spot_img
Saturday, September 30, 2023
Homeአበይት ዜናየቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ መሐመድ የታሰሩበትን ቢሮ መስታወት በመስበር ለማምለጥ ሙከራ...

የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ መሐመድ የታሰሩበትን ቢሮ መስታወት በመስበር ለማምለጥ ሙከራ አድርገዋል፡ ፖሊስ

advertisement

Abdi-Iley_

ቦርከና
ጥቅምት 9 ፤ 2011

“የቀድሞው የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ መሐመድ ከእስር ቤት መስኮት ሰብረው ለማምለጥ ሙከራ አድርገዋል” ሲል ፖሊስን ጠቅሶ የኢትዮጲያ ዜና አገልግሎት ዛሬ ዘግቧል።

አቶ አብዲ ዛሬ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀጠሮ ችሎት በቀረቡበት ወቅት መርማሪ ፖሊስ እንደገለጸው አቶ አብዲ መሐመድ ለደህንነታቸውና ለጤናቸው ሲባል የፖሊስ ቢሮ ውስጥ ታስረው የነበረ ሲሆን የታሰሩበትን ቢሮ መስታወት በመስበርና አንድ የጥበቃ አባልን ጉሮሮ በማነቅ ለማምለጥ ሙከራ አድርገዋል ብሏል ዘገባዉ።

ይሁን አንጅ አቶ አብዲ መሐመድ ድርጊቱ ሆን ብሎ ስሜን ለማጥፋትና እኔን ለመምታት የተደረገ ሴራ በማለት ድርጊቱን ፈጽመዋል መባሉ ውሸት መሆኑንና በእርሳቸው ላይም ከፍተኛ ጫና እየተደረገባቸው እንደሆነ መናገራቸዉን የኢዜዓ ዘገባ ያመለክታል።

ምቹ ባልሆነ እስር ቤት መታሰራቸውን፣ የአዕምሮ ህመምተኛ የሆነ ታሳሪ የታሰሩበትን ክፍል በር ገንጥሎ በመግባት ሁለት ቀን ጉዳት ሊያደርስባቸው እንደሞከረና ይህም በደህንነታቸው ላይ ስጋት እንደፈጠረባቸው ገልጸዋል።

የታሰሩበት እስር ቤት የማይመችና በጤናቸው ላይም እክል እንደፈጠረባቸውም የተናገሩት አቶ አብዲ በአንድ አጋጣሚም አንድ አስረኛ የሽንት ቤት በር ገንጥሎ እሳቸው ላይ በመጣል ጉዳት ሊያደርስ መሞከሩንም ተናግረዋል።

እንደ ኢዚዓ ዘገባ ከሆነ ፖሊስ ከእርሳቸው ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት ለግጭቱ መቀስቀስ ተጠያቂ መሆናቸውንና በዚህም ተጸጽተው ይቅርታ መጠያቃቸውን ገልጿል።

ፍርድ ቤቱ ምርመራውን እያካሄደ ያለው ፖሊስ የምርመራውን ውጤት ለጥቅምት 19 ቀን 2011 ዓ.ም ይዞ እንዲቀርብ በማሳሰብ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

አቶ አብዲ መሐመድ ከሐምሌ 26-30 ቀን 2010 ዓ.ም በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ ሳቢያ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወቃል።

በሰለሞን ይመር

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,705FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here