spot_img
Wednesday, June 7, 2023
Homeዜናኮሎኔል ጎሹ ወልዴ ከ32 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ ወደ ሃገራቸው ተመለሱ

ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ ከ32 ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ ወደ ሃገራቸው ተመለሱ

- Advertisement -
Goshu-Wolde_
ምንጭ : ኢቢሲ

ቦርከና
ጥቅምት 20 ፤ 2011 ዓ.ም.

በደርግ መንግስት በትምህርት ሚኒስቴርነት እና በውጭ ጉዳዮ ሚኒስትርነት ያገለገሉት ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ ከሰላሳ ሁለት ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ ከትናንት በስቲያ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል፡፡

እ.ኤ.አ አቆጣጠር በ 1986 ዓ.ም. የስራ መልቀቂያቸውን ከኒውዮርክ ለኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም መንግስት ከላኩ ጊዜ ጀምሮ ኑሮአቸውን በአሜሪካን ሃገር አድርገው ቆይተዋል፡፡

አሁን የ76 ዓመት አዛውንት የሆኑት ኮሎኔል ጎሹ የደርግ መንግስት በወደቀ ማግስት ኢትዮጵያን ከህወሓት አገዛዝ ለመታደግ በተደረገው ጥረት የመድህን ፖርቲን በመምራት አስተዋጾ ለማድረግ ሞክረዋል፡፡

ከዚያ በኋላ ለረዢም ጊዜ በፖለቲካ ጉዳይ በአደባባይ ድምጻቸውን ሳያሰሙ የቆዮት ጉምቱ ፖለቲከኛ በቅርቡ የአብይ አህመድ መንግስት የወሰዳቸውን የለውጥ ርምጃዎች በማድነቅ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲደግፈው የቪዲዮመልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል፡፡

የአሁኑ አመጣጣቸው ዘመድ ለመጠየቅ እና በኢትዮጵያ ውስጥ እየታዩ ያሉትን ለውጦች ለመደገፍ እንደሆነ የሚናገሩት ጎሹ ምንም አይነት የስልጣን ፍላጎት እንደሌላቸው ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,879FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here