spot_img
Wednesday, June 7, 2023
Homeአበይት ዜናየታጠቁ ወታደሮች ወደ ቤተመንግስት የመጡት የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ ማጨናገፍ ነበር – ጠ/ሚ...

የታጠቁ ወታደሮች ወደ ቤተመንግስት የመጡት የተጀመረውን ሀገራዊ ለውጥ ማጨናገፍ ነበር – ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ

- Advertisement -

Special Forces_

ቦርከና
ጥቅምት 8 ፤ 2011

በቅርቡ የደመወዝ ጭማሬ ለመጠየቅ ወደ ቤተ መንግስት ያመሩት ወታደሮች አገራዊ ለውጡን ለማደናቀፍ ያለሙ አካትን ተልዕኮ አንግበው እንደነበር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡

በ2011 የህዝብ ተወካዮችና የፌደሬሽን ምክር ቤቶች የጋራ መከፍቻ ላይ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ ባደረጉት ንግግር ላይ ለፓርላማ አባላት መልሽ ለመስጠት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ የታጠቀ ወታደር ወደ ቤተ መንግስት የመጣው አገራዊ ለውጡን ለማደናቀፍ ታስቦ የተደረገ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

ይሁን እንጂ ሁሉም የመጡት ወታደሮች ይህን እሳቤ ይዘው ነው የመጡት ለማለት እንደሚያስቸግርና በአንዳንድ ተንኮለኞች ሴራ ተጠንስሶ የተፈፀመ ድርጊት ነው እንደነበር ገልፀዋል፡፡

በዕለቱ የተወሰደው እርምጃ በጥንቃቄ ባይሆን ኖሮ አገርን ወደቀውስ የሚከት ክስተት እንደነበርም ነው ያብራሩት፡፡አሁን ላይ ራሱ ወታደሩ በሴራው ውስጥ የነበሩትን የድርጊቱን መሪዎች እየለየ አሳልፎ እየሰጠ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡

በወቅቱ የወታደሮቹን አመጣጥ ወታደራዊ ጥበብ በሚጠይቀው መልኩ አረጋግቶ መመለስ መቻሉ አገርን የማትረፍ ወሳኝ እርምጃ አድርጌ ነው የምወስደውም ብለዋል፡፡ “እየተዝናነሁ፣ እየሳቅኩ ቃለ መጠይቅ የሰጠሁት መንግስታችን ተነካ ብለው ከተለያዩ አቅጣጫዎች ህዝቡ ለመዋጋት እየመጣ ስለነበረ እነሱን ለማረጋጋት ነበርም” ብለዋል፡፡

ጄኔራል ሰዓረ መኮንን ባለፈው ቅዳሜ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ «ግለሰቦች የገፋፉት እና ያርገበገቡት ነው። እነዚህን ግለሰቦች ማን ነው የገፋቸው? የሚለውን አጣርተን እርምጃ እንወስዳለን።» ብለው ነበር።

ወታደሮቹ ወደ ቤተ-መንግሥት ለመሄድ የወሰኑት «በተበተነ አኳኋን» እንደሆነ የገለጹት ጄኔራል ሰዓረ የተፈጸመው ጥፋት ተራ የዲሲፕሊን ግድፈት እንዳልሆነ ጠቅሰዋል።

በሰለሞን ይመር

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,879FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here