መስሪያቤቶች ተጠሪነት ለሰላም ሚኒስቴር እንደሆነ ታውቋል። በተጨማሪም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከሃይማኖት ተቋማት ጋርም እንደሚሰራ ታውቋል።

ሌላ ለኢህአዴግ ሴት ፖለቲከኞች የተሰጠ ቁልፍ ቦታ የመከላከያ ሚኒስቴር ነው። ኢንጂነር አይሻ መሃመድ የሚኒቴር መስሪያ ቤቱን እንዲመሩ ተሾመዋል።

አዲሱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ካቢኔ የጎሳ እና የጾታ ስብጥሩ ላይ ጥያቄ ባያስነሳም ብቃትን ግምት ውስጥ ያስገባ አይደለም የሚል ትችት ተሰንዝሮበታል፤ በፖለቲካ ተንታኞች።

የካቢኔው ሙሉ ዝርዝር የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ባዘጋጀው የኢንፎግራፊክ ላይ እንደሚከተለው ቀርቧል

የካቢኔ አባላት
ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,920FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here