spot_img
Monday, October 2, 2023
Homeዜናየኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር...

የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ስምምነት ላይ ደረሰ

advertisement
ONLF_Ethiopia
ፎቶ ምንጭ : ፍና ብሮድካስቲንግ

ጥቅምት 12 ፤ 2011 ዓ.ም.

ለረጂም አመታት በትጥቅ ትግል ላይ የነበረዉ የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጭ ግንባር (ኦብነግ) በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ማስታወቃቸዉን ፋና ብሮድካስቲን ኮርፖሬት ዘግቧል።

እንደዘገባዉ ከሆን የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃ አውጪ ግንባርና የኢትዮጵያ መንግስት በትላንትናዉ ዕለት በአስመራ ባደረጉት ድርድር ነዉ ከስምምነት ላይ የደረሱት።

በስምምነቱም የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር ወደ ሀገር ቤት ተመልሶ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ስምምነት ላይ መድረሱን እንደተገለፀ ዘገባዉ ያመላክታል፤ ሆኖም ግን ሌሎች የስምምነቱ ዝርዝር ነጥቦች አላተካተቱም።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ያቀረቡትን የሰላም ጥሪ ተከትሎ ኦነግ፣ አርበኞች ግንቦት 7 እንዲሁም የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደምህት) የትጥቅ ትግል በማቆም ወደ ሀገር ቤት መግባታቸው ይታወቃል።

ሆኖም ግን መንግስት በትጥቅ ትግል ሲያደርጉ ከነበሩ ድርጅቶች ጋር ያደረጋቸዉ ዝርዝር ስምንነቶች በዉል ባለመገለፃቸዉ ምክኒያት የተለያዩ እሰጣ እገባዎች ሲፈጠሩ ታይተዋል፡፡

ለአብን ያክል የኦሮሞ ነፃነት ግንባር የትጥቅ ትግል በማቆም ወደ ሀገር ቤት መግባቱን ቢነገርም የኦነግ ታጣቂዎች ነን የሚሉ ሀይሎች በተለያዩ ቦታዎ ች ትጥቅ ሳይፈቱ እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ ታዉቋል፡፡

የኦነግ አመራሮችም ትጥቅ ለመፍታት ተስማምተን አልመጣንም በማለት ለመገናኛ ብዙሀን ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡

በሰለሞን ይመር

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,723FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here