spot_img
Tuesday, October 3, 2023
Homeአበይት ዜናበትግራይ ዘጠኝ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

በትግራይ ዘጠኝ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

advertisement

ትግራይ
ቦርከና
ኅዳር 16 ፤ 2011 ዓ. ም.

ዛሬ በትግራይ ዘጠኝ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ እንደተካሄደ የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። በአድዋ፣ አክሱም፣ ኮረም፣ አዲ ሽሁ፣ አላማጣ፣ መኾኒ፣ ሰቲት ሁመራ፣ ዓብይ ዓዲ እና ራያ የተካሄዱት ሰልፎች የህግ የበላይነት እንዲከበር ፤ በሙስና ተጠርጥረው የተያዙ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ብቻ እንዲዳኝ ፤ እና መሰል ጥያቄዎች ተስተጋብተዋል -እንደ መንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘገባ።

በተጨማሪም የማንነት ጥያቄዎች (የወልዋይት እና የራያን የሚመለከት ነው) የማንነት ጥያቄዎች አይደሉም ፤ ህዝቡን አይወክሉም የሚሉ መፈክሮች በየከተሞቹ በነበሩት ሰልፎች ላይ ተስተጋብተው እንደነበር ለማወቅም ተችሏል።

በወልቃይት እና በራያ የማንነት ጥያቄ ለአመታት ሲስተጋባ መቆየቱ ይታወሳል። እነዚህ አካባቢዎች ወደ ትግራይ የተከለሉት የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ስልጣን መያዝን ተከትሎ መሆኑ ይታወቃል።
___
ወቅታዊ እና ሚዛናዊ መረጃን ለማግኘት ቦርከናን በፌስ ቡክ ላይክ ያድርጉ።

- Advertisement -Early Bird Holiday Deals! Before you know it, the holidays will be right around the corner! Take advantage of our early bird deals today and save up to $40 on our fees with code SPOT40!
Stay Connected
28,789FansLike
13,723FollowersFollow
8,540SubscribersSubscribe
Stacy Adams
Must Read
Related News

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here