spot_img
Wednesday, June 7, 2023
Homeአበይት ዜናብርቱካን ሚዴቅሳ ምርጫ ቦርድን ለማደራጀት ምክር ቤቱ እምነት ጣለባቸው

ብርቱካን ሚዴቅሳ ምርጫ ቦርድን ለማደራጀት ምክር ቤቱ እምነት ጣለባቸው

- Advertisement -
ብርቱካን ሚዴቅሳ
ብርቱካን ሚዴቅሳ በፓርላማ ተገኝታ ቃለ መሃላ ስትፈጽም
ፎቶ : ኢብኮ

ቦርከና
ኅዳር 14 2011 ዓ.ም.

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትላንት ባካሄደው ስብሰባ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በእጩነት ያቀረቧቸውን ብርቱካን ሚዴቅሳን ሹመት አጽቋል።

ሹመቱ በአብላጫ ድምጽ በአራት ተቃውሞ እና በሶስት ድምጽ ተአቅቦ ነው የጸደቀው።

የአንድነት ለዲሞክራሲ እና ለፍትህ ተቃዋሚ ፓርቲ (በአሁኑ አጠራር ተፎካካሪ) መሪ የነበሩት ብርቱካን ሚዴቅሳ በፖለቲካ አመለካከታቸው ያለ አግባብ ታስረው ኢሰብዓዊ የሆነ ድርጊት እንደተፈጸመባቸው የሚታወስ ሲሆን ከተፈቱም በኋላ በስደት በአሜሪካን ሃገር ለሰባት ዓመታት ቆይተው በቅርቡ በመንግስት ግብዣ ወደ ሃገራቸው ተመልሰዋል።

አሜሪካን ሃገር በነበራቸው ቆይታ በሃርቫርድ ዮኒቨርሲቲ በፖሊሲ እና ህዝብ አስተዳደር ትምህርት የማስትሬት ዲግሪ ያገኙ ሲሆን ፤ “ናሺናል ኢንዶውመንት ፎር ዲሞክራሲ” በሚባለው የአሜሪካ ድርጂት በፊሎሺፕነት የተለያዮ ጥናቶችን እንዳካሄዱ የአሜሪካ ቆይታ ታሪካቸው ያስረዳል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ብርቱካን ሚዴቅሳ ምርጫ ቦርድን ነጻ ፤ ተዓማኒ እና ገለልተኛ ተቋም በማድረግ በ አዲስ መልክ ለማዋቀር የታሰበውን ለውጥ ያሳካሉ ብለው ያምናሉ ፤ ብዙ ኢትዮጵያውያንም ተመሳሳይ እይታ አላቸው።

በሌላ በኩል እንደ ጃዋር ሞሃመድ ያሉ የአክራሪ ኦሮሞ ብሄርተኛ “አክቲቪስቶች” የብርቱካንን መመረጥ አግባብ አይደለም በሚል በማህበራዊ ድረ ገጽ የተቃውሞ ዘመቻ የሚመስል ነገር አስነስተዋል።

ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
12,876FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here