spot_img
Sunday, May 28, 2023
Homeአበይት ዜናወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሰባት ዓመታት ስደት በኋላ ዛሬ ኢትዮጵያ ገብታለች

ወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሰባት ዓመታት ስደት በኋላ ዛሬ ኢትዮጵያ ገብታለች

- Advertisement -

Birtukan Mideksa

ቦርከና
ጥቅምት 29 2011 ዓ ም

ወ/ት ብርቱካን ሚዴቅሳ ከሰባት ዓመታት የስደት ቆይታ በኋላ ከሰዓታት በፊት ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ እንደደረሰች የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዘገባ ያመለክታል።

በህግ ትምህርት ከአዲስ አባባ ዮኒቨርሲቲ ዲግሪዋን የወሰደችው ብርቱካን ሚዴቅሳ በፌደራል ፍርድ ቤት በዳኝነት ከማገልገሏም ባሻገር ፤ በኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፖለቲካ በአመራር ደረጃ እንዳገለገለች ይታወቃል።

የምርጫ 97ትን ተከትሎ የቅንጂት ለአንድነት መሪዎች በታሰሩበት ሰዓት አብራ ለአንድ ዓመት ከስድስት ወር ጊዜ በላይ ታስራ የተፈታች ሲሆን ፤ ኋላም ቅንጂት በመፍረሱ
ምክንያት ፍትህ ለአንድነት እና ለዲሞክራሲን ፓርቲና በማቋቋም ግንባር ቀደሚ ሚና ተጫውታለች።

ከዚሁ ፓርቲ ሃላፊነቷ ጋር በተያያዘ ለስራ ወደ አውሮፖ ተጉዛ በነበረበት ጊዜ ባደረገችው ንግግር ምክንያት በምህረት ከእስር የተፈታችበትን ሁኔታ ጥሳለች በሚል የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ መንግስት እንደገና እንድትታሰር ተደርጋ ብዙ መከራ መቀበሏ ይታወሳል።በዓለም አቀፉ እና በኢትዮጵያውያን ግፊት ከእስር ከተፈታች በኋላ ወደ አሜሪካን ተሰዳ ለሰባት ዓመታት ያህል ቆይታለች።

በአሜሪካ በነበረችበት ጊዜ በሚባለው የዲሞክራሲ ተቋም ፊሎሽፕ በማግኘት ምርምር የሰራች ሲሆን በሃርቫርድ ዮኒቨርስቲም በመንግስት አስተዳደር የማስትሬት ዲግሪ አግኝታለች።

ወደ ሃገር ቤት የተመለሰችው በመንግስት ግብዣ እንደሆነ የአሜሪካ ድምጽ ራዲዮ ትላንት ካቀረበው ዘገባ መረዳት ተችሏል ፤ እየተደረገ ባለው የለውጥ ሂደት ውስጥ በዲሞክራሲ ተቋማት ግንባታ ላይ ለመሰራት ፍላጎት እንዳላትም ገልጻለች።
___
ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,856FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here