spot_img
Saturday, September 23, 2023
Homeዜናጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ የመጀመሪያውን የአውሮፓ ጉብኝት በፈረንሳይና በጀርመን ሊያደርጉ ነው

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ የመጀመሪያውን የአውሮፓ ጉብኝት በፈረንሳይና በጀርመን ሊያደርጉ ነው

advertisement
Abiy Ahmed አብይ አህመድ
ዶ/ር አብይ አህመድ

ቦርከና
ጥቅምት 8 ፤ 2011

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በቀጣዩ ሳምንት በአውሮፓ ይፋዊ የስራ ጉበኝት ያደርጋሉ ሲል ፋና ብሮደካስቲንግ ዘግቧል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአውሮፓ ጉብኝታቸውን ከፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በመቀጠልም ከጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ ሜርክል ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ይወያያሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዘገባዉ ያስረዳል።

ከዚህም በተጨማሪ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥቅምት 21 ቀን 2011 ዓ.ም ከተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ከሚውጣጡ 25 ሺህ ኢትዮጵያውያን ጋር በፍራንክፈርት ዉይይት እንደሚያደርጉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ አስታዉቋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የአውሮፓ ጉብኝት “አንድ ሆነን እንነሳ ነገን በጋራ እንገንባ” በሚል መሪ ቃል የሚካሄድ እንደሆነ ተነግሯል።

መግለጫውን የሰጡት የ ሚኒስቴሩ ቃል አቃባይ አቶ መለስ ዓለም ኢትዮጵያ በአዲስ የለውጥ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች ያሉት ሲሆን፥ ዳያስፖራውን የማያሳትፍ የሀገር ግንባታ ጎዶሎ ነዉ ማለታቸዉን ዘገባዉ አስፍሯል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉብኝቱን የሚያደርጉት በሀገራቱ መሪዎች በቀረበላቸው ግብዣ መሰረት ነው።

ከዚህ ቀደም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ወደ ሰሜን አሜሪካ በማቅናት በዚያ ከሚኖሩ ኢትዮጲያዉያን ጋር ዉይይት ማድረጋቸዉ ይታወቃል፡፡

በሰለሞን ይመር

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,676FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here